❀✞ማኅተብ የማሰር ጥቅሙ❀✞
❤️🔥[ክፍል - 3]❤️🔥
ማተብ ማሠር በኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ዘንድ ለብዙ ጊዜ ጸንቶ ለመኖር የቻለው ጥቅሙ የጐላ ሆኖ በመገኘቱ ነው። ለአንድ ሀገር አንድ ሰን ደቅ ዓላማ ለአንድ መሥሪያ ቤትም አንድ ዓይነት የጽሑፍ ምልክት ወይም አርማ እንደሚያስፈልገው ሁሉ በአንድ ሃይማኖት ጥላ ሥር ላለ ሕዝብም አንድ ዓይነት ምልክት በማስፈለጉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባሎችም በዚሁ ምልክት ሲጠቀሙ ቆይተዋል፤ አሁንም በመጠቀም ላይ ይገኛሉ። ይህ ምልክት በሀገራችን በሃይማኖት አንድነት የሌላቸው ሁሉ በአንድነት ሊፈጽሙት የማይገባቸውን ከመፈጸም እንዲድኑ ከማድረጉ በላይ አንድ መንገደኛ ሰው ሞቶ በተገኘ ጊዜ ክርስቲያንነቱ በዚሁ ምልክት አመልካችነት ተረጋግጦ አስፈላጊው ጸሎተ ፍትሐት ተደርጎለት በዐፀደ ቤተ ክርስቲያን እንዲቀበር በማድረግ ሲያገለግል ቆይቷል።
በጊዜያችን ግን ሃይማኖት በልብ ነው ምልክትም አያስፈልገውም በማለት በዚህ ምልክት የማይጠቀሙ ሰዎች እየበረከቱ ሄደዋል። የሚሰጡትም ምክንያት ጽዳት ያጐላል የሚል ነው፤ ጽዳት የማጉደሉ ሁኔታ ግን እንዳያያዙ ነው፤ የሚፈለገው ምልክትነቱ ነው እንጂ አንዳንዶቹ እንደሚያደርጉት የዐሥራ አምስት ክታብ ወይም ግሥንግሥ መሰብሰቢያ ማድረግ አይደለም።
ምንጭ :- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖትና ሥርዓት(በአእምሮ ማንደፍሮ የተዘጋጀ)
wwu>w.ethiopianorthodox.org
❤️🔥[ክፍል - 3]❤️🔥
ማተብ ማሠር በኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ዘንድ ለብዙ ጊዜ ጸንቶ ለመኖር የቻለው ጥቅሙ የጐላ ሆኖ በመገኘቱ ነው። ለአንድ ሀገር አንድ ሰን ደቅ ዓላማ ለአንድ መሥሪያ ቤትም አንድ ዓይነት የጽሑፍ ምልክት ወይም አርማ እንደሚያስፈልገው ሁሉ በአንድ ሃይማኖት ጥላ ሥር ላለ ሕዝብም አንድ ዓይነት ምልክት በማስፈለጉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባሎችም በዚሁ ምልክት ሲጠቀሙ ቆይተዋል፤ አሁንም በመጠቀም ላይ ይገኛሉ። ይህ ምልክት በሀገራችን በሃይማኖት አንድነት የሌላቸው ሁሉ በአንድነት ሊፈጽሙት የማይገባቸውን ከመፈጸም እንዲድኑ ከማድረጉ በላይ አንድ መንገደኛ ሰው ሞቶ በተገኘ ጊዜ ክርስቲያንነቱ በዚሁ ምልክት አመልካችነት ተረጋግጦ አስፈላጊው ጸሎተ ፍትሐት ተደርጎለት በዐፀደ ቤተ ክርስቲያን እንዲቀበር በማድረግ ሲያገለግል ቆይቷል።
በጊዜያችን ግን ሃይማኖት በልብ ነው ምልክትም አያስፈልገውም በማለት በዚህ ምልክት የማይጠቀሙ ሰዎች እየበረከቱ ሄደዋል። የሚሰጡትም ምክንያት ጽዳት ያጐላል የሚል ነው፤ ጽዳት የማጉደሉ ሁኔታ ግን እንዳያያዙ ነው፤ የሚፈለገው ምልክትነቱ ነው እንጂ አንዳንዶቹ እንደሚያደርጉት የዐሥራ አምስት ክታብ ወይም ግሥንግሥ መሰብሰቢያ ማድረግ አይደለም።
ምንጭ :- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖትና ሥርዓት(በአእምሮ ማንደፍሮ የተዘጋጀ)
wwu>w.ethiopianorthodox.org