ዲያቆን ንጋቱ ተሰማ


Kanal geosi va tili: ko‘rsatilmagan, ko‘rsatilmagan
Toifa: ko‘rsatilmagan


ይህ የኔ የዲያቆን ንጋቱ ተሰማ chanal ነው
በዚ chanal መንፈሳዊ የሆኑ ጽሁፎች የቤተክርስቲያን ዜናዎችን አቀርባለሁ

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
ko‘rsatilmagan, ko‘rsatilmagan
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri






















#እንኳን #ለአቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ_በዓል_በሰላምና_በጤና_አደረሳችሁ፡፡
መጋቢት ፭ በዓለ ዕረፍት ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
#share
አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (አቦ፥ አቡዬ)፤
* እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ብርሃነ ዓለም የኾኑ፤
* እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ክብርን የተሞሉ፤
* ኰከበ ገዳም፥ መናኔ ዓለም፥ ምድራዊ መልአክ፤
* ስማቸውን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ያወጣላቸው፤
* በአክናፈ መባርቅት ተጭነው የሚጓዙ፤
* 60 አናብስትና 60አናብርት ይታዘዙላቸው የነበሩ፤ የእግራቸው ትቢያ ለአራዊቶቹ ምግብ የኾነላቸው፤
* ለብዙ አእላፍ ቅዱሳን ወላዴ የኾኑና በረከትን የሰጡ ታላቅ አባት (ለአብነትም፤ ለቅዱስ #ላሊበላ፥ ለአቡነ #ሳሙኤል ዘዋልድባ፥ ለአባ #አንበስ ዘደብረ ሐዘሎ፥ ለአባ ብንያም ዘግብፅ)
፠፠፠ #ምድረ_ከብድ_፤ /ዝ_ምድር_ክቡድ_ውእቱ_/ ፤ #ዝቋላ (#ዝ_ቆላ)
 ምድረ ከብድ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ለመጀመሪያ ጊዜ ያረፉባት ቦታ ናት፤ ቀጥሎ ወደ ደብር ቅዱስ #ዝቋላ (#ዝ_ቆላ) ለጸሎት ሂደው ለሃገራችን ኢትዮጵያና ለዓለማችን ምሕረትና በረከትን ከአምላካችን ለ100 ዓመታት በባሕር ውስጥ ሆነው ለምነዋል፤
*ወደ ምድረ ከብድ ተመልሰው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል፤ ቊራም በሰይጣን ተመስሎ መጥቶ ዓይናቸውም ቢያጠፋውም ከ7 ሱባዔያት በኋላ ሊቀ መላእክት ሚካኤልና ገብርኤል ዓይናቸውን መልሰውላቸዋል፡፡
*ወደ ዝቋላ በመመለስም አጋንንትም ከምድረ ዝቋላ አጥፍተዋል፤
፠ እንደገና ወደ ምድረ ከብድ ተመልሰው በነበሩበት ጊዜ ታላላቆቹና በአንበሳ ዘባን ላይ የሚሄዱት #አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ ፣ #አባ_አንበስ_ዘደብረ_ሐዘሎ_አፋር)፣ #አባ_ብንያም_ዘግብፅ ከአባታችን ቡራኬ ለመቀበል መጡ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ተሰውረው ነበርና፤ የአቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ አናብስት የ3ቱን አባቶች አናብስት በሉባቸው፤ በ7ኛው ቀን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ተገልጠው የኾነውን ነገር በማየት የተበሉትን አናብስት እንዲመልሱ የራሳቸውን አናብስት አዘዟቸው መልሰውም እንደነበሩ በተዓምራት አስነስተው ሰጧቸው፤ በደመና ጠቅሰው ቅዱስ ፋኑኤል 3ት ሰማያዊ ኅብስትና 3ት ጽዋዕ ይዞ ለእንግዶቻቸው ይዘው ሠረገላ በሚባለው ዋሻ አመጡላቸውና ሰጥተው ሸኟቸው፤ እነዚህን ቅዱሳን በሸኙ በ7ኛው ቀን ወደ ተለያዩ ሃገራት ሄደው አስተምረዋል፡፡
፠ እድሜያቸው ረዥም እንደመሆኑ፤ ቅዱሱ ንጉሥ አፄ ላሊበላን ጨምሮ ሌሎችም ቅዱሳን ወደ ርሳቸው እየመጡ በረከትን ተቀብለዋል፡፡
፠#በግብፅ_300_ዓመታት_፥ #በኢትዮጵያ_ምድር_ላይ_262_ዓመታት (በዋነኛነት #በምድረ_ከብድና_በዝቋላ_ ቢኖሩም ሌሎችም የመሠረቷቸውና የኖሩባቸው ገዳማት አሉ፤ ለአብነትም ደቡብ ወሎ የሚገኘውን #ገዘዛ_አቦን_ መጥቀስ ይቻላል)
፠ በድምሩ 562 ዓመታት ከኖሩ በኋላ በንጉሥ ሕዝብናኝ(እንድርያስ) ዘመነ መንግሥት፤ መጋቢት 5 ቀን ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ብዙ ቃል ኪዳንን ጌታችን ሰጣቸው፥ 12 አክሊላትንም አቀዳጃቸው፤ የነበሩባት ምድረ ከብድ ገዳም ግን ራደች፥ ተንቀጠቀጠች፥ በብርሃንም ተጥለቀለች፤ ዝቅ እያለችም መንሸራተት ጀመረች፤ ጌታችንም አንቺ መሬት ሆይ ጽኚ ይህንን ኹሉ ስለቻልሽ ምድር ክቡድ /ኋላ ምድረ ከብድ/ ተብለሽ ተጠሪ አላት፤ የጻድቁም ነፍስ ከሥጋቸው ከሌሊቱ 6 ሰዓት ተለየች፡፡
፠ ይህችውም ምድረ ከብድ ጻድቁ የኖሩባትና የቀደሱባት፥ የመሠረቷትና ያነፅዋት፣ ሠራዊተ መላአክት የከተሙባት፣ ታላላቅ አበው መጥተው በረከት ከአባታችን የተቀበሉባት፣ አርምሞና ጸጥታ የማይለያት፤ አጸዷና ቅጥሯ ልቡናን የሚመስጥ፤ ከአ.አ 125 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ናት፡፡

