ሰባሁል ኸይር 𝔖𝚎𝔹𝕒ᕼ 𝓐𝓵𝐤𝐞𝒚ℜ


Channel's geo and language: not specified, not specified
Category: not specified


𝔖𝚎𝔹𝕒ᕼ 𝓐𝓵𝐤𝐞𝒚ℜ
በጀነት ገበያዎች ላይ እየተንቀዋለልን እንገናኝ😍

Related channels

Channel's geo and language
not specified, not specified
Category
not specified
Statistics
Posts filter


የሆኑ ሸኽን የሆነ ቤት ሶደቃ እንሂድ ብለዋቸው አሻፈረኝ አልሄድም ብለው ከብዙ ጭቅጨቃና ማግባባት ቡሃላ ተስማምተው ይሄዳሉ

ቤት እንደገቡ ተበልተው አይደለም በአይን ታይተው የማያልቁ የምግብ መአት ቀርቦ እሳቸው እየተጠበቁ ይደርሳሉ

ታዲያ እየበሉ በመሃል ድንግጥ እያሉ ትከሻቸውን ወደ ላይ ሽክፍ እያደረጉ ያዩዋቸው ሰዎች ምነው እነ ሸህ ደነገጡሳ ቢሏቸው

"የቀረሁ መስሎኝ" 😂😂😂

እንኳንም አልቀረሁ የሚያስብሉ ግብዣዎችን ያብዛልን

https://t.me/SebahulKeyr


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
አልሀምዱሊላህ ዛሬ ደስታችን ወደር የለውም ሶሪያ ከአንባገነኑ አመራር ነፃ ወጥታለች አልሀምዱሊላህ❤️❤️❤️❤️❤️


የተገላለጠችዋን ሲሆን "ምን ታውቃለህ ውስጧ ንፁህ ሊሆን ይችላል" ይላል።
ኒቃብ የለበሰችውን ግን "ከጀርባዋ ምን እንዳለ ምን ታውቃለህ?" ይላሉ።

(لَقَدِ ابْتَغَوُا الْفِتْنَةَ مِنْ قَبْلُ وَقَلَّبُوا لَكَ الْأُمُورَ)

"ከዚህ በፊት ሁከትን በእርግጥ የፈለጉ ሲሆን ነገሮችንም ሁሉ ገለባብጠውልሀል፡፡"
[አተውባ: 48]

ተነካክቶ የተተረጎመ

Mubarek


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
አንድ ቀን ፀሀይን በምስራቅ ስንጠብቃት በመዕራብ መውጣቷ አይቀርም

ያኔ የተውበት በሮች በሙሉ ዝግ ናቸው
መፀፀት የማይጠቅምበት ሰዓት
እድል እና ተስፋ በሙሉ ወደ ጭለማ የሚቀየርበት ሰዓት………😓😓😓


ኢላሂ ………🤲

አንተ ከኔ ሌላ ብዙ አለህ ለማኝ
እኔ ካንተ ሌላ ማን አለ ሚሰማኝ
መንገድ ጠፍቶብኛል በረህመትህ ጥራኝ……

የተብቃቃህ ጌታ የከውኑ ባለቤት
እጆቼን አንስቼ ኢላሂ………እላለሁ እስክትለኝ አቤት
አንተ ከኔ ይልቅ ለኔ ስለምታውቅ
በመንገድህ ምራኝ ወንጀልህን ልራቅ🤲🤲

𝙼𝓑𝐀𝑹𝑬𝔎


አመለ ሸጋው መሐመድ!

መዲና ውስጥ በሚገኝ ገበያ በአንዱ ጥግ ቁጭ ብሎ የሚለምን አይነ ስውር አይ^ሁድ ነበር። ይህ ሰው ዘወትር እዬጮኸ ለአላፊ አግዳሚው በሚያስተላልፈው አንድ መልእክት ይታወቃል። "ወንድሞቼ ሆይ ሙሐመድ ከተባለ ሰው ራቁ። እሱ ቀውስ ነው። ዋሾ ነው። ጠንቋይም ነው። ከቀረባችሁት በድግምቱ ያሳምናችኋል።" ይላል። ረሱሉሏህ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም ስለዚህ በዬቀኑ ስለሚረግማቸውና ሥማቸውን ስለሚያጠለሸው ሰው ሰምተዋል። ግን አልተቆጡም። ከቁብም ሳይጥፉት ነበር የሚያልፉት። ይባስ ብለው ሁሌም ጠዋት ጠዋት ወዳለበት ስፍራ እየሄዱ አንዲት ቃል ሳይተነፍሱ በእጃቸው ይመግቡት ጀመር። መጋቢው ነቢ መሆናቸውን ሳያውቅ አፉ ውስጥ የሚገባውን ለስላሳ ምግብ በደስታ እያኘከ ይውጣል። ሲጠግብ ያመሰግናል። ይህ ሲሆን አንድም ጊዜ ማንነታቸውን አልገለጡለትም። ይሄ ተግባራቸው አንድም ቀን ሳይቋረጥ ከዚህ ዓለም እስኪለዩ ድረስ ቀጠለ።

