Abduljebar Mohammed Nur


Channel's geo and language: not specified, not specified
Category: not specified



Channel's geo and language
not specified, not specified
Category
not specified
Statistics
Posts filter






Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Sefina 10


Forward from: MuhammedSirage M/Nur TextPosts
إنا لله وإنا إليه راجعون
የሱና ወንድም ሞት ቀላል አይደለምና ብዙ ያጎድላል!
መቀመጫቸውን ሳውዲ ካደረጉትና በሰለፊያ ዳዕዋ ላይ በተለያዩ መንገዶች ጥሪን ሲያደርጉ ከነበሩ ወንድሞቻችን ውስጥ አንዱ ነበር ። በትግርኛ ቋንቋ ሰለፊያን ለመርዳት ከመታገሉ ጋር በአማርኛም የቻለውን ያህል ይሰራ ነበር ።

በደረሰበት ህመም ምክንያት ከጥቂት ወራት በፊት በሳውዲ ጂዳ ህክምና ሲደረግለት በነበረ ሰአት በቴሌግራም አናግሬው በትንሹ ተጫውተን ነበር ። ለ 3 ወራት ያህል በሽታ ላይ እንደሆነ ነገረኝ ። ህመሙ እየጠናበት እንደመጣ ከገለፀልኝ በሇላ የሚሆነውን አዋቂው አላህ ነው ነበር ያለኝ ።
በጠናበት በሽታ ላይ ሆኖ እንኳን ስለ ዳዕዋ ያወራኝና ይጠይቀኝ ነበር ። ለሰለፊ ወንድሞቹም ሰላምታን እንዳደርስለት አደራውን አደረሰኝ ።

በዛሬው እለት ሞቱን ከአንዳንድ ወንድሞች ሰማሁ ።
ውድ ወንድማችን
أبو بتول إبراهيم آدم
በአካል ባላውቀውም ሞቱን መስማቴ ለኔ ቀላል አልነበረም! የሱና ወንድሜ ፣ "የማላውቀው" ወዳጄ ፣ የሱና ወንድሜ ነውና ‼ ወዳጄ አላህ ይማርህ!

اللهم اغفر له وارحمه وأكرم نزله ووسع مدخله ونقه من الذنوب كما ينقى الثوب الأبيض من الدنس ..


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Afwan net worku aschgarie slehone new


Sefina qirat 9


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Abduljebar Mohammed nur sefina 8


🔈#ትንሽ ስለ ተብሊግ

🔶ማነው በጥሩ የሚያዘው ከመጥፎ የሚከለክለው ከሚለው ሙሐደራ የተወሰደ አጭር ትምህርት

🎙 በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ)

