በረመዳን ምን ይጠበቅብናል?
ክፍል ❶❶
የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡-
ما من ذنب أجدر أن يعجل الله تعالى لصاحبه بالعقوبة في الدنيا مع ما يدخره له في الآخرة من قطيعة الرحم، والخيانة والكذب، وإن أعجل الطاعة ثواب لصلة الرحم، حتى إن أهل البيت ليكونوا فجرة فتنموا أموالهم، ويكثر عددهم إذا تواصلوا
“ዝምድናን እንደመቁረጥ፣ እንደ ክዳትና ውሸት አኼራ ላይ ከሚከማች ቅጣት በተጨማሪ ዱንያ ውስጥ ቅጣት የሚያቻኩል ምንም አይነት ኃጢያት የለም።
ዝምድናን እንደመቀጠል በፍጥነት ምንዳው የሚሠጥበት በጎ ሥራ የለም። የመፍጠኑም ማሳያ ጠማሞች ቢሆኑም እንኳን የዝምድና ቀጣዩ ቤተሰቦች ገንዘብ ሲበረክት ልናይ እንችላለን። ዝምድናቸውን በቀጠሉ ቁጥር ቁጥራቸው ሲበዛም እናያለን።”
የረመዳንን መግባት ዘመዶቻችንን ለመዘየር መልካም አጋጣሚ እናድርገው። ምናልባት የማያዘያይር ችግር ከገጠመን ስልክ እና መሠል የመገናኛ መንገዶችን በመጠቀም ከዚህ በጎ ሥራ ተጠቃሚ እንሁን።
بلوا أرحامكم ولو بالسلام
“…በሰላምታም ቢሆን ዝምድናችሁን ቀጥሉ።”ብለዋል የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ)።
ማንም ሰው ያለፈን ጥል እና ቅያሜ ላለመጠያየቂያ ሰበብ ሊያደርገው አይችልም።
አንድ ሠው ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ.) መጣና “እኔ ዘመዶች አሉኝ። እቀጥላቸዋለሁ ይቆርጡኛል። መልካም እውልላቸዋለሁ፤ እነርሱ ያስከፉኛል። እኔ ስችላቸው እነርሱ ድንበር ያልፉብኛል።” አለ። መልእክተኛውም (ሰ.ዐ.ወ.) እንዲህ አሉ፡-
لئن كان كما تقول فكأنما تسفهم الملل ولا يزال معك من الله ظهير عليهم ما دمت علي ذلك
“እንደምትለው ከሆንክ ልክ ረመጥ እንደምታቅማቸው ነው። በዚህ ሁኔታ እስካለህ ድረስ ላንተ ከአላህ በኩል ጠባቂ ከመኖር አይወገድም።”
4.ምግብ ማብላት
ይህ ትልቅ የበጎ ተግባር ደጃፍ ነው። ነገር ግን ብዙዎች ችላ ብለውታል።
إن من الجنة غرفا يري ظاهرها من باطنها، وباطنها من ظاهرها قالوا: لمن هي يا رسول الله؟ قال: لمن أطعم الطعام وأطاب الكلام، وصلى بالليل والناس نيام
“ጀነት ውስጥ ሰገነቶች አሉ። የውጭው ክፍል ከውስጥ ይታያል። የውስጡን ደግሞ ከውጭ በኩል ማየት ይቻላል።”
አሉ፤ የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.)። የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ለማን የተዘጋጁ ናቸው? ብለው ጠየቁ፤ ሶሐቦቹ። “ምግብ ላበላ፤ ንግግርን ላሳመረ፤ ሰዎች ተኝተው ሳሉ በለሊት ለሰገደ።”
ሱሀይብ (ረ.ዐ.) ብዙ ምግብ ያበላ ነበር።
