በረመዳን ምን ይጠበቅብናል?
ክፍል ❹
ከአላህ ጋር…
ረመዳን እያንዳንዱ ሙስሊም ልቡን ህያው የሚያደርግባቸው እና ከጌታው ጋር ያለውን አብሮነትና ግንኙነት የሚያዳብርባቸው ብዙ አማካዮችን (ወሳኢል/means) ይፈጥራል። ከእነዚህ ጥቂቶቹን እነሆ፡-
1. ፆም
ይህ ነፍስን ለመቆጣጠር የሚረዳ ምርጥ መንገድ ነው። እንዲህ የምንለው ለምን መሰላችሁ? ነፍስ የአላህን ባሮች ከአላህ መንገድ የምታሰናክል ክፉ ነገር ናት።
ተፈጥሮዋ ደስታን እንድትፈልግና ከግዴታዎቿ እንድትሸሽ ያደርጋታል። እርሷን የሚያርቅ (የሚያርም) ምርጥ መንገድ ደግሞ ፆም ነው።
እርሱ የስሜቷን በር የሚያጣብብ ነገር አለው። ስለዚህ በፆማችን ይህን መጠቀም ከፈለግን የቀኑን አብዝሀ-ክፍል በእንቅልፍ ማሳለፍ የለብንም።
ኢፍጣር ላይ ምግብና መጠጥ ስንጠቀምም መሀከለኛ መሆን አለብን። የምግብ አይነቶችን ማብዛት የለብንም። አንድ አይነት ምግብ በቂያችን ነው።
አል-ሐሊሚይ እንዲህ ይላሉ፡-
“…ሐላል የሆኑ ምግቦችን ማብዛት ጥሩ አይደለም። ምናልባት ሰውነቱን ያከብደውና እንቅልፍ እንቅልፍ ያሰኘዋል።
ከዒባዳና ከዚክር ያግደዋል። ስለዚህ ረሐቡን የሚቆርጥበት ያህል ከተበላ በቂ ነው። ምግብ የሚበላበት አላማም በዒባዳ ለመጠንከር ይሁን።”
ከምግብና መጠጥ ከመፆም ጋር በቻልነው ያህል ከክፉ ንግግሮችና ሳቅ ራሳችንን ማፆም ይገባናል።
“ምላስህን ያዝ!” ይሁን ለራሳችን የምናነሳው መፈክር። ከአልባሌ ጨዋታዎችና ከሌሎችም የምላስ ጣጣዎች እራሳችንን እንጠብቅ።
2. ከመስጊድ ጋር ያለንን ግንኙነት ማጠናከር
መስጊድ ልብን የሚያበራ ታላቅ ሚና አለው። አላህ እንዲህ ይላል፡-
اللَّهُ نُورُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ
“አላህ የሰማያትና የምድር አብሪ ነው።” (አን-ኑር 24፤ 35)
ከዚያም ቀጥሎ ያለውን አንቀፅ ደግሞ እንመልከት።
فِي بُيُوتٍ أَذِنَ اللَّهُ أَن تُرْفَعَ وَيُذْكَرَ فِيهَا اسْمُهُ يُسَبِّحُ لَهُ فِيهَا بِالْغُدُوِّ وَالْآصَالِ
“አላህ እንድትከበርና ስሙ በውስጧ እንዲወሳ ባዘዘው ቤቶች ውስጥ (አወድሱት)። በውስጧ በጧትና በማታ ለእርሱ ያጠራሉ።” (አን-ኑር 24፤ 36)
የእነዚህ ሁለት አንቀፆች ትርጉም እንዲህ ሊለን ፈልጓል።
መስጊድ ውስጥ ልብህ ከአላህ ጋር ይተሳሰራል። ነፍስህም ከኃጢያት ይጠበቃል።
ألا أدلكم على ما يمحو الله به الخطايا ويرفع به الدرجات، قالوا بلى يا رسول الله، قال: إسباغ الوضوء على المكارة وكثرة الخطى إلى المساجد وانتظار الصلاة بعد الصلاة، فذلكم الرباط فذلكم الرباط
“አላህ ኃጢያት የሚምርበት ደረጃ ከፍ የሚያደርግበትን ነገር አልነግራችሁም?!” አሉ የአላህ መልእክተኛ። “አዎን! የአላህ መልእክተኛ ሆይ!” አሉ፤ ባልደረቦቻቸው።
“ቅዝቃዜ በሚኖር ጊዜ ዉዱእ አዳርሶ ማድረግ፣ ወደ መስጊድ እርምጃ ማብዛትና ከሶላት በኋላ ሶላትን መጠበቅ። ይኻችሁ ነው ዒባዳን በዒባዳ ላይ ማነባበር (ሪባጥ) ማለት።”
የሙእሚን ቀልብ ከአንድ ሁኔታ ወደሌላ ይገላበጣል። ውስጡ የሚደረጉ የኢማንና የስሜት ጥሪዎች መሀል የሚደረግ ጦርነት አለ።
በኢማን ጥላ ስር እንዲቆይ ማድረግና ማረጋጋት ይገባል። ይህን ጊዜ የመስጊድ ሚና ጎልቶ ይታያል። ሰይዲና አባሁረይራህ (ረ.ዐ) ተከታዩን አንቀፅ ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ፡-
يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اصْبِرُوا وَصَابِرُوا وَرَابِطُوا وَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ
“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ታገሱ ተበራቱም (በጦር ሜዳ ኬላ ላይ) ተሰለፉም ትድኑም ዘንድ አላህን ፍሩ።” (አሊ ዒምራን 3፤ 200)
“በነብዩ ዘመን ሪባጥ (በጦር ሜዳ ኬላ ላይ የሚደረግ ሰልፍ) የሚደረግበት ዘመቻ አልነበረም።
ይህ አንቀፅ ለመንገር የፈለገው ዋና ነጥብ ከሶላት በኋላ ሶላት መጠበቅን ነው።”
መስጊድ በጧት እንግባ። ከሰገድን በኋላም ቦታችንን አንተውም። ምክንያቱም መላኢካዎች ዱዐ ያደርጉልናል።
በሃዲስ እንደተዘገበው“እያንዳንዳችሁ በሰገዳችሁበት ስፍራ ከተቀመጠ ዉዱእ እስካልፈታ ድረስ ‘አላህ ሆይ! ማረው። አላህ ሆይ! እዘንለት እያሉ’ መላኢካዎች ዱዓ ያደርጉለታል።”
ይህ ቱሩፋት አብዝሀኛው ሰላቷን ቤቷ ውስጥ የምትሰግድ እህታችን አታጣውም። ቤቷ ውስጥ አንዲት ስፍራ መስጊድ ብላ ብትወስን፣ ወደዚያው ስፍራ በጊዜ ብትሄድ፣ ከሶላት በኋላም ሶላት ብትጠብቅ፣ እዚያው ሶላቱን ብትደጋግምበትና የችሎታዋን ያህል እዚያው ብትቀመጥ ታገኘዋለች።
3. ቁርአን ህይወት ነው
ረመዳን የቁርአን ወር ነው። የነብዩ ተግባር የሚጠቁመው ረመዳን ውስጥ ቁርአንን አብዝቶ ማጥናት አስፈላጊ መሆኑን ነው። ቁርአን ልብን ህያው ለማድረግ ፍቱን መድሀኒት ነው፤ መንፈስን በብርሀን ለማሸብረቅ መልካም መንገድ ነው።
يَا أَيُّهَا النَّاسُ قَدْ جَاءَتْكُم مَّوْعِظَةٌ مِّن رَّبِّكُمْ وَشِفَاءٌ لِّمَا فِي الصُّدُورِ وَهُدًى وَرَحْمَةٌ لِّلْمُؤْمِنِينَ
“እናንተ ሰዎች ሆይ! ከጌታችሁ ግሳጼ በደረቶች ውስጥም ላለው (የመጠራጠር በሽታ) መድኃኒት ለምእምናንም ብርሃንና እዝነት በእርግጥ መጣችላችሁ።” (ዩኑስ 10፤ 57)
ሙስሊም ለቁርአን ባለው ቅርበት ያህል ለአላህ ይቀርባል። የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ይላሉ፡-
أبشروا!! فإن هذا القرآن طرفه بيد الله وطرفه بأيديكم فتمسكوا به فإنكم لن تهلكوا ولن تضلوا بعده أبداً
“አይዟችሁ! ይህ ቁርአን ጫፉ በአላህ እጅ ነው። ጫፉ ደግሞ እናንተ እጅ ላይ ነው። ከርሱ በኋላ አትጠፉም። አትጠሙምም።”
ይህ መድኃኒት ፍቱን የሚሆነው እና የልባችንን ህመም የሚፈውስልን አላህ እንደሚፈልገው ስንጠቀምበት ነው። ቁርአን የወረደው እንድናስተነትነው ነው።
ከውስጡም ለህይወታችን የሚበጁ ትምህርቶችን እንድንቀስም ታዘናል። በምላሳችን እንድናነበው ብቻ አይደለም ወደኛ የመጣው። አላህ እንዲህ ብሏል፡-
كِتَابٌ أَنزَلْنَاهُ إِلَيْكَ مُبَارَكٌ لِّيَدَّبَّرُوا آيَاتِهِ وَلِيَتَذَكَّرَ أُولُو الْأَلْبَابِ
“(ይህ) ወዳንተ ያወረድነው ብሩክ መጽሐፍ ነው። አንቀጾቹን እንዲያስተነትኑና የአእምሮዎች ባለቤቶችም እንዲገሰጹ (አወረድነው)።” (ሷድ 38፤ 29)
አንዳንድ ደጋግ ሰዎች እንዲህ አሉ፡-
ማንም ሠው ከቁርአን ጋር ተቀምጦ ሳያተርፍ ወይም ሳይከስር አይነሳም። አላህ እንዲህ ብሏል፡-
🔂 ሼር 🔂 ሼር 🔂 ሼር 🔂
🍀 ዲነል ኢስላም Tube
🔑"ለመልካም ነገር ቁልፍ ሁን!!"
http://t.me/Dinel_Islam_Tube http://t.me/Dinel_Islam_Tube
ክፍል ❹
ከአላህ ጋር…
ረመዳን እያንዳንዱ ሙስሊም ልቡን ህያው የሚያደርግባቸው እና ከጌታው ጋር ያለውን አብሮነትና ግንኙነት የሚያዳብርባቸው ብዙ አማካዮችን (ወሳኢል/means) ይፈጥራል። ከእነዚህ ጥቂቶቹን እነሆ፡-
1. ፆም
ይህ ነፍስን ለመቆጣጠር የሚረዳ ምርጥ መንገድ ነው። እንዲህ የምንለው ለምን መሰላችሁ? ነፍስ የአላህን ባሮች ከአላህ መንገድ የምታሰናክል ክፉ ነገር ናት።
ተፈጥሮዋ ደስታን እንድትፈልግና ከግዴታዎቿ እንድትሸሽ ያደርጋታል። እርሷን የሚያርቅ (የሚያርም) ምርጥ መንገድ ደግሞ ፆም ነው።
እርሱ የስሜቷን በር የሚያጣብብ ነገር አለው። ስለዚህ በፆማችን ይህን መጠቀም ከፈለግን የቀኑን አብዝሀ-ክፍል በእንቅልፍ ማሳለፍ የለብንም።
ኢፍጣር ላይ ምግብና መጠጥ ስንጠቀምም መሀከለኛ መሆን አለብን። የምግብ አይነቶችን ማብዛት የለብንም። አንድ አይነት ምግብ በቂያችን ነው።
አል-ሐሊሚይ እንዲህ ይላሉ፡-
“…ሐላል የሆኑ ምግቦችን ማብዛት ጥሩ አይደለም። ምናልባት ሰውነቱን ያከብደውና እንቅልፍ እንቅልፍ ያሰኘዋል።
ከዒባዳና ከዚክር ያግደዋል። ስለዚህ ረሐቡን የሚቆርጥበት ያህል ከተበላ በቂ ነው። ምግብ የሚበላበት አላማም በዒባዳ ለመጠንከር ይሁን።”
ከምግብና መጠጥ ከመፆም ጋር በቻልነው ያህል ከክፉ ንግግሮችና ሳቅ ራሳችንን ማፆም ይገባናል።
“ምላስህን ያዝ!” ይሁን ለራሳችን የምናነሳው መፈክር። ከአልባሌ ጨዋታዎችና ከሌሎችም የምላስ ጣጣዎች እራሳችንን እንጠብቅ።
2. ከመስጊድ ጋር ያለንን ግንኙነት ማጠናከር
መስጊድ ልብን የሚያበራ ታላቅ ሚና አለው። አላህ እንዲህ ይላል፡-
اللَّهُ نُورُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ
“አላህ የሰማያትና የምድር አብሪ ነው።” (አን-ኑር 24፤ 35)
ከዚያም ቀጥሎ ያለውን አንቀፅ ደግሞ እንመልከት።
فِي بُيُوتٍ أَذِنَ اللَّهُ أَن تُرْفَعَ وَيُذْكَرَ فِيهَا اسْمُهُ يُسَبِّحُ لَهُ فِيهَا بِالْغُدُوِّ وَالْآصَالِ
“አላህ እንድትከበርና ስሙ በውስጧ እንዲወሳ ባዘዘው ቤቶች ውስጥ (አወድሱት)። በውስጧ በጧትና በማታ ለእርሱ ያጠራሉ።” (አን-ኑር 24፤ 36)
የእነዚህ ሁለት አንቀፆች ትርጉም እንዲህ ሊለን ፈልጓል።
መስጊድ ውስጥ ልብህ ከአላህ ጋር ይተሳሰራል። ነፍስህም ከኃጢያት ይጠበቃል።
ألا أدلكم على ما يمحو الله به الخطايا ويرفع به الدرجات، قالوا بلى يا رسول الله، قال: إسباغ الوضوء على المكارة وكثرة الخطى إلى المساجد وانتظار الصلاة بعد الصلاة، فذلكم الرباط فذلكم الرباط
“አላህ ኃጢያት የሚምርበት ደረጃ ከፍ የሚያደርግበትን ነገር አልነግራችሁም?!” አሉ የአላህ መልእክተኛ። “አዎን! የአላህ መልእክተኛ ሆይ!” አሉ፤ ባልደረቦቻቸው።
“ቅዝቃዜ በሚኖር ጊዜ ዉዱእ አዳርሶ ማድረግ፣ ወደ መስጊድ እርምጃ ማብዛትና ከሶላት በኋላ ሶላትን መጠበቅ። ይኻችሁ ነው ዒባዳን በዒባዳ ላይ ማነባበር (ሪባጥ) ማለት።”
የሙእሚን ቀልብ ከአንድ ሁኔታ ወደሌላ ይገላበጣል። ውስጡ የሚደረጉ የኢማንና የስሜት ጥሪዎች መሀል የሚደረግ ጦርነት አለ።
በኢማን ጥላ ስር እንዲቆይ ማድረግና ማረጋጋት ይገባል። ይህን ጊዜ የመስጊድ ሚና ጎልቶ ይታያል። ሰይዲና አባሁረይራህ (ረ.ዐ) ተከታዩን አንቀፅ ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ፡-
يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اصْبِرُوا وَصَابِرُوا وَرَابِطُوا وَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ
“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ታገሱ ተበራቱም (በጦር ሜዳ ኬላ ላይ) ተሰለፉም ትድኑም ዘንድ አላህን ፍሩ።” (አሊ ዒምራን 3፤ 200)
“በነብዩ ዘመን ሪባጥ (በጦር ሜዳ ኬላ ላይ የሚደረግ ሰልፍ) የሚደረግበት ዘመቻ አልነበረም።
ይህ አንቀፅ ለመንገር የፈለገው ዋና ነጥብ ከሶላት በኋላ ሶላት መጠበቅን ነው።”
መስጊድ በጧት እንግባ። ከሰገድን በኋላም ቦታችንን አንተውም። ምክንያቱም መላኢካዎች ዱዐ ያደርጉልናል።
በሃዲስ እንደተዘገበው“እያንዳንዳችሁ በሰገዳችሁበት ስፍራ ከተቀመጠ ዉዱእ እስካልፈታ ድረስ ‘አላህ ሆይ! ማረው። አላህ ሆይ! እዘንለት እያሉ’ መላኢካዎች ዱዓ ያደርጉለታል።”
ይህ ቱሩፋት አብዝሀኛው ሰላቷን ቤቷ ውስጥ የምትሰግድ እህታችን አታጣውም። ቤቷ ውስጥ አንዲት ስፍራ መስጊድ ብላ ብትወስን፣ ወደዚያው ስፍራ በጊዜ ብትሄድ፣ ከሶላት በኋላም ሶላት ብትጠብቅ፣ እዚያው ሶላቱን ብትደጋግምበትና የችሎታዋን ያህል እዚያው ብትቀመጥ ታገኘዋለች።
3. ቁርአን ህይወት ነው
ረመዳን የቁርአን ወር ነው። የነብዩ ተግባር የሚጠቁመው ረመዳን ውስጥ ቁርአንን አብዝቶ ማጥናት አስፈላጊ መሆኑን ነው። ቁርአን ልብን ህያው ለማድረግ ፍቱን መድሀኒት ነው፤ መንፈስን በብርሀን ለማሸብረቅ መልካም መንገድ ነው።
يَا أَيُّهَا النَّاسُ قَدْ جَاءَتْكُم مَّوْعِظَةٌ مِّن رَّبِّكُمْ وَشِفَاءٌ لِّمَا فِي الصُّدُورِ وَهُدًى وَرَحْمَةٌ لِّلْمُؤْمِنِينَ
“እናንተ ሰዎች ሆይ! ከጌታችሁ ግሳጼ በደረቶች ውስጥም ላለው (የመጠራጠር በሽታ) መድኃኒት ለምእምናንም ብርሃንና እዝነት በእርግጥ መጣችላችሁ።” (ዩኑስ 10፤ 57)
ሙስሊም ለቁርአን ባለው ቅርበት ያህል ለአላህ ይቀርባል። የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ይላሉ፡-
أبشروا!! فإن هذا القرآن طرفه بيد الله وطرفه بأيديكم فتمسكوا به فإنكم لن تهلكوا ولن تضلوا بعده أبداً
“አይዟችሁ! ይህ ቁርአን ጫፉ በአላህ እጅ ነው። ጫፉ ደግሞ እናንተ እጅ ላይ ነው። ከርሱ በኋላ አትጠፉም። አትጠሙምም።”
ይህ መድኃኒት ፍቱን የሚሆነው እና የልባችንን ህመም የሚፈውስልን አላህ እንደሚፈልገው ስንጠቀምበት ነው። ቁርአን የወረደው እንድናስተነትነው ነው።
ከውስጡም ለህይወታችን የሚበጁ ትምህርቶችን እንድንቀስም ታዘናል። በምላሳችን እንድናነበው ብቻ አይደለም ወደኛ የመጣው። አላህ እንዲህ ብሏል፡-
كِتَابٌ أَنزَلْنَاهُ إِلَيْكَ مُبَارَكٌ لِّيَدَّبَّرُوا آيَاتِهِ وَلِيَتَذَكَّرَ أُولُو الْأَلْبَابِ
“(ይህ) ወዳንተ ያወረድነው ብሩክ መጽሐፍ ነው። አንቀጾቹን እንዲያስተነትኑና የአእምሮዎች ባለቤቶችም እንዲገሰጹ (አወረድነው)።” (ሷድ 38፤ 29)
አንዳንድ ደጋግ ሰዎች እንዲህ አሉ፡-
ማንም ሠው ከቁርአን ጋር ተቀምጦ ሳያተርፍ ወይም ሳይከስር አይነሳም። አላህ እንዲህ ብሏል፡-
🔂 ሼር 🔂 ሼር 🔂 ሼር 🔂
🍀 ዲነል ኢስላም Tube
🔑"ለመልካም ነገር ቁልፍ ሁን!!"
http://t.me/Dinel_Islam_Tube http://t.me/Dinel_Islam_Tube