🌐 https://t.me/shakirsultan


Forward from: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ሰለምቴነት ማሸማቀቂያ አይደለም!
~
አንዳንድ ሰዎች በእምነታዊ ጉዳዮች ላይ ስሜታቸውን ለመከተል፣ ከወረዱበት ለመውረድ ፈቃደኛ ያልሆላቸውን ሙስሊም ወደ ኋላ ታሪኩ በማጠንጠን “አንተ ሰለምቴ አይደለህ? ምን ታውቃለህ?” እያሉ ሊያሸማቅቁ ይጥራሉ። የተለየ አውቀው፣ የተሻሉ ሆነው ሳይሆን እንዲሁ የነሱን ስሜት ተከትሎ ስላላጨበጨበ ብቻ አንድን ሙስሊም በዚህ መልኩ ለማሸማቀቅ መሞከር ጋጠ-ወጥነት ነው።
ሰለምቴነት ክብር እንጂ ነውር አይደለም። ሰለምቴነት ገድል እንጂ ማሸማቀቂያ አይደለም። በዚህ ፈተናው በበዛበት፣ የጥፋት ሃይሎች በሚርመሰመሱበት፣ ኢስላምን የሚያጠለሹ አካላት እንደ አሸን በፈሉበት፣ እጅግ ከባባድ ማደናገሪያዎች ያለ ገደብ በሚለቀቁበት ዘመን በምንም ሰበብ ቢሆን ወደ ኢስላም የሚመጡ ሰዎች ሊከበሩ እንጂ ሊጠለሹ አይገባቸውም። ድክመትም ካለባቸው መሸፈ፞ን እንጂ ማጋለጥ አይገባም። ከቻልን ሞራል እንስጥ። ይህን ማድረግ ካቃተን በማሸማቀቅ ገፍተን እንዳናስወጣቸው እንጠንቀቅ።
ክርስቲያን ወይም አይሁድ የነበረ ሰውኮ ወደ ኢስላም ቢገባ በእጥፍ እንደሚመነዳ ነብዩ ﷺ ተናግረዋል። [ቡኻሪና ሙስሊም] አልኢማም አልቡኻሪ ረሒመሁላህ በሶሒሐቸው بَابُ فَضْلِ مَنْ أَسْلَمَ مِنْ أَهْلِ الكِتَابَيْنِ የሚል ርእስ እንዳሰፈሩ እናስተውል። ‘ፈድል’ ማለት ልቅና፣ ብልጫ ማለት ነው። ነብያችን ﷺ ለሮማው ንጉስ ሒረቅል በፃፉት ደብዳቤ ላይ ወደ ኢስላም ሲጠሩት ምን ነበር ያሉት?
أَسْلِمْ تَسْلَمْ، يُؤْتِكَ اللَّهُ أَجْرَكَ مَرَّتَيْنِ
“ስለም። ትድናለህ። አላህ ምንዳህን #ሁለት_ጊዜ ይሰጥሀል።” [ቡኻሪና ሙስሊም] ይሄ መልእክት በሒረቅል ላይ ብቻ የተገደበ አይደለም። የኢብኑ ሐጀርን ማብራሪያ ይመልከቱ። [ፈትሑል ባሪ፡ 8/221]
በነገራችን ላይ አንድ ካፊር ወደ ኢስላም ከገባ ከመስለሙ በፊት ሲፈፅማቸው የነበሩ መልካም ስራዎች ይታሰቡለታል። ሐኪም ኢብኑ ሒዛም ረዲየላሁ ዐንሁ “በዘመነ ጃሂሊያ ስፈፅማቸው ስለነበሩት ዒባዳዎች፤ ሶደቃ፣ ባሪያ ነፃ ማውጣት፣ ዝምድናን መቀጠል በተመለከተ ንገረኝ እስኪ። ምንዳ ይኖራቸዋልን?” ብለው ነብዩን ﷺ ቢጠይቁ እንዲህ ብለው ነው የመለሱላቸዋል፡-
أَسْلَمْتَ عَلَى مَا أَسْلَفْتَ مِنْ خَيْرٍ
“ካሳለፍከው መልካም ስራ ጋር ነው የሰለምከው።” [ሶሒሕ ሙስሊም]
ልብ በል! ሐኪም ኢብኑ ሒዛም ከመካ መኳንንት የነበሩ ሲሆን በድር ላይ ከቁረይሾች ጋር ተሰለፈው ጦርነቱን ተካፍለዋል። አላህ ሲያድላቸው እንደ አጋሪ ጓደኞቻቸው በድር ላይ ሳይገደሉ በመትረፋቸው ኋላ ላይ ሰልመዋል። ለዚህም ነበር “የበድር ቀን ከመገደል ባተረፈኝ ጌታ ይሁንብኝ” እያሉ ይምሉ የነበሩት።
ወንድሜ ሆይ!
1. እስኪ የነ ዑመርንና ሌሎችም በጀነት የተመሰከረላቸውን ሶሐብዮች ታሪክ እናንብብ። ከነዚያ ታላላቅ የኢስላም ፈርጦች ውስጥ ቀድሞ ጣኦት አምላኪ የነበሩትኮ እጅግ በርካታ ናቸው።
2. እስኪ የነ ዐብደላህ ኢብኑ ሰላም፣ የነብያችን ﷺ ሚስት ሶፍያን ታሪክ እናገላብጥ። ከነዚያ እንቁ ሶሐብዮች ውስጥ ቀድሞ አይሁድ የነበሩት ብዙ ናቸው።
3. እስኪ የነ ሰልማኑል ፋሪሲ፣ ዐዲይ ኢብኑ ሓቲምና መሰል ሶሐቦችን ታሪክ እንፈትሽ። አዎ ከነዚያ ወደር የለሽ የኢስላም ጀግኖች ውስጥ ከመስለማቸው በፊት በክርስትና ውስጥ ያለፉ ነበሩ።
4. ከሶሐቦች ጊዜ ወዲህም ታሪክ የሰሩ፣ ለኢስላምና ለሙስሊሞች በዋጋ የማይተመን ውለታን የዋሉ በርካታ ሰለምቴዎች አልፈዋል።

