Ibnu Hashim(امير هاشم)


Kanal geosi va tili: ko‘rsatilmagan, ko‘rsatilmagan
Toifa: ko‘rsatilmagan


"ألا لستُ للفردوسِ أهلا ولا أقوى على نار الجحيم فهبْ لي توبة واغفر ذنوبي فإنك غافر الذنب الأغامي"!!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
ko‘rsatilmagan, ko‘rsatilmagan
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ተጋበዙልኝ መልካም ለይል....!

=
@IbnuHashm


በነገራችን ላይ በአሁኑ ጊዜ ከአረበኛ ቀጥሎ እንግሊዘኛ ቋንቋ ማወቅ በጣም ይጠቅማል ይህንን የቋንቋ ትምህርት ቤት promotion ስሰራ እኔ እራሴዉ ሂጄ ነዉ promotion ልስራላችሁ ያልኳቸዉ ምክንያቱም አብዘሀኞቻችሁ እዚህ ቻናሌ ላይ ያላችሁ ቤተሰቦቼ እንግሊዘኛ ቋንቋ መናገር አትችሉም። ይህንንም በማሰብ እኔ እዚህ የምኖርበት ከተማ ላይ top የሚባሉ የቋንቋ ትምህርት ቤቶችን አጣርቼ አሪፍ የሚባለዉን Azela የቋንቋ ትምህርት ቤት መረጥኩ። ከዛ ሂጄ ዋና ማናጀሩን በonline እንዲያስተምራችሁ አናገርኩት እሱም በደስታ እሺ አለኝ።

አዜላ የቋንቋ ትምህርት ቤት ከ10 አመት በላይ በጣም ልምድ ባላቸዉ መምህራኖች ነዉ ቋንቋ የሚያስተምረዉ። እኔ ራሴዉ የእንግሊዘኛ ቋንቋ ያዳበርኩት በዚሁ ትምህርት ቤት ነዉ። ብታምኑም ባታምኑም አንድ ሰዉ አዜላ የቋንቋ ትምህርተ ቤት ገብቶ እንግሊዘኛ መልመድ ሳይሆን እንግሊዘኛ ማዉራት ችሎ ነዉ የሚወጣዉ። ይህ የትምህርት ቤቱ ህግ ነዉ!

እናንተ በ10 አመት እና በ12 አመት Normal(መደበኛ) ትምህርት ቤት እየተማራችሁ ያልቻላችሁትን ቋንቋ አዜላዎች በ10 ወር ኮርስ እንግሊዘኛ መልመድ ሳይሆን እንግሊዝኛ ማዉራት እንድትችሉ ያደርጋሉ። ይቺን የ10 ወር ኮርስ በደንብ ከተከታተላችሁ እመኑኝ ትለወጣላችሁ። ከ10 ወር ቡኋላ ካልተለወጣችሁ እኔን መጣችሁ ዉቀሱኝ እዉነቴን ነዉ።

በጣም ደስ ያለኝ ነገር ደግሞ ለእህቶቻችን ሸሪዐን ባማከለ መልኩ ፊታቸዉ ማሳየት የማይፈልጉ በድምፅ ብቻ በመግባት የሚሰጡትን ሁሉንም ኮርስ መከታተል ይችላሉ። ማንበብ የማይችሉ ሰዎች ለብቻቸዉ መማር ይችላሉ ከa,b,c,d ጀምረዉ ይማራሉ።ለያንዳንዱ ትምህርት Hand Out እና module ተዘጋጅቷል

በማይታመን ዋጋ እናንተን ለማስተማር ዝግጅቱን አጠናቆ እየጠበቃችሁ ነዉ። ይህንን ዕድል ተጠቀሙበት
ለመመዝገብ 👉 @habib_azela