ደጉ ነቢ ጌታቸውን ተገናኙ። ቀናት አለፉ። ከሳቸው ሌላ ለዚህ ሰው ምግብ የሚያመጣለት አንድም ሰው አልነበረም። አንድ ቀን የነቢ ባለሟል ሰይድ አቡበክር ረ.ዓ ወደ ልጃቸው ሰይደት አዒሻ ረ.ዓ ጎራ ብለው ረሱሉሏህ ያስለመዱትና እሳቸው ሊያስቀጥሉት የሚገባ ለዬት ያለ ተግባር ካለ ጠየቋት። አዒሻ መለሰች። "አባቴ ሆይ! በእርግጥ አንተ ያልተከተልከው የነቢ ኮቴ የለም። አንዲት የቀረች ነገር ብቻ ልጠቁምህ።" አለች። ምን እንደሆነ ጠዬቁ። የገበያውንና የዓይነ ስውሩን ነገር ነገረቻቸው። በማግስቱ ሰይድ አቡበክር ወደተነገራቸው ቦታ ምግብ ቋጥረው አቀኑ። በእጃቸው ዳጎስ ያለ ጉርሻ ያዙና ዓይነስውሩን ሰው ጠጋ ብለው ለመመገብ ሞከሩ። ይሄኔ ሆድ የባሰው ሰውዬው በቁጣ "ማነህ አንተ?!" ብሎ ጮኸ። "ሁሌ ጠዋት ጠዋት ላይ የምመግብህ ሰው ነኛ!" አሉ። "አይደለህም አትዋሸኝ" ብሎ በድጋሚ አንባረቀ። ሰይድ አቡበክር ደነገጡ። "እንዴት እንደዚህ አልክ?" ብለው ጠዬቁት። ሰውዬው መለሰ። "ያኛው ሰው አይከብድም። እጁን መያዝና የሚመግበኝን መቀበል ለኔ ቀላል ነው። ደግሞ ምግቡን ወደ አፌ ከማስገባቱ በፊት ጥሩ አድርጎ ያዘጋጅልኝ ነበር።"

ሰይድ አቡበክር እንባቸውን መያዝ አልቻሉም። ለቀቁት። አሁን ማንነታቸውን ለሰውዬው ማሳወቅ አለባቸው። "አልተሳሳትም። እኔ እስከዛሬ እዬመጣ ሲመግብህ የነበረው ሰው አይደለሁም። ባልደረባው ነኝ። እሱ አሁን እዚህ ምድር ላይ የለም። ያ ሰው የአላህ መልእክተኛ ሙሐመድ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም ነበር።" አሉ። "ሙሐመድ?" ዓይነስውሩ ሰው በድንጋጤ ተውጦ ጠዬቀ። ፋታ ሳይወስድ አስከተለ። "እኮ እያልከኝ ያለኸው ያ አንድም ቀን ሳያቋርጥ በዬቀኑ እየመጣ በእጁ ሲመግበኝ የነበረው ሰው ሙሐመድ ነው ነውን?" "አዎን ሙሐመድ ነበር።" አሉ ሰይድ አቡበክር። ሰውዬው ያልጠበቀውን እውነታ እንደሰማ እዬዬውን አቀለጠው። "ይሄን ሁሉ ጊዜ ስረግመው ሳንቋሽሸው ነበር። እሱ ግን አንድም ጊዜ እንኳን አልወቀሰኝም። ጭራሽ በዬቀኑ እዬመጣ ይመግበኝ ነበር። እንዴት ያለ ቅድስና ነው!? ዋ አለማወቄ!" እያለ ማልቀሱንና በፀፀት ጅራፍ ራሱን መግረፉን ቀጠለ።