ከዚያም ዑመር (ረ.ዐ.) “ሱሀይብ ሆይ! አንተ ብዙ ምግብ ታበላለህ። ይህ ደግሞ ገንዘብን ማባከን ነው።” አሉት። እርሱም “የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) ከእናንተ መሀል ምርጣችሁ ምግብ ያበላና ሰላምታን የመለሰ ነው። ብለውኛል። እኔንም ብዙ እንዳበላ ያደረገኝ ይህ ነው።” አለ።
ዐሊይ ኢብኑ አቢጣሊብ (ረ.ዐ.) እንዲህ ይሉ ነበር። “ወደ ሱቅ ወጥቼ አንዲት ባርያ ገዝቼ ነፃ ከማደርግ ጓደኞቼን ሰብስቤ አንዲት ቁና ምግብ ባበላ እመርጣለሁ።”
በመሀላችን ያለውን ትስስርና ፍቅር ለማጠንከር ጓደኞቻችንን፣ ወዳጆቻችንን፣ ወንድሞቻችንን እና ጎረቤቶቻችንን ሰብስበን ብንጋብዝ መልካም አየር እንፈጥራለን። ከዚሁ ጋር ምስኪኖችን ማብላት ደግሞ ልዩ ጥቅም አለው።
ልቡ በመድረቁ እየተጎዳ መሆኑን የመሰሞተን አንድ ሰው የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) እንዲህ ሲሉ መክረውታል።
إن أحببت أن يلين قلبك فأطعم المسكين وأمسح رأس اليتيم
“ልብህ እንዲለሰልስ ከፈለክ ሚስኪኖችን መግብ። የየቲምን ራስ አብስ።”
ለድሆችና ለሚስኪኖች የማፍጠሪያ ግብዣዎችን እናዘጋጅ።
ከነርሱም ጋር አብረን በመቀመጥ ምግባቸውን ብንቋደስ እና የወንድምነትና የእህትነት ስሜታቸውን ለማሳደግ ብንሞክር ልብ ላይ የሚፈጥረው የኢማን ስሜት ልዩ ነው።
ከዚህም ጋር ችግር ያለባቸውን፣ በበደል ስር የሚኖሩ፣ ነእስር የሚማቅቁት፣ በመሳደድ ላይ የሚገኙና በረሀብ አረንቋ እየተንገላቱ የሚገኙ ህዝቦችን እናስብ።
من فطر صائما كان له مثل أجره غير أنه لا ينقص من أجر الصائم شيئا
“ፆመኛን ያስፈጠረ ሰው የፆመኛው ምንዳ ሳይቀንስ ለርሱም የፆመኛው አምሳያ ምንዳ።”የሚለውን የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ.) ብስራት እንዳንረሳ።
5.ሠዎችን ማስታረቅ
ብዙ ጊዜ ሠዎች የሚቀያየሙባቸውን ነገሮች ብንመለከት ተራ ጉዳዮች እንደሆኑ እንታዘባለን። ነገር ግን ሰይጣን በመሀል ገብቶ ያቀጣጥለዋል።
ከዚያም አባትና ልጅን ያቆራርጣል። ጎረቤትን ከጎረቤት ጋር ያቃቅራል። ወዳጅን ከወዳጁ ያጣላል። በዚህ በተመረዘ አየር ላይ ጥርጣሬዎች ይበዛሉ። ዝምድናዎችም ይቆረጣሉ። ጠላትነትም ይዋረሳል። ስለዚህ ሠዎችን ለማስታረቅ መጣር ታላቅ ምንዳ አለው።
ብዙ ጊዜ ሠዎች የሚቀያየሙባቸውን ነገሮች ብንመለከት ተራ ጉዳዮች እንደሆኑ እንታዘባለን። ነገር ግን ሰይጣን በመሀል ገብቶ ያቀጣጥለዋል። ከዚያም አባትና ልጅን ያቆራርጣል። ጎረቤትን ከጎረቤት ጋር ያቃቅራል። ወዳጅን ከወዳጁ ያጣላል።
በዚህ በተመረዘ አየር ላይ ጥርጣሬዎች ይበዛሉ። ዝምድናዎችም ይቆረጣሉ። ጠላትነትም ይዋረሳል። ስለዚህ ሠዎችን ለማስታረቅ መጣር ታላቅ ምንዳ አለው።
لَّا خَيْرَ فِي كَثِيرٍ مِّن نَّجْوَاهُمْ إِلَّا مَنْ أَمَرَ بِصَدَقَةٍ أَوْ مَعْرُوفٍ أَوْ إِصْلَاحٍ بَيْنَ النَّاسِ ۚ وَمَن يَفْعَلْ ذَٰلِكَ ابْتِغَاءَ مَرْضَاتِ اللَّهِ فَسَوْفَ نُؤْتِيهِ أَجْرًا عَظِيمًا