ለትርፍ ሳይሆን እናንተ እንድትለወጡ ነዉ አላማችን። በእኔ ቻናል ስም ቀድመዉ ለሚመጡ 10 ሰዎች 10% ክፍያ እንቀንስላቸዋለን ብለዋል።

t.me/IbnuHashm


Azela Language Schools

አስደሳች ዜና ከአዜላ የቋንቋ ትምህርት ቤት ጊዜ ተቀይሯል ራስን ማሻሻል እና ማብቃት እንደ ድሮ አይከብድም ብሩህ ነገን ለሚሹ ቆራጥ ሰዎች አማራጮች ሞልተዋል። የረዥም አመታት ልምድ ባላቸዉ አስተማሪዎች እንግሊዝኛ ቋንቋ ባሉበት ቦታ ሆነው በስልክ ወይም ኮምፕዩተር መማር የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ኦንላይን ክላስ በቪዲዮ ኮል ማስተማር መጀመራችንን ስንገልፅ በደስታ ነው።

እንግሊዘኛ ቋንቋን እቤትዎ ሁነዉ በ Online ለመልመድም ይሁን ለመለማመድ
> በሳምንት ለ3 ቀን
> ለ1 ሰዓት ከጠዋት፣ ከሰዓትና ማታ በሚመችዎ ሰዐት መማር ይችላሉ

የምናስተምረዉ ትምህርቶች
* Speaking
* Grammar
* Reading
* Writing

እቤትዎ ሁነዉ በአጭር ጊዜ ይማሩ ይለወጡ!
Azela Language School

ለመመዝገብ👇
@habib_azela


أعوذ بالله من الشيطان الرجيم
                                   
ዛሬ ኢንሻአሏህ ሱረቱል ኒሳእ እንቅራ

📔ከቁጥር - 106-121
📔ምዕራፍ - 4
📔ገፅ - 96-97

t.me/IbnuHashm


ዘካ ማውጣት

ዘካ በገንዘብ ዉስጥ ግዴታ ስትሆን ወዲያው ፈጥኖ መከፍል ዋጂብ ይሆናል፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ''ዘካን ስጡ" ይላልና፡፡ ያልተገደበ ትእዛዝ ወዲያው መፈፀም እንዳለበት ያሳያል፡፡ የድሃው ፍላጎትም ፈጥኖ እንዲከፈለው ያስገድዳልና፡፡ ማዘግየቱ ድሃውን መጉዳት ነው፡፡ ዘካ ዋጂብ የሆነበት ሰው እንደ መክሰር፣ መሞትና የመሳሰሉት ድንገተኛ እንቅፋቶች ሊያጋጥሙትና ዘካው በራሱ ጫንቃ ላይ እንዲቀር ምክንያት ሊሆኑም ይችላሉ፡፡ ፈጥኖ ማውጣት ከስስታምነት መራቅ ነው፤ ጫንቃንም ንጹህ ማድረግ ነው፡፡ አስገዳጅ ሁኔታ (ደሩራ) ከሌለ በስተቀር ወይም ለሚበጅ ነገር (ለመስለሓ) በስተቀር፡፡ ለምሳሌ የበለጠ ችግር ላለበት ሰው ለመስጠት ቢያቆይ፣ ወይም ገንዘቡ በቦታው ባለመኖሩ፣ ወይም በራሱ ላይ ወይም በገንዘቡ ላይ አደጋ በመፍራትና ለመሳሰሉት ሁኔታዎች የሚቆይ ካልሆነ በስተቀር፡፡

ማስገንዘቢያ፡- በሕፃን ገንዘብና በእብድ ገንዘብ ላይ ዘካ ዋጂብ ነው፡፡ ማስረጃዎቹ ጥቅላዊ ስለሆኑ፡፡ በገንዘባቸው ላይ ኃላፊ የሆነ ሰው ዘካውን ከነሱ ላይ ያወጣል፡፡ ይህ በነሱ ላይ ዋጂብ የሆነ ሐቅ ስለሆነ ዉክልና ይገባበታል፡፡

ማስገንዘቢያ፡- በኒይ-ያ እንጂ ዘካን ማውጣት አይቻልም፡፡ ነቢዩ ﷺ “ሥራዎች (የሚመዘኑት) በኒይ-ያዎቻቸው ነው” ብለዋልና - ሙት-ተፈቁን ዐለይህ፡፡

