MuhammedSirage M.Nur G:
"ሞት"
ትናንት ያኗኗረን አብሮን የደገሰ
በቤት በመንደሩ ስቆ እንዳልነገሰ
የሱም ቀን አክትሞ ጥሎን ገሰገሰ
ያ ሁሉ አለፈና አፈር ተንተራሰ ።
እንዲያ እንዳልተሳቀ አጭቶና አግብቶ
ከብሮም እንዳልታየ ሽጦና ገብይቶ
በሄደበት መሬት ዛሬ አየንው ገብቶ።
የወጣት ጉልበቱ ላልቶና ደካክሞ
የልጅነት ወዙ ወይቦና ከስሞ
ስንቱ ሰው ተለየን አብሮን ሲስቅ ከርሞ!!
ስንቱም "ልጅ" ተለየን ጉተናው ሳይጠና
ገና እንደጀመረ የኑሮን ጎዳና
ገና ሳይደርስበት የሶስቱን ጉልቻ
ሳይደገስለት ለትዳር ጋብቻ።
ከቶ ስንቱ ሄደ ስንቱ ሰው አለቀ
የተፃፈለትን ቀን እየጠበቀ! !
ተው ወንድሜ ይብቃን ይሙት መታወሩ
በቤት በመኪና ጠምብዞ መስከሩ
ቀብሩን መዘንጋቱ በቃ ያክትምለት
በመልካም እንተካው ያለፈን ያመፅ ‘ለት!!
t.me/MSirageText
"ሞት"
ትናንት ያኗኗረን አብሮን የደገሰ
በቤት በመንደሩ ስቆ እንዳልነገሰ
የሱም ቀን አክትሞ ጥሎን ገሰገሰ
ያ ሁሉ አለፈና አፈር ተንተራሰ ።
እንዲያ እንዳልተሳቀ አጭቶና አግብቶ
ከብሮም እንዳልታየ ሽጦና ገብይቶ
በሄደበት መሬት ዛሬ አየንው ገብቶ።
የወጣት ጉልበቱ ላልቶና ደካክሞ
የልጅነት ወዙ ወይቦና ከስሞ
ስንቱ ሰው ተለየን አብሮን ሲስቅ ከርሞ!!
ስንቱም "ልጅ" ተለየን ጉተናው ሳይጠና
ገና እንደጀመረ የኑሮን ጎዳና
ገና ሳይደርስበት የሶስቱን ጉልቻ
ሳይደገስለት ለትዳር ጋብቻ።
ከቶ ስንቱ ሄደ ስንቱ ሰው አለቀ
የተፃፈለትን ቀን እየጠበቀ! !
ተው ወንድሜ ይብቃን ይሙት መታወሩ
በቤት በመኪና ጠምብዞ መስከሩ
ቀብሩን መዘንጋቱ በቃ ያክትምለት
በመልካም እንተካው ያለፈን ያመፅ ‘ለት!!
t.me/MSirageText