“ከውይይታቸው በምጽዋት ወይም በበጎ ሥራ ወይም በሰዎች መካከል በማስታረቅ ከሚያዙ ሰዎች ውይይት በስተቀር በብዙው ውስጥ ደግ ነገር የለበትም። ይኸንንም (የተባለውን) የአላህን ውዴታ ለመፈለግ የሚሠራ ሰው ታላቅ ምንዳን እንሰጠዋለን።” (አን-ኒሳእ 4፤ 114)
የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) በዚህ መልካም ሥራ ውስጥ የሚሳተፍን ሠው ከፆመኞች፣ ከሠጋጆችና ከመፅዋቾች የላቀ ደረጃ እንዳለው ቃል ገብተዋል። ምክንያቱም ይህ ተግባር በማህበረሰብ መሀል እርቅን ማስፋፋት፣ እዝነትና ፍቅርን ማጎልበት ነው። መልእክተኛው (ሰ.ዐ.ወ)
ألا أخبركم بأفضل من درجة الصيام والصلاة والصدقة؟ قالوا: بلي، قال: صلاح ذات البين فإن فساد ذات البين هي الحالقة
“ከፆም ከሶላት እና ከሶደቃ ደረጃ በላይ የሆነን ነገር አልነግራችሁም!?” አሉ። “አዎን! ንገሩን” አሉ፤ ባልደረቦቻቸው። “ሰዎችን ማስታረቅ ነው። በሰዎች መሀል ያለ ግንኙነት መበላሸት (ዲንን) ይላጫል።”የተጣሉ ሠዎችን ይህን የአላህ አንቀፅ እናስታውሳቸው።
وَالصُّلْحُ خَيْرٌ
“መታረቅም መልካም ነው።” (አን-ኒሳእ 4፤ 128)
ከነፍሳችን እንጀምር። የበደለንን ይቅር እንበል። ላስከፋን በጎ እንዋል። ለሌሎች ወገኖች የመቻል፣ የትእግስት፣ የእዝነት እና የሰፊ ልብ ምሳሌ እንሁን።
.........ይቀጥላል
🔂 ሼር 🔂 ሼር 🔂 ሼር 🔂
🍀 ዲነል ኢስላም Tube
🔑"ለመልካም ነገር ቁልፍ ሁን!!"
http://t.me/Dinel_Islam_Tube http:
ክፍል ❶❶
የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡-
ما من ذنب أجدر أن يعجل الله تعالى لصاحبه بالعقوبة في الدنيا مع ما يدخره له في الآخرة من قطيعة الرحم، والخيانة والكذب، وإن أعجل الطاعة ثواب لصلة الرحم، حتى إن أهل البيت ليكونوا فجرة فتنموا أموالهم، ويكثر عددهم إذا تواصلوا
“ዝምድናን እንደመቁረጥ፣ እንደ ክዳትና ውሸት አኼራ ላይ ከሚከማች ቅጣት በተጨማሪ ዱንያ ውስጥ ቅጣት የሚያቻኩል ምንም አይነት ኃጢያት የለም።
ዝምድናን እንደመቀጠል በፍጥነት ምንዳው የሚሠጥበት በጎ ሥራ የለም። የመፍጠኑም ማሳያ ጠማሞች ቢሆኑም እንኳን የዝምድና ቀጣዩ ቤተሰቦች ገንዘብ ሲበረክት ልናይ እንችላለን። ዝምድናቸውን በቀጠሉ ቁጥር ቁጥራቸው ሲበዛም እናያለን።”
የረመዳንን መግባት ዘመዶቻችንን ለመዘየር መልካም አጋጣሚ እናድርገው። ምናልባት የማያዘያይር ችግር ከገጠመን ስልክ እና መሠል የመገናኛ መንገዶችን በመጠቀም ከዚህ በጎ ሥራ ተጠቃሚ እንሁን።
بلوا أرحامكم ولو بالسلام
“…በሰላምታም ቢሆን ዝምድናችሁን ቀጥሉ።”ብለዋል የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ)።
ማንም ሰው ያለፈን ጥል እና ቅያሜ ላለመጠያየቂያ ሰበብ ሊያደርገው አይችልም።