ዘካውን ባለገንዘቡ ራሱ ቢያከፋፍለው ይሻላል፡፡ ተገቢ ለሆኑ ሰዎች መድረሱን እርግጠኛ ለመሆን፡፡ ከሱ ላይ የሚያወጣለትን ሰው መወከልም ይችላል፡፡ የሙስሊሞች መሪ (ኢማም) ዘካውን ሰብስቦ ለማከፋፈል ከፈለገ ለሱ ይሰጣል:: ወይም ኢማሙ ልኮት ዘካ ለሚሰበስበው ሰው ይሰጣል፡፡

ዘካ በሚከፈልበት ጊዜ ከፋዩም ተቀባዩም ዱዓ ቢያደርጉ ይወደዳል፡፡ አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፡- خُدْ مِنْ أَمْوَالِهِمْ صَدَقَةً تُطَهِّرُهُمْ وَتُزَكِّيهِمْ بِهَا وَصَلَّ ''ከገንዘቦቻቸው በርሷ የምታጠራቸውና የምታፋፋቸው የሆነችን ምጽዋት ያዝ፤ ለነሱም ፀልይላቸው'' – (አት-ተውባ፡ 103)፡፡

ዐብደላህ ቢን አቢ አውፋ (ረ.ዐ) ''የአላህ መልክተኛ ﷺ ሰዎች ሰደቃቸውን (ዘካቸውን) ይዘው ሲመጡ ''አልላሁምመ ሰልሊ ዐለይሂም - አላህ ሆይ! በነሱ ላይ ሰላት (እዝነት) አውርድ'' ይሉ ነበር” ብሏል፡፡

ሰውየው ችግር ያለበት ከሆነና በዘልማዱ ዘካ ይወስድ የነበረ ከሆነ ይህ ዘካ ነው ብለው ሳይነግሩት ይሰጡታል - እንዳይከብደው፡፡ ችግር ያለበት ከሆነና በዘልማዱ ዘካ የማይቀበል ከሆነ ዘካ መሆኗን ይነግሩታል፡፡

ዘካን ወደ ሌላ ቦታ ስለመውሰድ፡- በላጩ ሁሉንም ዘካተል-ማል በአገሩ ዉስጥ ማውጣት ነው፡፡ ገንዘቡ ባለበት አገር ዉስጥ ለሚገኙ ድሆች ማከፋፈል፡፡ በሸሪዓው ተቀባይነት ላለው ምክንያት ዘካን ወደ ሌላ አገር መውሰድ ይቻላል፡፡ ለምሳሌ በሌላ አገር ዉስጥ ችግርተኛ የሆኑ ዘመዶች ካሉት፤ ወይም ደግሞ ገንዘቡ ከሚገኝበት አገር ውስጥ ካሉት ሰዎች የበለጠ ሌሎቹ ችግርተኛ ከሆኑ፡፡ ሰደቃዎች (ዘካዎች) ከሌላ አገር ወደ ነቢዩ ﷺ ተወስደው ነቢዩ ﷺ ለሙሃጂሮችና ለአንሳር ድሆች ያከፋፍሉ ነበርና፡፡

ዘካን አስቀድሞ መክፈል፡- ዘካን ዋጂብ ከመሆኗ በፊት ለሁለት ዓመት ወይም ከዚያ ላነሰ ጊዜ አስቀድሞ መክፈል ይቻላል፡፡ አሕመድና አቡዳዉድ እንደዘገቡት ነቢዩ ﷺ ከዐብ-ባስ የሁለት ዓመት ሰደቃ (ዘካ) አስቀድመው ተቀብለዋቸዋልና፡፡ ዋጂብ የሚሆንበት ምክንያት (ሰበብ) ከተገኘ ዘካን ዋጂብ ከመሆኗ በፊት አስቀድሞ መክፈል ይቻላል፡፡ የእንስሳት ዘካም ይሁን የእህል ወይም የሁለቱ ገንዘቦች ወይም የሸቀጥ እቃዎች ኒሳብ ከሞላ አስቀድሞ መክፈል ይቻላል፡፡