አሁን በእርግጥ ጊዜው ረፍዷል። ሆኖም አንድ ነገር ማድረግ ይችል ነበር። እሱንም አደረገው። ኸሊፋው ሰይድ አቡበክር ጋር ቀርቦ በብቸኝነት የሚገዙት አምላክ አላህ እንደሆነና ያ ትልቁ፣ ቸር ለጋሱ፣ አልባሽ አጉራሹ፣ አመለ ሸጋው፣ ለሁሉ አዛኙ ሰው የእርሱ መልዕክተኛ መሆኑን መሰከረ። አሽሃዱአንላኢላሃኢለሏህ ወአሽሃዱ አንነ ሙሐመደን ረሱሉሏህ!!
ሥሙ የተጠራበት ሁሉ ማማሩ! ሸሃዳው፣ ሶላቱ፣ አዛኑ መውት ሐያቱ ያለ ሥሙ አይሞላም። በል ያዘው ደጋግመው ሙሐመድ በለው!!!

ሶሉ_ዓለል_ሐቢብ!
አሏሁመሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዲና ሙሐመድ ወዓላ ኢሊሂ ወሶህቢሂ ወሰለም!💚💚💚

𝙼𝚄𝙱𝙰𝚁𝙴𝙺❤️




ሁሉም ሰው በተመሳሳይ ፍቅር አላደገም ለሁሉም ሰው ህይወት ገር አይደለችም ……አንዳንድ ሰው በልጅነት በገጠመው ሀዘን …ችግር…ግፍ ምክንያት ልቡ ስስ ነው ለመሰበር ምክንያት አይፈልግም መንገድ ላይ አንድ ሰው ገላምጦት ቢያልፍ ሰው ሁሉ ይጠላኛል የሚል ድምዳሜ ውስጥ ሊደርስ ይችላል ……
በተቃራኒው ደሞ በደረሰባቸው ጉዳት ምክንያት ፍቅር መቀበል ምን እንደሆነ ማያውቁ እና ፍቅር ሲሰጣቸው ሊጎዱ አይነት ስሜት ሚሰማቸው ደከም ያሉ የሚያሳዝኑ የአለህ ባሮች ሞልተዋል…!

በቻላችሁት መጠን እንደዚህ አይነት ሰዎች ደመነፍሳቸውን ለማከም ሞክሩ…እዘኑላቸው …ፍቅር እንደሚሰጥ …መወደድ እንደሚገባቸው ምንም ማይጎላቸው ሙሉ ሰዎች እንደሆኑ ንገሯቸው …ተረዷቸው …ውደዷቸው…!

ሰላመን❤️

ᗰᑌᗷᗩᖇᗴK


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ቁርዓንን ለልባችን ❤️


ከሰዎች አንጀትሽን ማን ይበላዋል? ብባል.....

እውነተኛ ማንነታቸውን መቀበል የከበዳቸው ሰዎች። ከሱም ላይ ናርሲስትነት አጥቅቷቸው ሁሉም ነገር ለነርሱ ይገባ እንደነበር በማሰብ ትእቢት ሚወጥራቸው ሰዎች።

ከዛ ያ ይገባኛል ብለው እሚያስቡትን ቦታ፣ ኳሊቲ ፣ እውቀት፣ ንብረት፣መልክ... እንደሌላቸው ማሰብ ስለማይፈልጉ ለመቀየርም ሳይሆን እንዳላቸው ለማስመሰል ይታትራሉ።

ልክ ማዘራቸው ጨው ከጎረቤት እየተበደረች እጭ እሚሏት ሴትዬ ልጅ እሷም ተበድራ የኮሊደሩን ልማት መስላ ከተማው ለይ አለኔ ማን አለ ብላ ስትውረገረግ እና እዩኝ ብላ አሳር ስበላ እንደምትውለው.....