ልብ በል ወንድሜ! ልብ በይ እህቴ! ኢስላም መለኮታዊ ሃይማኖት እንጂ የማንም ግላዊ ንብረት አይደለም። ኢስላም ለሰው፣ ለጂኑ ባጠቃላይ የቀረበ አምላካዊ መድህን እንጂ ያሰኘንን የምናስገባበት፤ የደበረንን የምናስወጣበት ያባታችን ግቢ አይደለም። ኢስላም ልክ ቄሶች “ውጉዝ ከመ አሪዮስ!” ብለው እንደሚያባርሩት ሸይኾችም እንዳሻቸው የሚፈርዱበት ቀልደኛ ቀኖና የለውም። ስለዚህ ወንድሜ! እስልምናን ከአባት ከአያት የወረስከው አንተ፣ በኢስላም ላይ ከሰለምቴው የተለየ የባለቤትነት መብት የለህም። ከአላህ ዘንድ ያለህ ደረጃ ከፍ የሚለው በተቅዋህ ብቻ ነው። ለሰለምቴው ኢስላምን የሰጠው የፈጠረው ጌታ እንጂ እኔ ወይም አንተ አይደለንም። እኛ ይህን የጌታ ፀጋ አከፋፋዮች አይደለንም።
ምናልባት “በሰለመ በማግስቱ ፈትዋ ካልሰጠሁ ብሎ የሚገላገል ሰለምቴስ ዝም ይባል ወይ?” የሚል ሊኖር ይችላል። ይሄ ሌላ ርእስ ነው። እያወራሁ ያለሁት ሰለምቴነትን ለማንቋሸሻነት ስለሚጠቀሙ አካላት ነው። የነሱን ስሜት ተከትሎ ስላልፈሰሰ ብቻ “እሱኮ ሰለምቴ ነው?” በማለት ለማንጓጠጥ መሞከር ምን ማለት ነው? እስኪ አስቡት! በሚያጋጥሙ አንዳንድ አለመግባባቶች የተነሳ “እሱኮ መስለሙንም እንጃ!”፣ “እሱኮ የሰለመ ጊዜ ቄሶች በደስታ እንኳን ሄደልን ያሉት ነው”፣ “እሱኮ እንደገና ወደ ክርስትና ሳይመለስ አይቀርም”፣ “እሱኮ ሶላት አይሰግድም"፣ "እሱኮ ውዱእ ሲያደርግ ታይቶ አይታወቅም"፣ "እሱኮ ይሰክራል …” ወዘተ በሚሉ እጅግ ሰቅጣጭና ፀያፍ ውንጀላዎች በሃሰት የሚወ፞ነጀል ሰለምቴ ምን እንደሚሰማው አስቡ እስኪ!! በተጨባጭ የተከሰቱ ሃሰተኛ ውንጀላዎችን ነው በምሳሌነት የጠቀስኩት። ተወንጃዮቹ ደካሞች ቢሆኑ ኖሮ በቀላሉ ወደ ኩፍር ተገፍተው ከኢስላም በሸሹ ነበር። ግና ኢስላም ማለት የነዚህ ዋልጌዎች የግል ንብረት እንዳልሆነ ጠንቅቀው ማወቃቸው በጃቸው። ግና ሰዎቹን ከማወቃቸው በፊት ኢስላምን ማወቃቸው ጠቀማቸው። እንጂ እንደዋዛ አኩርፈው በበረገጉ ነበር።
ወላሂ! አንድ ስንት ስራ የሰራ ወንድም ፈፅሞ ይዋሻሉ ብለን በማንገምታቸው ሰዎች በተደጋጋሚ በመወ፞ንጀሉ የተነሳ ብዙ ሰዎች እስልምናውን እስከሚጠራጠሩት የደረሱበት ሁኔታ በተጨባጭ አውቃለሁ። መነሻው ግን የእነዚያ ታማኞች የመሰሉን ሰዎች ክፋት ነበር።
በተረፈ ሰለምቴ ሆነው ስንቶችን ቁጭ አድርገው እየገሩ ያሉ ኡስታዞች አሉ?! ሰለምቴ ሆነው ለስንቶች መስለም ሰበብ የሆነ ስራ ላይ በሰፊው የዘመቱ አሉ?! ካረገዙ በኋላ በባሎቻቸው ተከድተው ብዙ ፈተና ቢደርስባቸውም ከነ ችግራቸው በኢስላማቸው ላይ እንደፀኑ ያሉ ስንት ሰለምቴዎች አሉ?! ወንድ ወይም ሴት ተከትለው ስንቶች በሚከፍሩበት ዘመን ለኢስላም ሲሉ ከቤተሰብ የተቆራረጡ፣ ትዳራቸውን የበተኑ ስንት ቆራጥ ሰለምቴዎች አሉ?! ነባር ሙስሊሞች በእርዳታ በቆሎ እምነታቸውን በሚቀይሩበት ምድር ለኢስላም ሲሉ ሁለ ነገራቸውን አጥተው ለእለት ጉርስ የተቸገሩ ስንት ፈተና ያልበገራቸው ሰለምቴዎች አሉ?!