t.me/IbnuHashm




ዘካቱል-ፊጥር

ዘካቱል-ፊጥር የተባለችው ረመዷንን በመፍታት ወይም በማፍጠር የሚወጣ ዘካ ስለሆነ ነው፡፡ ዋጂብ ለመሆኗ ማስረጃዋ አላህ (ሱ.ወ)قَدْ أَفْلَحَ مَن تَزَكَّىٰ የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡(አል-አዕላ 14) ሰዒድ ቢን አል- ሙሰይብ እና ዑመር ቢን ዐብዱልዐዚዝ “እዚህ መጥራራት ማለት የተፈለገው ዘካቱል-ፊጥርን ማውጣት ነው” ብለዋል፡፡ وآتوا  الزكا“ዘካን ስጡ" በሚለው ጥቅላዊ የአላህ ቃል ዉስጥም ይገባል፡፡

በሰሒሐይንና በሌሎችም ዉስጥ እንደተዘገበው ኢብኑ ዑመር (ረ.ዐ) “የአላህ መልክተኛ ﷺ በሙስሊሞች - በባሪያውም ሆነ በነፃው፣ በሴቱም ሆነ በወንዱ፣ በትንሹም ሆነ በትልቁ ላይ ዘካተል-ፊጥርን አንድ ሳዕ ስንዴ ወይም አንድ ሳዕ ገብስ መስጠት ግዴታ አደረጉ፡፡” ብሏል፡፡

ዘካቱል-ፊጥር ዋጂብ መሆኗን ሙስሊሞች ኢጅማዕ ያደረጉበት መሆኑን ዑለሞች አወስተዋል፡፡

የመደንገጓ ጥበብ፡- ለጾመኛው በጾሙ ጊዜ ከሚከሰቱ አልባሌ ንግግሮችና አላስፈላጊ ነገሮች የሚያጠራው ሲሆን ለሚስኪኖችም ምግብ እንዲሁም የጾምን ግዴታ በመፈፀም ላይ ለአላህ ምስጋና ማቅረብ ነው፡፡

ማስገንዘቢያ፡- ዘካቱል-ፊጥር በሁሉም ሙስሊም ወንድም ሆነ ሴት፣ ትንሽም ሆነ ትልቅ፣ ነፃም ሆነ ባሪያ ላይ ዋጂብ ነው - ቀደም ሲል የተጠቀሰው የኢብኑ ዑመር ሐዲሥ ይህንኑ ያረጋግጣልና፡፡ በሐዲሡ ዉስጥ የአላህ መልክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) በሙስሊሞች - በባሪያውም ሆነ በነፃው፣ በሴቱም ሆነ በወንዱ፣ በትንሹም ሆነ በትልቁ ላይ ዘካተል ፊጥርን መስጠት ፈርድ ወይም ግዴታ እንዳደረጉ ይገልጻል፡፡

ማስገንዘቢያ፡- ሁሉም ሰው የሚሰጠው መጠን አንድ ሳዕ ነው፡፡ እሱም አራት ሙድ ወይም ሁለት ኪሎ ከአራት መቶ ግራም ነው፡፡

ዘካተል-ፊጥር ዋጂብ የሚሆንባቸው ነገሮች፡-

ዘካቱል-ፊጥር የሚወጣው ባገሩ ባብዛኛው ጥቅም ላይ ከሚውል የቀለብ ዓይነት ነው - ስንዴም ይሁን ገብስ ወይም ቴምር ወይም ከነዚህ ሌላ የአካባቢው ሰው ባብዛኛው ለምግብነት የሚጠቀምበት ነገር እንደ ሩዝ፣ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ሥጋ፣ እና ሰው እንደየአገሩ ለምግብነት የሚጠቀምበት ነገር ነው፡፡