አንድ ሠው ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ.) መጣና “እኔ ዘመዶች አሉኝ። እቀጥላቸዋለሁ ይቆርጡኛል። መልካም እውልላቸዋለሁ፤ እነርሱ ያስከፉኛል። እኔ ስችላቸው እነርሱ ድንበር ያልፉብኛል።” አለ። መልእክተኛውም (ሰ.ዐ.ወ.) እንዲህ አሉ፡-
لئن كان كما تقول فكأنما تسفهم الملل ولا يزال معك من الله ظهير عليهم ما دمت علي ذلك
“እንደምትለው ከሆንክ ልክ ረመጥ እንደምታቅማቸው ነው። በዚህ ሁኔታ እስካለህ ድረስ ላንተ ከአላህ በኩል ጠባቂ ከመኖር አይወገድም።”
4.ምግብ ማብላት
ይህ ትልቅ የበጎ ተግባር ደጃፍ ነው። ነገር ግን ብዙዎች ችላ ብለውታል።
إن من الجنة غرفا يري ظاهرها من باطنها، وباطنها من ظاهرها قالوا: لمن هي يا رسول الله؟ قال: لمن أطعم الطعام وأطاب الكلام، وصلى بالليل والناس نيام
“ጀነት ውስጥ ሰገነቶች አሉ። የውጭው ክፍል ከውስጥ ይታያል። የውስጡን ደግሞ ከውጭ በኩል ማየት ይቻላል።”
አሉ፤ የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.)። የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ለማን የተዘጋጁ ናቸው? ብለው ጠየቁ፤ ሶሐቦቹ። “ምግብ ላበላ፤ ንግግርን ላሳመረ፤ ሰዎች ተኝተው ሳሉ በለሊት ለሰገደ።”
ሱሀይብ (ረ.ዐ.) ብዙ ምግብ ያበላ ነበር።
ከዚያም ዑመር (ረ.ዐ.) “ሱሀይብ ሆይ! አንተ ብዙ ምግብ ታበላለህ። ይህ ደግሞ ገንዘብን ማባከን ነው።” አሉት። እርሱም “የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) ከእናንተ መሀል ምርጣችሁ ምግብ ያበላና ሰላምታን የመለሰ ነው። ብለውኛል። እኔንም ብዙ እንዳበላ ያደረገኝ ይህ ነው።” አለ።
ዐሊይ ኢብኑ አቢጣሊብ (ረ.ዐ.) እንዲህ ይሉ ነበር። “ወደ ሱቅ ወጥቼ አንዲት ባርያ ገዝቼ ነፃ ከማደርግ ጓደኞቼን ሰብስቤ አንዲት ቁና ምግብ ባበላ እመርጣለሁ።”
በመሀላችን ያለውን ትስስርና ፍቅር ለማጠንከር ጓደኞቻችንን፣ ወዳጆቻችንን፣ ወንድሞቻችንን እና ጎረቤቶቻችንን ሰብስበን ብንጋብዝ መልካም አየር እንፈጥራለን። ከዚሁ ጋር ምስኪኖችን ማብላት ደግሞ ልዩ ጥቅም አለው።
ልቡ በመድረቁ እየተጎዳ መሆኑን የመሰሞተን አንድ ሰው የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) እንዲህ ሲሉ መክረውታል።
إن أحببت أن يلين قلبك فأطعم المسكين وأمسح رأس اليتيم
“ልብህ እንዲለሰልስ ከፈለክ ሚስኪኖችን መግብ። የየቲምን ራስ አብስ።”
ለድሆችና ለሚስኪኖች የማፍጠሪያ ግብዣዎችን እናዘጋጅ።
ከነርሱም ጋር አብረን በመቀመጥ ምግባቸውን ብንቋደስ እና የወንድምነትና የእህትነት ስሜታቸውን ለማሳደግ ብንሞክር ልብ ላይ የሚፈጥረው የኢማን ስሜት ልዩ ነው።
ከዚህም ጋር ችግር ያለባቸውን፣ በበደል ስር የሚኖሩ፣ ነእስር የሚማቅቁት፣ በመሳደድ ላይ የሚገኙና በረሀብ አረንቋ እየተንገላቱ የሚገኙ ህዝቦችን እናስብ።
من فطر صائما كان له مثل أجره غير أنه لا ينقص من أجر الصائم شيئا