ታድያ ምን ታዘብኩ...ለዚህ ድራማ ደሞ በአካል ማያውቋቸው ኦድየንሶች ጥሩ ግብአት መሆናቸውን። ልክ እንደ fb ኸልቅ... በፖስት እየመጡ መሰከስ ብቻ ነው ሚጠበቅባቸው😂

ታድያ ከድራማቸው አላህ በረዘቃቸው ልክ በሚያተርፏቸው የዋህ ኮሜንታተሮች ....እዛ ፖዚሽን ላይ እንዳለ ሰው ትሪት ሲያደርጉዋቸው በዛ ውስጥ ኢጎዋቸውን ያስታምማሉ።

እስከዚ ያለውኮ አይመለከተኝምም አይረብሸኝም ነበር🙈

በአካልም እዚህም መንደር ከማስተውላቸው ይህ አይነት ችግር ያለባቸው ሰዎች ላይ ምን ተጨማሪ ችግር አለባቸው መሰላቹ.....

አልሞኝ ያልዋቸውን ወይም ደሞ ትክክለኛ ሚመኙት ቦታ ላይ ያሉ ሰዎችን ሲያገኙ ቀድመው ይተናኮሱና ጠበኛ ይሆናሉ😂

እና በጠዋቱ ምን አሳሰበኝ 🤔መሰላቹ....

እሄን ሁላ መፍጨርጨራቸውን በደምብ ገብቶን ከጥግ ሁነን ምንታዘብ መኖራችንን ያውቁ ይሆን ?

ከቀኞቹ አውለኝ😌


ክፍል-2 እውነተኛው የእስር ቤት ገጠመኝ


✍️ሰዎች ምንድን ነው ለማለት ለመጠየቅ መድፈር ተሳናቸው ድባቡ ትንሽ ያስፈራ ነበርና።ነሷራ አምናያዎቹ እሳት የሆነ ግልምጫቸውን መወርወር ጀመሩ እኔም ሓስቢየላህ ወኒዕመል ወኪል እያልኩ ራሴን ለማረጋጋት ሞከርኩ። አሁንም ባለሱፉ ከፌደራሎቹ ጋ ጠጋ ብሎ እንደማስጨነቅ አይነት መንገድ ተጠቅሞ ወደ ቤትህ ምራ በማለት ሲያንባርቅብኝ እኔም ኮስተር ብዬ ቤት የለኝም አልኩኝ
ሃሃሃሃ ቤት የለህም ጎዳና ነው ወይስ ጫካ የምት ኖረው በማለት አሾፉና ያችን ጥቁር ዱላ አስተካከሉ
✍️ኣሃ ሊወግሩኝ ነዋ ብዬ ተመትቸም ቤትም መርቸ ኣይይ ይሄማ አይሆንም ወዳጆቹ እንዲያዝኑ ጠላቶቸ ደስ እንድላቸው አላደርግም ብዬ ከውስጤ ጋ ተስማማሁና ወደ ቤት መምራቱን መረጥኩ ምክናያቱም ተመትቸም ቤትም በግድ መምራቴ አይቀርምና።

✍️ና ብለው ገፍተር ለማድረግ እየሞከሩ ፓትሮል ላይ ጫኑኝና በሒወቴ ጠባሳው የማይለቀኝን ስራ ሊሰሩ ወደ ሰፈር ቤት ፍተሻ ጉዞ ጀመርን።
✍️አንድ ባለሐብት ወንድም ስቴሽነሪ ሱቅ ላይ ተቀጥሬ እሰራ ስለነበር ከተማሪ እስከ የመንግስት ሰራተኛው በርካታው የከተማ ሕዝብ ያውቁኛልና በፓትሮል ተጭኘ ባዩ ጊዜ በድንጋጤ ራሱን የያዘ የሚያለቅስም መንገድ ዳር ቆሞ ሁኔታውንም የሚመለከት ሰው ሞልቷል።

✍️ፓትሮሉ ሰፈር በደረሰ ጊዜ የወታደሩን ድባብ ያዩ የሰፈር ሰወች ህፃናቶች ዋይታቸውን ለቀቁት።
፨ውሓ እየረጨሁ የማጫውታቸው በዚህ ጨዋታ ሱስ የሆነባቸው ከስራ ወደሰፈር መምጣቴን የሚጠባበቁት ህፃናቶች በዛች ቀን ግን ጨለማ የሆነባቸው መሳሪያ የደቀኑና የሰፈሩን ዋና ቦታዎች አቀባብለው በሚጠባበቁ ወታደሮች ተከብቤ ባዩኝ ጊዜ
😥ሰው የሚታሰረው ሰው ጋ ተጣልቶ መሆኑን ብቻ እሱኮ አይጣላም በማለት ከወላጆቻቸው ጋ ይዳረቃሉ።

✍️በዚህ መልኩ ግቢውን አቀባብለው የሚጠብቁ ወታደሮች ተመድበው የተወሰኑት እኔን ይዘው ወደ ቤት ውስጥ ገባን።
✍️እንደ እኔ ቤት ፍተሻ የሚባል ነገር በጣም አሳማሚ ከሕሊና የማይጠፋ ድርጊት ነው።

✍️ኪታቤን ከወጥ ጋ እያዳፉ ዘግናኙ የቤት ፍተሻ ተጀመረ ልብስን በጫማ እየረገጡና ውሓውንም እየደፉ ያጣድፉኝ ጀመር።
✍️አንዱ ፓስፓርት አገኘሁ ሲል ሌላኛው የስላቅ እየሳቀ ሶማሊያ ነው ሶሪያ የምትሄደው ይላል።
✍️ሌላው ፍላሾች አገኘሁ ሲል ኮርስ የሚሰጥበት ነው ይባባላሉ።የባንክ ደብተር አገኘሁ ሲለው ከአረብ አገር የሚቀበልበት ነዋ ይባባላሉ።

✍️ይሄ ሁሉ ኪታብ ምንድን ነው በማለት ከጫፍ ሲነካው ከመደርደሪያ ሙሉ ወረደ በጫማው ረገጠው እኔ ግን አሁን ደንዝዣለሁ

✍️ሰዓቱ እየመሸ ነው መግሪብ ደረሰ ያገኙትን ይዘው ከቤት ወጡና መሳሪያ አለህ አውጣ በማለት ያፋጥጡኝ ጀመር።እኔም እረ የለኝም አልኩ አንዱ ደብተራ አምንያ ማተቡን በእጁ ይዞ አንተ እኛን ልትገድል ነው በማለት በጥፊ ሊማታ ሲንደረደር አንድ ፌደራልና ፖሊስ እረፍ በሕግ ጥላ ስር ነው በማለት አስቆሙልኝ።
መሳሪያውን አውጣ እያሉ የተወሰነ ካስጨነቁኝ በሗላ ቀጥታ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ፓትሮል ላይ ጭነው ይዘውኝ ሄዱ።

✍️የመጀመሪያዋ የእስርቤት አዳር ......

https://t.me/SebahulKeyr




እውነተኛ ታሪክ ክፍል አንድ

☔️ወደ ሗላ ህዳር 8/3/2012 እና እኔ☔️

✍️ቀኑ ሰኞ ነው እንደ አገራችን ሳምንታዊ ቀን አቆጣጠር ሰኞ የመጀመሪያ ቀን የስራ ቀን ነው። እኔም ከሷሒቤ ጋ ከጀመርናት ስራ ላይ ተጥጃለሁ ነገር ግን ብዙ ጊዜ የማያቸው ሕልሞች ውለው ሳያድሩ በዟሒሩ ከች ይላሉና ጁሙዓ ለቅዳሜ ለይል አንድ ሕልም አይቸ ስለነበር በስጋትና በተበታተነ ሐሳብ ውስጥ ነኝ።ለሷሒቤ ሕልሜን ስለነገርኩት እሱም ስጋት ይዞታል ነገር ግን ያ ቀን ሰኞ ድባቡ ደስ ይላል ዝሁር ድረስ ቆየንና ወደየሰፈራችን አመራን።ምሳ በልተን ድጋሜ ወደ ስራ ገብተን ተፍ ተፍ ማለትን ጀመርን አስር ሶላት ደረሰና ሰግጀ ልቤ ጥሩ ስሜት ሲያጣብኝ ወደ እናቴ ደወልኩና ዘለግ ያለ ወሬ አወራ ምነው ድምፅህ አሞሓል እንዴ አለች እናቴ እኔም እረ ደህና ነኝ አልኩ ግራ በተጋባ ስሜት ከዛም በቃ ሰላም አምሹ ተባብለን ስልኩ ተዘጋ።
✍️ከ10ሰዓት ከ30በሗላ ነው የመንግስት ሰራተኛው የሚወጣበት ተማሪውም ከትምህርት የሚለቀቅበት ወቅት ደርሷል ወደ ከተማ ጎራ ብለው አስቤዛ የሚያደርጉ ሰዎች ከተማዋ ላይ የሚርመሰመሱበት ሰዓት ነው።በዚህ ሰዓት ከተማዋ ጭንቅ ጥብብ ብሏታል ፌደራሎች ፣ፖሊሶች ፣ልዩ ሚሽን ፈፃሚ ፖሊሶች ወዘተ አባላት ከተማዋ ዋና ዋና ቦታቸውን ይዘዋል።ከምሰራበት ሕንፃ ፊትለፊት ያለው ሕንፃ ላይ ስናይፐሮች ቦታቸውን ይዘዋል የተሽከርካሪዎች ሐረካ ተቀንሷል ።እኔ ግን ስራ ቦታዬ ውስጥ ነኝና ውጭ ላይ ምን እየተካሄደ እንደሆነ አላወኩም።
✍️ሁኔታውን የሚያዩ ሰዎች ምን አይነት ባለስልጣን ከተማችን መጥቶ ነው ወይስ ምን ምን አይነት ፀጉረ ልውጥ ገብቶ ነው የሚል የስጋት ወሬ ጫጫታ ተያይዟል።

✍️በዚህ ጊዜ ክትትል ክፍሉና የተመረጡ ፌደራሎች ከአጋዥ GPs ጋ በመሆን ከባንክ ባወጡት ፎቶዬ ተመርተው ሱራው ተመሳስሎባቸው አንድ ወንድማችን ሱቅ ጋ በመድረስ ይይዙታል በእርግጥ GpS እሱ አይደለም እያላቸው ነበር እነርሱ ግን መረጋጋት አልቻሉምና
✍️ሱራውን እያሳዩ ይህ አንተ ነህ አሉት ወንድማችንን በድንጋጤ እየተንተባተበ እረ እኔ አይደለሁም ሲላቸው በጣም መደነገጡን እንደ አድቫንቴጅ ተጠቅመው እሽ ይህንን ባለፎቶ ታውቀዋለህ ሲሉት የደነገጠ ሰው ችግር ነውና አወ አውቀዋለሁ አለ።
✍️አወ አውቀዋለሁ ካልክ ጉዳዩ ሲልሲላ አለውና ምራ የሚል ጥያቄ ይከተላል። እናም የት ነው ምራ ሲሉት እሽ በማለት ቀጥታ ወደ እኔ ስራ ቦታ ይዟቸው መጣ።

✍️ልክ ፎቁን ወጥተው ሱቅ በር ላይ ሲደርሱ ወንድማችን ጣቱን ወደ እኔ በመቀሰር 👉ይህ ነው አላቸው። እኔም ምንድን ነው ሸይኽ ፉላን ስል እንባው አይኑን ሲሞላው ተመለከትኩ ኣሓ ያ እጄ በካቴና ውስጥ ሲገባ ያየሁት ሕልም ዛሬም ግልፅ ሆኖ መጣ ማለት ነው ብዬ የያዝኩትን ትልቅ የጨርቅ መቀስ ይዠ ቀጥ ብዬ ቆምኩ።

፨ከተማዋ ውስጥ አይቸው የማላውቀው ሱፉን ደቅ አድርጎ የለበሰ ሰው ወደ ፊት ቀደም ብሎ ፉላን ማለት አንተ ነህ አለኝ ስልኩ ላይ ያለውን ከባንክ የወጣ ፎቶ እያሳየኝ።
እኔን ይመስላል እስኪ ስልኩን አምጣው ብዬ ጠጋ እንደማለት ስል በቅፅበት ረጃጅሞቹ ፌደራሎች ከቀኝም ከግራም እጄን ጠምዘዝ በማድረግ ጠፍንገው ያዙኝና የያዝኩትን መቀስ ቀምተው አስቀመጡ።

✍️ሱቁ ውስጥ ጓደኞቸ ደንግጠው እንደ እንጨት ደርቀዋል እኔ ቀድሞ ኢሻራው ስለመጣ ብዙም አልደነገጥኩም።ያው እጅ ሰጠሁ ማለት ነው ብዬ ለራሴ ነገርኩና ፀጥ አልኩ።

✍️ከሕንፃው በፍጥነት ይዘውኝ ወረዱና የሆነች ቅያስ አለች ወደሷ ገለል አድርገው በከበባ አስቀመጡኝ።በመገናኛ የሚያወሩት ቀውጢ ሆኗል። ሰዎች እንዴ እሱን ለመያዝ ነው ይህ ሁሉ ጋጋታና ወታደር ደህናውን ልጅ ይላሉ......
ይቀጥላል






“ከፅጌሬዳ አበባዎች ጋር አመሳስዬሽ ቢራቢሮዎች እንዲስሙሽማ አላደርግም” አላት … አይ አፍቃሪ በቢራቢሮም ይቀናልኮ😁

https://t.me/SebahulKeyr


እስክንደማ ቆንጥጣችሁን አይዞህ ለምትሉን ነፍሶች
እንኳን ደስ አላችሁ ይሀው ወደቅን አሁንስ ደስተኛ ናችሁ…………
እስኪ እኛ ከወደቅን በኋላ የት እንደደረሳችሁ እናያለን

https://t.me/SebahulKeyr


አንዳንዶች አንተን በመጥፎ ሊጠረጥሩህ ይችላሉ። ሌሎች ደግሞ ከውሀ የጠራህ ንፁህ እንሆንክ የሚያስቡህ ይኖራሉ። እነዛም አይጠቅሙህም፣ እነዚህም አይጎዱህም።የህይወትህን መንገድ ምን እንደምታሳልፍ ምን ላይ እንደሆን ለማንም ማስረዳትም አይጠበቅብህም። ጉዳዩ ትክክለኛው ማንነትህ ነው። አሏህ ስላንተ የሚያውቀው ነገር ነው። ስላንተ ስለሚባለው አትጨነቅ። ማን እንደሆንክ ራስህ ታውቃለህ። አሏህ ንያህንም ሁኔታህንም ይበልጥ ያውቃል። በአንተና በአሏህ መካከል ያለውን ብቻ አስተካክል። ከዛም ተረጋግተህ መንገድህን ቀጥል!


መንገድ ጠፍቶን ስንደናበር ላረጋጉን ...ወደቅን ስንላቸው ላልፈረዱብን...በድለናቸው ይቅርታን ለሰጡን...ሚስጥራቸውን ላጋሩን...ደስታችንን ለተካፈሉን...ሃዘናችንን ቦታ ለሰጡት...ለተጠነቀቁልን...አጋርነታቸው ወረት ለሌለበት...ደግነታቸው ለማይስተን...ለሚወዱን...ሊረዱን የመንገዳችን ጫፍ ድረስ አብረውን ለሚጓዙት...ለሚያበረቱን...ሰላም ለእናንተ😊..ኑሩልን የህይወታችን ቅመሞች❤


ሰላም ባንተ ላይ ይሁን ወዳጄ…… ❤️

ኢማሙ አህመድ አንድ ጊዜ ተጠየቁ:-
ከሰዎች አዛ እንዴት ነው ሰላም መሆን ምንችለው ? ተብለው
እሳቸውም እንዲህ አሉ

ትሰጣቸዋለህ አትወስድባቸውም……
አዛ ያደርጉሃል አዛ አታደርጋቸውም………
ችግሮቻቸውን ትፈፅምላቸዋለህ ያንተን ችግር እንዲፈፅሙ አትጠብቅም………

ያኔ ጠያቂው"ይሄማ በጣም ከባድ ነው "አለ

እሳቸውም "አዎ ከሰዎች አዛ መቼም ሰላም መሆን አይቻልም "አሉ

እናም ወድማለም………
ከሰዎች ወቀሳ ሀሜት ውሸት እና አዛ መዳን እማይታሰብ ነው ………ዋናው ነገር የሚናገሩብህ እና የሚያወሩብህ ነገር እውነት እንዳይሆን
በድርጊቶችህ ላይ ውለታን አትጠብቅ ……
አንዳንዴ ስብራትህ እሚሆነው ብዙ ሰርተህለት ብዙ ወዳጅነት በመካከላችሁ ያለ በሚመስልህ አስመሳው ሰው ነው……

ለዚህም ነው ሀቢቡና እንዲህ ያሉት:-
"ወንድሙን በማገዝ ላይ እራሱን ቢዚ ያደረገ አለህ እሱን በማገዝ ላይ ይሆናል"ያሉት

አስተውል ወንድሙን ያገዘ "አለህ"ያግዘዋል እንጂ "ከወንድሙ ምላሹን ያገኛል" አላሉም

እናም ሁሌም በቆምክበት መሰረት ላይ ቀጥ በል የሰዎች የቃላት አሉባልታ እንዳያንገዳግድህ …………

መልካም ኸሚስ…❤️❤️❤️❤️

20 last posts shown.

174

subscribers
Channel statistics