ደግሞም አላዋቂ ሰለምቴ እውቀት በሚጠይቁ ጉዳዮች ላይ ያላቅሙ ገብቶ ካገኘን ብቃቱ ካለን በአደብ ማስተማር እንጂ ሰለምቴነቱን ለማሸማቀቂያ መጠቀም፣ ሰለምቴነቱን እንደ ነውር በመቁጠር በየደረሱበት ማማት የለየለት ብልግና ነው። መሀይም የሆነ ሰው ሰለምቴም ባይሆን ያላቅሙ እንዲያወራ የተሰጠው የተለየ ስልጣን ወይም መብት የለውም። ስለዚህ ሰለምቴው በተለየ የሚኮነንበት ምክንያት ምንድነው? ሰለምቴ ሆኖ ከብዙዎቻችን የተሻለ ግንዛቤ ያለው ስንት ሰው አለ? ከውልደት እስከ እርጅና እድሜውን ኢስላም ውስጥ አሳልፎ አሊፍ ትቁም ትጋደም የማያውቅ እልፍ አእላፍ ህዝብስ የለም ወይ? እውቀትኮ በመማር እንጂ በውልደት የሚገኝ አይደለም። “ሸንበቆ አስር አመት ውሃ ውስጥ ቢቆይ አዞ አይሆንም” ይባላል። ለውጥ ከአላህ እገዛ ጋር በጥረት እንጂ በምኞትም በጉራም አይገኝም።

(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥር 01/2012)


የተለያዩ ቂርአት ለማዳመጥ የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ
@Muhammedbatii