“ፆመኛን ያስፈጠረ ሰው የፆመኛው ምንዳ ሳይቀንስ ለርሱም የፆመኛው አምሳያ ምንዳ።”የሚለውን የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ.) ብስራት እንዳንረሳ።
5.ሠዎችን ማስታረቅ
ብዙ ጊዜ ሠዎች የሚቀያየሙባቸውን ነገሮች ብንመለከት ተራ ጉዳዮች እንደሆኑ እንታዘባለን። ነገር ግን ሰይጣን በመሀል ገብቶ ያቀጣጥለዋል።
ከዚያም አባትና ልጅን ያቆራርጣል። ጎረቤትን ከጎረቤት ጋር ያቃቅራል። ወዳጅን ከወዳጁ ያጣላል። በዚህ በተመረዘ አየር ላይ ጥርጣሬዎች ይበዛሉ። ዝምድናዎችም ይቆረጣሉ። ጠላትነትም ይዋረሳል። ስለዚህ ሠዎችን ለማስታረቅ መጣር ታላቅ ምንዳ አለው።
ብዙ ጊዜ ሠዎች የሚቀያየሙባቸውን ነገሮች ብንመለከት ተራ ጉዳዮች እንደሆኑ እንታዘባለን። ነገር ግን ሰይጣን በመሀል ገብቶ ያቀጣጥለዋል። ከዚያም አባትና ልጅን ያቆራርጣል። ጎረቤትን ከጎረቤት ጋር ያቃቅራል። ወዳጅን ከወዳጁ ያጣላል።
በዚህ በተመረዘ አየር ላይ ጥርጣሬዎች ይበዛሉ። ዝምድናዎችም ይቆረጣሉ። ጠላትነትም ይዋረሳል። ስለዚህ ሠዎችን ለማስታረቅ መጣር ታላቅ ምንዳ አለው።
لَّا خَيْرَ فِي كَثِيرٍ مِّن نَّجْوَاهُمْ إِلَّا مَنْ أَمَرَ بِصَدَقَةٍ أَوْ مَعْرُوفٍ أَوْ إِصْلَاحٍ بَيْنَ النَّاسِ ۚ وَمَن يَفْعَلْ ذَٰلِكَ ابْتِغَاءَ مَرْضَاتِ اللَّهِ فَسَوْفَ نُؤْتِيهِ أَجْرًا عَظِيمًا
“ከውይይታቸው በምጽዋት ወይም በበጎ ሥራ ወይም በሰዎች መካከል በማስታረቅ ከሚያዙ ሰዎች ውይይት በስተቀር በብዙው ውስጥ ደግ ነገር የለበትም። ይኸንንም (የተባለውን) የአላህን ውዴታ ለመፈለግ የሚሠራ ሰው ታላቅ ምንዳን እንሰጠዋለን።” (አን-ኒሳእ 4፤ 114)
የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) በዚህ መልካም ሥራ ውስጥ የሚሳተፍን ሠው ከፆመኞች፣ ከሠጋጆችና ከመፅዋቾች የላቀ ደረጃ እንዳለው ቃል ገብተዋል። ምክንያቱም ይህ ተግባር በማህበረሰብ መሀል እርቅን ማስፋፋት፣ እዝነትና ፍቅርን ማጎልበት ነው። መልእክተኛው (ሰ.ዐ.ወ)
ألا أخبركم بأفضل من درجة الصيام والصلاة والصدقة؟ قالوا: بلي، قال: صلاح ذات البين فإن فساد ذات البين هي الحالقة
“ከፆም ከሶላት እና ከሶደቃ ደረጃ በላይ የሆነን ነገር አልነግራችሁም!?” አሉ። “አዎን! ንገሩን” አሉ፤ ባልደረቦቻቸው። “ሰዎችን ማስታረቅ ነው። በሰዎች መሀል ያለ ግንኙነት መበላሸት (ዲንን) ይላጫል።”የተጣሉ ሠዎችን ይህን የአላህ አንቀፅ እናስታውሳቸው።
وَالصُّلْحُ خَيْرٌ
“መታረቅም መልካም ነው።” (አን-ኒሳእ 4፤ 128)
ከነፍሳችን እንጀምር። የበደለንን ይቅር እንበል። ላስከፋን በጎ እንዋል። ለሌሎች ወገኖች የመቻል፣ የትእግስት፣ የእዝነት እና የሰፊ ልብ ምሳሌ እንሁን።
.........ይቀጥላል
🔂 ሼር 🔂 ሼር 🔂 ሼር 🔂
🍀 ዲነል ኢስላም Tube
🔑"ለመልካም ነገር ቁልፍ ሁን!!"
http://t.me/Dinel_Islam_Tube http: