የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ የዳይሬክተሮች ቦርድ ተቋቋመ‼️
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ የዳይሬክተሮች ቦርድ ተቋቋመ።
ቦርዱ በውጭ ሀገራት የሚኖሩ 11 ኢትዮጵያውያን፣ የሲቪል ማኅበራትና የኢትዮጵያ መንግሥት ተወካዮች አሉት።
የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ አማካሪ አባላት የተመሰከረላቸው አምስት በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ ሦስት ከሴቶች፣ ከወጣቶችና ከኢትዮጵያ ነዋሪዎች የተውጣጡ አባላት ያሉት የሲቪክ ማኅበራት ተወካዮችና ሦስት የኢትዮጵያ መንግሥት ተወካዮች ይገኙበታል።
የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ የዳይሬክተሮች ቦርድ፣ የፈንዱን አጠቃላይ ፖሊሲ፣ ስትራቴጂ፣ ቁጥጥርና ተጠያቂነት የሚያስተዳድር የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ የበላይ ነው።
ከሥራዎቹም መካከል በኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ ተለይተው የሚታወቁ እና የተረጋገጡ ፕሮጀክቶችን ድጋፍ በመመርመር እንደሚያጸድቅ ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
በዚህም መሠረት የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ዝርዝር ከዚህ የሚከተሉት ናቸው፤
1. ሥርጉት ያደታ፥ ሎይድ ባንክ ግሩፕ
2- ዶክተር ምሕረት ማንደፍሮ፥ ትሩዝ ኤይድና ቃና ቴሌቪዥን
3. ቸርነት ደበሌ፥ ኪያ ትራቭል እና ቢዝነስ
4. ዮሐንስ አሰፋ፥ ዮ.ኤስ.አይ.ዲ
5. ዶክተር አብዱልዋሀብ ኢብራሂም አቡዳቢ
6. ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ፥ ሜሪጆይ ኢትዮጵያ
7. የወጣቶች ተወካይ በቦርድ ታይቶ የሚወሰን ይሆናል
8.ኢየሱስ ወርቅ ዛፉ፥ ኅብረት ባንክ
9.ሰላማዊት ዳዊት፥ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ
10. ሂሩት ዘመነ ፥ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት
11. ብሌን ማሞ፥ ገንዘብና የኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር መስሪያ ቤት
@Ebstube@Ebstube