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Forward from: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
እስክንድር ነጋ፣ ቅልስልሱ እባብ
~~~~~~~~~~~~
እስክንድር ነጋ ሲበዛ ተንኮለኛ የሆነ ቅልስልስ እባብ እንደሆነ በሚገባ አውቃለሁ። ግን በዚህ ደረጃ ቅርሻቱን ባደባባይ የሚተፋ ደነዝ እንደሆነ አስቤው አላውቅም። የሞጣውን የመስጂዶችና የሙስሊሞች ንብረት ቃጠሎ ከመካከለኛው ምስራቅ ጋር ግንኙነት ባለው የተደራጀ የአሸባሪ ቡድን የተፈፀመ ሊሆን ይችላል እያለ ነው። ስለዚህ መስጂዱንና ንብረቱን ያቃጠለው እራሱ ሙስሊሙ ነው ማለት ነው።
እስክንድር በቅርቡ በአውሮፓ እና አሜሪካ በሄደበትም ይህንን ቡድን በሽብርተኝነት እንዲፈረጅ ለማድረግ ሲሰራ እንደነበር ተናግሯል። ማንን እየከሰሰ ተንኮል ሲሸርብ እንደነበር አያችሁ አይደል? ሙስሊሙ ላይ ስንት አይነት ቁማር እንደሚጫወቱ ተመልከቱ እንግዲህ። የመንግስት አካላት፣ የቤተ ክህነት ሰዎች፣ ማህበረ ቅዱሳን እና አደገኛ ቦዘኔዎች ተቀናጅተው ማቃጠላቸው አልበቃ ብሎ በቁስላችን በህመማችን ላይ ሌላ ዙር ጥቃት ከፍተውብናል።
ያገር ውስጡ አልበቃ ብሎ በምእራብ ሃገራት እየተሽሎከለኩ የሚያሴሩብን ሌላ ረጅም ሴራ እንዳለ እየነገሩን ነው። በነገራችን ላይ በነ መለስ ጊዜም የተፈፀመብንም ይሄው ነው። በ1997ቱ ምርጫ "ኢህአዴግ ለሙስሊሞች በሚሰራው ‘ፌቨር’ የተነሳ በ20 አመት ጊዜ ኢስላም በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ነው። አክራሪ እስልምና እና አሸባሪነት በከፍተኛ ፍጥነት እግሩን እየተከለ ነው" እያሉ ምእራባውያን ዘንድ መንግስትን ከከሰሱ በኋላ ነው ኢህአዴግ የምእራባውያኑን ድጋፍ ለማግኘት ሲል በሙስሊሙ ላይ ከወትሮው የተለየ ቀጥተኛ ዘመቻ የከፈተው።
ዛሬም እነ እስክንድር እያደረጉት ያለው ይህንኑ ነው። የመንግስት አብዛኛው አካሄድ ወደነሱ ያዘነበለ ከመሆኑም ጋር ሙስሊሙ ላይ እየደረሰ ያለው መከራ እነሱ በሚፈልጉት መጠን ስላልሆነ ሰፊና የተቀናጀ ስራ እየሰሩ እንደሆነ ፍንጭ እየሰጡን ነው። እውነት ለመናገር እኛ ከነሱ ቅንነት አንጠብቅም። ለኢስላምና ለሙስሊሞች አንዱ ከሌላው ያላቸው ርቀት እምብዛም ነው። በዚህ ረገድ "የአንድነት ሃይሉ" ከፅንፈኛ ብሄርተኛው አይለይም። በሁለት እግሩ ተደላድሎ እስኪቆም ድረስ እንጂ በሙስሊሞች ጉዳይ ላይ በመንግስትና በተቃዋሚ መካከል ያለው ርቀትም ብዙ አይደለም። ስለዚህ የኛ ጉዳይ የኛ ብቻ ነው። የረጅምና የአጭር ጊዜ እቅዶችን ነድፈን መንቀሳቀስ ያለብን እኛው ነን። የኛን ስራ ሌላ አካል እንዲፈፅምልን መጠበቅ የዋህነት ነው። ሁሉም በየፊናው ሊንቀሳቀስ ይገባል። ደግሞም እንችላለን ኢንሻአላህ። ዲናችንን ከነዚህ እባቦች ለመከላከል እንዲሁም ሕዝባችንን ከነዚህ ተኩላዎች ለማትረፍ ወገናችንን በዲኑም በዱንያውም ለማንቃት መታገል ያስፈልጋል።


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Sefina 6


Sefina 5


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Video is unavailable for watching
Show in Telegram

20 last posts shown.

1 831

subscribers
Channel statistics