🛑የኢትዮዺያ ብሔራዊ ባንክ Cryptocurrency መጠቀም እንደ ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ተቆጥሮ በህግ ፊት እንደሚያስጠይቅ ትናንተ ከዘመን ጋዜጣ ያየሁት ፅሁፍ ይናገራል።
🛑ይህ ፅሁፍ ብሔራዊ ባንክ ለፕረስ ጋዜጣ ያወጣው ፅሁፍ ሲሆን ለጠቅላላ ዕውቀት ይሆናቹ ዘንድ ቃል በቃል Copy Paste ያለምንም ጭማሬ እና ቅነሳ አስቀምጬላቹሀለው።
ከኢትዮዺያ ብሔራዊ ባንክ የተሰጠ የፕረስ መግለጫ
የኢትዮዺያ የገንዘብ መደብ ብር እንደሆነ እና በብሔራዊ ባንክ በሌላ አኳኃን ካልተፈቀደ በስተቀር በሀገሪቱ የሚከናወኑ ማናቸውም የገንዘብ ግንኙነቶች ሁሉ የሚከፈሉት በብር እንደሚሆን የብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 591/2000 በግልፅ ይደነግጋል። በተጨማሪም በክፍያ ሥርአት አዋጅ ቁጥር 718/2003 መሠረት በየትኛውም የክፍያ መፈፀሚያ ሰነድም ሆነ ሥርአት ያለ ብሔራዊ ባንክ ፍቃድ የገንዘብ ዝውውርም ሆነ ገንዘብ ነክ አግልግሎት መሥጠት አይቻልም።
ነገር ግን ከጥናት ለመረዳት እንደተቻለው በአሁኑ ወቅት ከህግ እውቅና ውጩ የክሪፕቶ ከረንሲ፣ እንደ ቢትኮይን እና የመሳሰሉት የምናባዊ ንብረት/ገንዘብ (ቨርቹዋል አሴት) በሀገራችን እየተስፋፋ መጥቷል።
በተጨማሪም ይህ ተግባር ከብሔራዊ ባንክ ውጪ ከፍተኛ የገንዘብ ዝውውር የሚደረግበት፤ እና በተለይም በወንጀል የተገኘን ገንዘብ ለማሸሽ ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ እንደሆነ ለመረዳት ተችሏል።
ይህ እየተስተዋለ ያለው ምናባዊ ንብረት/ገንዘብን ለግብይት ወይም ለክፍያ መጠቀም በኢትዮዺያ ብሔራዊ ባንክ ዕውቅና ያልተሰጠው ድርጊት በመሆኑ ሕብረተሰቡ ከእንዲህ አይነት ሕገ-ወጥ ተግባር እራሱን መጠበቅ ይኖርበታል።
በመሆኑም ይህን ፈፅመው በሚገኙ አካላት ላይ ብሔራዊ ባንክ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ እየገለፅን፤ ሕብረተሰቡም ይህንን ሕገወጥ ተግባር የሚሠሩ አካላትን ሲመለከት ለብሔራዊ ባንክ እና ለሚመለከታቸው ህግ አስከባሪ አካላት ጥቆማ እንዲሰጥ እናሳስባለን።