ወተቀበልዎ መላእክት በስብሐት ወበማኅሌት፤
ወአብዕዎ ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ አብዕዎ ገብረ ሕይወት፡፡

@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5




``ዮሐንስ መደብር``

ከኢትዮጵያ ተሰርቆ ወደ ውጪ ሀገር ተወስዶ ከሊቃውንት ዐይን ለዘመናት ተደብቆ የቈየው፥ የነቅዩስ ጳጳስ በነበረው ቅዱስ ዮሐንስ በዓረብኛ ቋንቋ የተደረሰው፥ ድንቅ መንፈሳዊ የታሪክ፣ የምርምር፣ የጥበብ፣ የፍልስፍና መጽሐፍ የሆነው ``ዮሐንስ መደብር`` የተሰኘው መጽሐፍ በሚደንቅ የአተረጓጐም ስልት ተተርጒሞ፥ ለአንባብያን እንዲመች ተደርጎ፥ ጎን ለጎን በግእዝና በአማርኛ ሆኖ ተጽፎ የሕትመት ቀኑን በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።

ይህ ``ዮሐንስ መደብር`` የተሰኘው የነቅዩስ ጳጳስ የዮሐንስ መጽሐፍ ዐረብኛንና ግእዝን አቀላጥፎ ይችል በነበረው፥  ዲያቆን ቅብርያል በሚባል ግብጻዊ ዲያቆን በ16ኛው መ.ክ.ዘ የሰራዊት አለቃ በነበረው አትናቴዎስና በእቴጌ ማርያም-ሥና ትእዛዝ  በ፲፭፻፺፬ (1594) ዓ.ም በዐፄ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት በአራተኛው ዓመት ከልሳነ ዐረቢ ወደ ልሳነ ግእዝ ተተርጕሟል። ተሰርቆ ወደ ውጪ ሀገር እስከ ተወሰደበት ዘመን ድረስም ብዙ ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ይማሩበትና ያስተምሩበት የነበረ መጽሐፍ ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ የተለያዩ ሀገራት ሐያልነትን ከመተረክ አልፎ የሐበሾች/ኢትዮጵያውያን አኵሪ የጀግንነት ታሪክን በሰፊው የሚያትት ድንቅ መጽሐፍ ነው።

የ``ዮሐንስ መደብር`` ይዘት በጥቂቱ፦

●በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ታሪካቸው ያልተሟሉትን አሟልቶ ይዟል።
●ከአዳም ጀምሮ እስከ እስከ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ ያለው፥ ለ6200 ዓመታት የዘለቀው፥ የስድስት ሺህ ዓመታት ታሪክን አጠቃሎ ይዟል።
●በዓለም ላይ የነገሡት የተለያዩ ሀገራት  ኀያላን ነገሥታት ሙሉ ታሪካቸውን ይተርካል።
●በዓለም ላይ የተነሡትን መናፍቃን ታሪካቸውንና ምንፍቅናቸውን ተርኮ መልስ ይሰጣል።
●ከአንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን አንሥቶ እስከ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ የተነሡትን ቅዱሳን ሊቃውንትን በመዘርዘር ሙሉ ታሪካቸውን ያስቀምጣል።

የዮሐንስ መደብር ጥቅሙ፦

●የመጽሐፍ ቅዱስ ዕውቀትዎን ሙሉ ያደርጋል።
●ዓለም ዐቀፍ ታሪክን እንዲያውቁ ያደርጋል።
●መናፍቃን ለሚያነሧቸው የምንፍቅና ትምህርቶች መልሳቸውን እንዲያውቁ ያስችላል።
●የእግዚአብሔር ሀልዎትና መግቦት፣ አንድነትና ሦስትነት፥ በጥቅሉ ምሥጢረ ሥላሴን በጕልህ እንዲያውቁ ይረዳል።
●ነገረ ማርያም፣ ነገረ ቅዱሳንንና ነገረ መስቀልን በአግባቡ እንዲገነዘቡ ያደርጋል።
●የኢትዮጵያ ጥንታዊ ዓለም ዓቀፋዊ መሪነትንና ኀያልነትን እንዲያውቁ ያደርጋል።
●የተለያዩ ነገድ አሰፋፈርና አቀማመጥን ለይተው እንዲያውቁ ያግዛል።
●ስለ ሥነ ፈለክ፣ ስለ ዑደተ ፀሓይ ወወርሕ፣ ስለ ምሕዋረ ከዋክብትና ስለ ዐበይት አፍላጋት... ሰፊ ዕውቀትን ያስጨብጣል።
●የግእዝ ቋንቋ ክህሎትዎን ያዳብራል።

የመጽሐፉ ተርጓሚና አሳታሚ፦
መጋቤ ምስጢር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ
በድሬዳዋ ርእሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል የቅኔና የመጽሐፍ ትርጓሜ መምህር፥ የድሬዳዋ ሊቃውንት ጉባኤ ዋና ጸሓፊ

👇ለሚያደርጉልኝ ድጋፍ ከወዲሁ ልባዊ መንፈሳዊ ምስጋናዬን እያቀረብኩ መጽሐፉ ታትሞ ገበያ ላይ እንዲውል እስፖንሰር ለመሆንና ለማገዝ፥ አልያም ቀድሞ ተመዝግቦ መጽሐፉን ለመግዛት የሚከተለውን ሊንክ ጠቅ አድርገው ቢገቡ ያገኙናል።👇

https://t.me/yohanis_medebir




ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈ dan repost
​​👼 ቅዳሴ ማለት ምንም ማለት ነው?
🤔 በቅዳሴ ጊዜ 5ቱ ምሥዋዕቶች ምን ምን ናቸው?
🥰 14ቱ ፍሬ ቅዳሴያት እነማን ይሆኑ?

😇 ካህናት በቅዳሴ ወቅት 2: 3: 4: 5: 7: 12: ወይም 24: ሆነው ከቀደሱ ምሳሌነቱ ምን ምን ይሆን?
🧎‍♂ እኛ ክርስቲያኖች ቅዳሴን ባስቀደስን ቁጥር 4 ነገሮች እናገኛለን ምን ይሆኑ?
👼 አምስቱ የስሜት ሕዋሳት በፀሎተ ቅዳሴ ጊዜ ያስቀድሳሉ እንዴት?


            ይ🀄️ላ🀄️ሉ ይማሩ
                  👇🏾👇🏾👇🏾

https://t.me/addlist/AQPOMxHXz_42NDE0


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን✝

❖❖ታላቅ መንፈሳዊ የንግስ ጉዞ ወደ ምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መነሰፈስ ቅዱስ ገዳም❖❖


የተወደዳችው የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን ቆያችሁ እግዚአብሔር አምላካችን የተመሰገነ ይሁን እንደሚታወቀው #መጋቢት_5 ቀን የአባታችን የ እረፍት ክብረ በዓል በደማቅ ሁኔታ ይከበራል ስለዚህም በየአመቱ ማህበራችን ይህን አመታዊ የማይቀር ጉዞ በደማቅ ሁኔታ አዘጋጅቶሎታል ፈጥነው በመደወል የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ!

የጉዞ ቦታ :- ምድረ ከብድ

የጉዞ ቀን ፦  መጋቢት 4 - 5

የጉዞ መነሻ:-  12:00


የጉዞ መነሻ ቦታ:- ፒያሳ ጊዮርጊስ

የጉዞ ዋጋ:- 800 ብር

ጉዞውን ለመሄድና ከበረከቱ ለመሳተፍ ከስር በተጠቀሱት ስልክ ቁጥሮች በመደወል ተመዝገቡ ያለን ውስን ቦታ ስለሆነ....!!!!!!
   
   |➛ +251910455701
   |➛ +251911354174
   |➛ +251961089373
    "ወስብሃት ለእግዚያብሔር ወለ ወላዲቱ ድንግል "
.አዘጋጅ:- ማህበረ እመጓ ዑራኤል ወ አቡነ መልከፀዴቅ




✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ስርዓተ ምልጣን ዘመጋቢት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊
ከሁሉ አስቀድሞ ጸሎት ከተደረሰ በኃላ ዲያቆን መስቀሉን ይዞ ምስባክ ይስበክ

ምስባክ፡90፡13

ይበል ዲያቆን:
ወትከይድ አንበሳ ወከይሴ፡፡
እስመ ብየ ተወከለ አድኀኖ፡፡
ወእከድኖ እስመ አእመረ ስምየ፡፡
ወንጌል ፡-ሉቃ.21፡33-ፍ.ም

ወንጌል ከተነበበ በኃላ

እስመ ለዓለም #በቅኝት መጀመሪያ ይሉትና ሌሎች በዜማ #ይቀበላሉ

እስመ ለዓለም
ይትፌስሑ በኀበ አልቦቱ ሞት፤ይነሥኡ እሴቶሙ፤እስመ ትዕግሥት ተውህበ ሎሙ ከመ ይንሥኡ፤ብዙኅ ሕማሙ ለጻድቃን፤ ወእምኵሉ ያድኅኖሙ እግዚአብሔር፤ወየዓቅብ ነፍሳቲሆሙ፤እስመ እንዘ ይነብሩ ውስተ ዓለም እለ ሎቱ ተቀንዩ በሕይወቶሙ ፤(ማንሻ-) ከመ ይንሥኡ አስበ ስብሐቶሙ፤ አክሊል ንጹሕ ዲበ ርእሶሙ

መቃኘታቸው -=አይሁድ ጌታን ለመያዝ ይሁዳን አመልካች አድርገው ለመፈለጋቸው ምሳሌ ነው

መቀበላቸው፦የአይሁድ ጭፍሮች ጌታን ከይሁዳ ተረክበው ውሳኔያቸውን የመፈጸማቸው ምሳሌ

🕊🕊
ግሩማን መላእክት ሱራፌል ወኪሩቤል፤ እለ አክናፊሆሙ ነበልባል፤ ወረዱ ዮም ይትቀበሉከ በብሂል፤ አማን፤ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል።

ስርአተ ምልጣን፦

መሪ-ሃሌ ሉያ
ተመሪ-ሃሌ ሉያ
መሪ- ግሩማን መላእክት
ተመሪ- ግሩማን መላእክት
መሪ- ሱራፌል ወኪሩቤል
ተመሪ-ሱራፌል ወኪሩቤል
መሪ- እለ አክናፊሆሙ ነበልባል
ተመሪ- እለ አክናፊሆሙ ነበልባል
መሪ- ወረዱ ዮም
ተመሪ- ወረዱ ዮም
መሪ- ይትቀበሉከ በብሂል
ተመሪ- ይትቀበሉከ በብሂል
መሪ-አማን
መሪ-አማን
መሪ- ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል።
ተመሪ- ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል።

ከዚህ በኃላ "ሃሌ ሉያ" ብሎ ዝማሜውን ይዘምማሉ፤ ንሺው ጋር በመሄድ ለሁለት ረዘም ባለ ዜማ ይመራራሉ

መሪ-ወረዱ ዮም
ተመሪ- ወረዱ ዮም
መሪ- ይትቀበሉከ በብሂል
ተመሪ- ይትቀበሉከ በብሂል
መሪ-አማን
ተመሪ- አማን


በዝማሜ ሁሉም - ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል

መምራት፦ ሊቀ ካህናት ሐና ጌታን እንዲይዙ ጭፍሮችን የመላኩ ምሳሌ

መመራት፦የአይሁድ ጭፍሮች በተሰጣቸው ትዕዛዝ መሠረት ጌታን ይዘው መጀመሪያ ከሊቀ ካህናቱ ሀና ፊት ለማቅረባቸው ምሳሌ

ዝማሜ፦መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሀና ወደ ቀያፋ ፣ከጲላጦስ ወደ ሔሮድስ መመላለሱንና መውደቁን ያመለክታል። በመቋሚያው መሬቱን መምታታቸው አይሁድ የጌታን እራስ በዘንግ መምታታቸውን ያመለክታል።

ሁለተኛ ሰው ከንሺው ጀምሮ ያነሳል

ወረዱ ዮም ይትቀበሉከ በብሂል፤ አማን በአማን፤

በዝማሜ ሁሉም - ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል።

ሶስተኛ ሰው አሁንም እንዲሁ ንሺውን ያነሳል

በመቀጠል  "አማን በአማን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል "  የሚለው በዝማሜ ተብሎ ከጽናጽል ና ከከበሮ ጋር ይቀርባል

አባባሉም፦
በጽፋት የከበሮ አመታት ፩ ጊዜ

አማን በአማን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል

ከዚያ በቁርቋሮ እና በጽፋት

አማን በአማን አማን በአማን ገብረ መንፈስ ቅዱስ አማን በአማን ....     ፩ዴ በቁርቋሮ
አማን በአማን አማን በአማን ገብረ መንፈስ ቅዱስ አማን በአማን....    ፩ዴ በጽፋት

ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል....     ፩ዴ በቁርቋሮ
ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል....    ፩ዴ በጽፋት

አመላለስ አባባል ፦

አማን በአማን አማን በአማን ገብረ መንፈስ ቅዱስ አማን በአማን አማን በአማን/፪ ጊዜ/
ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል/፪ ጊዜ/

አመላለሱ ተብሎ እንዳለቀ በጽፋት የከበሮ አመታት

ወረዱ ዮም ይትቀበሉከ በብሂል፤ አማን በአማን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል

ዝግ አባባል

ወረዱ ዮም ወረዱ ዮም /፪ጊዜ/
ይትቀበሉከ በብሂል ወረዱ ዮም /፪ጊዜ/

አማን በአማን
ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል


ከዚ በኃላ በጽፋት ፦
ግሩማን መላእክት ሱራፌል ወኪሩቤል፤ እለ አክናፊሆሙ ነበልባል፤ ወረዱ ዮም ይትቀበሉከ በብሂል፤ አማን፤ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል።

ወረቡ እዚጋ ይባላል፦
''ግሩማን መላእክት''/፪/ ሱራፌል ወኪሩቤል እለ አክናፊሆሙ ነበልባል/፪/
ወረዱ ዮም ይትቀበሉከ በብሂል አማን ገብረ ህይወት/፪/

በቁም አባባል፦
አማን በአማን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል

ቁም- አይሁድ በህጋቸው አርባ ሲገርፉት ረጋ ብለው መጀመራቸውን ያመለክታል

እስመ ለዓለሙን በቁም በመረግድ እንዲሁም በጽፋት ይሉትና ወረቡን አንስተው ስርዓቱን ይፈጽማሉ

@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5


አመ ፭ሱ ለመጋቢት ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሥርዓተ ማህሌት

የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።

መልክአ ሥላሴ፦
ሰላም ለሕፅንክሙ ምርፋቀ ጻድቃን አግብርቲሁ፤ ማያተ ኢያሱ ሥላሴ እለ ትውኅዙ እምሕሊናሁ፤ እንዘ በአፍአሁ አንትሙ ወአንትሙ በውሣጤሁ፤ ኢነጸረ ኀበ ሐይመት ከመ አብርሃም አቡሁ፤ ወመስኮተ ነቢይ ዳንኤል ኢፈቀደ ያርኁ።

ዚቅ
ላህም መግዝዕ ተጠብሐ፤ ጽዋዓ መድኃኒት ተቶስሐ፤ አግብርት አግብርት አግብርት ይረፍቁ፤ ውስተ ሕፅኑ ለመርዓዊ፡፡

መልክአ ሚካኤል
ሰላም ለሕፅንከ እንተ በዲቤሁ ሕቁፍ፤ ጸሎተ ቅዱሳን ውኩፍ፤ ሚካኤል ክቡር መስፍነ ትጉሃን አእላፍ፤ ለረዲኦትየ ከመ ዘይሠርር ዖፍ፤ እንዘ ትሠርር ነዓ በ፪ኤ አክናፍ።

ዚቅ
ወይሁቦ ጸሎቶ ለዘጸለየ፤ ወባረከ ዓመተ ጻድቃኑ፡፡

ዘጣዕሙ፦
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።

ዚቅ
አመ ኖኅ ይእቲ መድኃኒት፤ እንተ ኮነት አንቀጸ ሕይወት ማርያም ቅድስት።


ዚቅ(ሌላ)
ማርያም ቤዛ ብዙኃን፤ ሕይወተ ኮነት ለኲሉ ዓለም፤ ፍሥሐነ ለእለ አመነ፡፡

መልክአ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘኆኅያቲሁ ቅሩጽ፤ ኀበ ዓምደ ብርሃን ጽዱል ወአኮ ዘዕፅ፤ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ኃያል ሠዋቄ ትንቱናን እምዳኅፅ፤ ለዝክረ ስምከ ሠናየ ዜና ወድምፅ፤ ትሴብሕ ኢትዮጵያ ወትዜምር ግብፅ።

ዚቅ
አባ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዘይሠርር በአክናፍ ከመ አዕዋፍ፤ ኀበ ዓምደ ወርቅ ስሙ ጽሑፍ፡፡

ወረብ
ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዘይሠርር በአክናፍ/፪/
'ኀበ ዓምደ ወርቅ'/፪/ ስሙ ጽሑፍ/፪/

መልክአ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
ሰላም ለከናፍሪከ ወለአፉከ ሰላም፤ ዓቃቤ ሥርዓት ዘሤመ ወማዕፆ ሕግ ዘዓቅም፤ ገብረ መንፈስ ቅዱስ መነኮስ በምግባረ ሠናይ ፍጹም፤ እንበለ መብልዕ ወስቴ እንዘ ትትጋደል በጾም፤ ነጺራ ትዕግሥተከ አንከረት ገዳም፡፡

ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ በንጹሕ ዘፆመ፤ በከናፍሪሁ ማዕፆ ዘሤመ፤ ሐዳስ ይትዋረስ ዓለመ።

ወረብ
ሃሌ ሃሌ ሉያ በንጹሕ ዘፆመ በከናፍሪሁ ማዕፆ ዘሤመ/፪/
ሐዳስ ይትዋረስ ዓለመ/፬/

መልክአ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
ሰላም ለከርሥከ ዘተሴሰየ ኅብስተ፤ አኮ ኅብስተ ምድራዌ እንተ ያመጽዕ ሐኬተ፤ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ኲሉ ይንዕዱከ ከሡተ፤ ብርሃነ ለዕውራን ወለሐንካሣን ፍኖተ፤ ወለበሐማን ቃለ ዘኮንኮሙ አንተ፡፡

ዚቅ
ኦ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አኮ ኅብስተ ምድራዌ ዘተሴሰይከ፤ አላ ኅብስተ ሰማያዌ እምሰማየ ሰማያት ዘበስለ፤ ኦ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አኮ ስቴ ምድራዌ ዘሰተይከ፤ አላ ስቴ ሰማያዌ እምሰማየ  ሰማያት ዘተቀድሐ።

ወረብ
ኦ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አኮ ዘተሴሰይከ ኅብስተ ምድራዌ ኅብስተ/፪/
አላ ኅብስተ ሰማያዌ እምሰማየ ሰማያት/፪/

መልክአ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
ሰላም ለጸአተ ነፍስከ እንተ ረሰየ ህላዌ፤ ኀበ ኢሰማዕ ቦቱ ዜና ሞት ወዝክረ ደዌ፤ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አንተ ዘገዳማውያን ሠርዌ፤ ወረዱ ጊዜ ሞትከ ዑፁፋነ ፅዱል ሥርጋዌ፤ ከመ ይትቀበሉ ኪያከ መርዓዌ፡፡

ዚቅ
ወወጽአት መንፈሱ ሶቤሃ፤ ወተቀበልዎ መላእክት በስብሐት ወበማኅሌት፤ እንዘ ይብሉ ሃሌ ሉያ፤ ወአብዕዎ ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ፡፡

ወረብ
ወተቀበልዎ መላእክት በስብሐት ወበማኅሌት/፪/
ወአብዕዎ ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ አብዕዎ ለገብረ ሕይወት/፪/

መልክአ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
ሰላም ለበድነ ሥጋከ ብርሃነ ሰማይ ዘአገቶ፤ እለ ያዕቆብ ወዮሴፍ እስከነ ፈርሁ ቀሪበቶ፤ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ባዕል ለብዕለ ጸጋከ ዘያስተቶ፤ ኃያል ብእሲ ይንሣእ ሢመቶ፤ ወበዓለ ዕዳ ይበርብር ንዋዮ ወቤቶ፡፡

ዚቅ
ፀሐይ ፀሐይ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ፀሐይ፤ ዘያበርህ ስኑ በውስተ ቀላይ፤ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ ዘባረኮ አግዚእ አዶናይ።

መልክአ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
ሰላም መቃብሪከ ዘኢተከሥተ ለባዕድ፤ ከመ መቃብሩ ለሙሴ ወልደ ዮካብድ፤ ዜና መቃብርከሰ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጸማድ፤ ቦ ዘይቤ በኢየሩሳሌም ዓፀድ፤ ወቦ ዘይቤ ሀለወ በከብድ፡፡

ዚቅ
ወረደ ብርሃን ኀበ መቃብሩ ለብእሴ እግዚአብሔር፤ ወኮነ መቃብሩ ዘየሐዩ ዱያነ፤ ጸሎቱ ለገብረ መንፈስ ቅዱስ ወበረከቱ የሃሉ ምስሌነ፡፡

ወረብ፦
ወረደ ብርሃን ወረደ ብርሃን  ኀበ መቃብሩ ለብእሴ እግዚአብሔር፤
ወኮነ መቃብሩ ዘየሐዩ ዱያነ ጸሎቱ ለገብረ ህይወት፤

ዓዲ (ወይም)
ዚቅ፦
አባ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዘእግዚአብሔር ገብር በእደ መላእክት ቅቡር፤ በኢየሩሳሌም ሀገር፤ ኀበ ኢይበጽሕ ሰብእ በእግር፤ እንበለ ዳዕሙ ዖፍ ዘይሠርር።

ምልጣን፦
ግሩማን መላእክት ሱራፌል ወኪሩቤል፤ እለ አክናፊሆሙ ነበልባል፤ ወረዱ ዮም ይትቀበሉከ በብሂል፤ አማን፤ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል።

አመላለስ
'አማን በአማን'/፪/ ገብረ መንፈስ ቅዱስ 'አማን በአማን'/፪//፩/
ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል/፬/

ወረብ
'ግሩማን መላእክት'/፪/ ሱራፌል ወኪሩቤል እለ አክናፊሆሙ ነበልባል/፪/
ወረዱ ዮም ይትቀበሉከ በብሂል አማን ገብረ ህይወት/፪/

እስመ ለዓለም
ይትፌስሑ በኀበ አልቦቱ ሞት፤ይነሥኡ እሴቶሙ፤እስመ ትዕግሥት ተውህበ ሎሙ ከመ ይንሥኡ፤ብዙኅ ሕማሙ ለጻድቃን፤ ወእምኵሉ ያድኅኖሙ እግዚአብሔር፤ወየዓቅብ ነፍሳቲሆሙ፤እስመ እንዘ ይነብሩ ውስተ ዓለም እለ ሎቱ ተቀንዩ በሕይወቶሙ ፤(ማንሻ-) ከመ ይንሥኡ አስበ ስብሐቶሙ፤ አክሊል ንጹሕ ዲበ ርእሶሙ

@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5


አመ ፭ሱ ለመጋቢት ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሥርዓተ ዋዜማ

ሃሌ ሉያ-
አባ አባ ክቡር ገብረ መንፈስ ቅዱስ ክቡር፤ ብእሴ እግዚአብሔር፤ ተሰምዓ ዜናከ ውስተ ኲሉ ምድር፤ ድርገተ ኮንከ እንተ ላዕለ ኃይል፤ አባ፤ ጸሊ በእንቲአነ።

ምልጣን
ተሰምዓ ዜናከ ውስተ ኲሉ ምድር፤ ድርገተ ኮንከ እንተ ላዕለ ኃይል፤ አባ ጸሊ በእንቲአነ፤ አባ ጸሊ በእንቲአነ።

አመላለስ፦
አባ ጸሊ በእንቲአነ፤(2)
አባ ጸሊ ጸሊ በእንቲአነ፤(4)

💠ለእግዚአብሔር ምድር በምልዓ
አባ ጸሊ በእንቲአነ፤ ጸሎትከ ወትረ ይብጽሐነ፤ አባ ጸሊ በእንቲአነ።

💠እግዚአብሔር ነግሠ፦

ወረደ ብርሃን ኀበ መቃብሩ ለብእሴ እግዚአብሔር፤ ወኮነ መቃብሩ ዘየሐዩ ዱያነ፤ ጸሎቱ ለገብረ መንፈስ ቅዱስ ወበረከቱ የሃሉ ምስሌነ።

💠ይትባረክ፦
ኪያከ መሠረት አንተ ብነ፤ አባ ጸሊ በእንቲአነ፤ እስመ ጸሎተ ጻድቅ ይሰምዕ እግዚአብሔር።

  💠ሰላም፦
አበው ቅዱሳን እለ ደብር ወገዳም፤ አስተምህሩ ለነ፤ ነሃሉ ወትረ በሰላም።

💠አመላለስ፦
እለ ደብር ወገዳም እለ ደብር ወገዳም/፪/
አስተምህሩ ለነ ነሃሉ ወትረ በሰላም/፬/

ዓዲ (ወይም)
💠ሰላም
አበው ቅዱሳን ዔሉ ውስተ አድባር ወበዓታት፤ አዕረፉ በክብር ወበብዙኅ ሰላም።

💠አመላለስ፦
አበው ቅዱሳን ዔሉ ውስተ አድባር ወበዓታት/፪/
አዕረፉ በክብር ወበብዙኅ ሰላም/፪/

@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

4 784

obunachilar
Kanal statistikasi