የዘካተል ፊጥር መክፈያ ጊዜ:-

ከዒድ ቀን በፊት በአንድ ወይም በሁለት ቀን አስቀድሞ መክፈል ይቻላል፡፡ ሰሓቦች ከዒድ አል-ፊጥር በፊት በአንድ ወይም በሁለት ቀን አስቀድመው ይሰጡ እንደነበር ቡኻሪ ዘግቧል፡፡ በዒድ ቀን ከሰላት በፊት ማውጣት በላጭ ነው፡፡ ይህ ወቅት ካመለጠውና ያለዑዝር ማውጣቱን ከዒድ ሰላት ካዘገየው ወንጀለኛ ይሆናል ቀዷ ማውጣትም አይችልም፡፡ ያቆየው በዑዝር ከሆነ ለምሳሌ ረስቶ ወይም የሚያወጣን ሰው ወክሎ ተወካዩ ካላወጣ በቀዷ መልክ ማውጣት ዋጂብ ይሆንበታል፡፡ ኢብኑ ዐብ-ባስ (ረ.ዐ) ባስተላለፉት ሐዲሥ “ከሰላት በፊት የሰጣት ሰው እሷ ተቀባይነት ያለት ዘካ ነች፡፡ ከሶለት በኋላ የሰጣት ሰው ደግሞ እሷ ከሰደቃኞች አንዷ ናት” ብለዋል - አቡዳዉድ፣ ኢብኑ ማጃ፣ እና አል-ሓኪም የዘገቡት ሲሆን እል-ሓኪም ሰሒሕ ነው ብሎታል፡፡

ግምቱን መከፈል፡- የዘካተል-ፊጥርን ግምት በገንዘብ (በብር) መክፈል አይበቃም፡፡ ከነቢዩም ﷺ ሆነ ከሰሓቦች ከአንዳቸውም የዘካቱል-ፊጥርን ግምት በገንዘብ ማውጣታቸው አልተዘገበምና፡፡ ነቢዩ ﷺ ግዴታ ያደረጉትም አምድ ሳዕ ምግብ (እህል) ነው፡፡

ሰደቀቱል-ፊጥር ለማውጣት በተወሰነው ጊዜ ውስጥ ወደ ባለመብቷ መድረስ ይኖርባታል፡፡ ወይም ደግሞ ባለመብቱን ወከሎ ለሚቀበል ወኪል መድረስ ይኖርባታል፡፡ ከፋዩ በተወሰነው ጊዜ ዉስጥ ሊሰጠው ያሰበውን ሰው ወይም ወኪሉን ካላገኘ ለሌላ ሰው መስጠት ዋጂብ ይሆንበታል፡፡
ወሏሁ አዕለም

t.me/IbnuHashm




ቢሆን ጥሩ ነበር፣ ካልሆነ ግን . . .

ቢሆን ጥሩ ነበር፣ ካልሆነ ግን ሌላ መንገድ አለ! ሌላ ሕይወት አለ! ሌላ አቅጣጫ አለ! ሌላ አማራጭ አለ!

•  እውነት ነው፣ ተምሬ ቢሆን ኖሮ ጥሩ ነበር . . . የመማሩን እድል ካላገኘሁ ግን ሕይወትን ውብ የሚያደርጉ ሌሎች ብዙ አማራጮች አሉ፡፡
•  እውነት ነው፣ ትዳሬ በሰላም ቀጥሎ ቢሆንና ባይፈርስ ጥሩ ነበር . . . አንዴ ከሆነና ሁኔታውን በፍጹም ማደስ ካልቻልኩ ግን የተዝረከረከውን ሕይወቴን አፋፍሼ፣ ሰብስቤና እንደገና አደራጅቼ በአዲስ መልኩ ሕይወት ይቀጥላል፡፡
•  እውነት ነው፣ የምወደው ስራ ቢኖረኝ ኖሮ ጥሩ ነበር . . . ሁኔታው ያንን ለማግኘት ካልፈቀደልኝ ግን ባለኝና ካለሁበት በመነሳት የማድግበትን መንገድ የመፈለግ መነሳሳቱ አለኝ፡፡ 

በአጭሩ፣ ሕይወት እኔ እንደምፈልጋት ብትሆን ጥሩ ነበር፣ ካልሆነ ግን ለምን አልሆነም ብዬ ደብሮኝ አልውልም፡፡ ቀና እላለሁ! ብርቱ ሰው ለመሆን እወስናለሁ! ስብር አልልም! አልደካክምም!

መልካም ቀን!

t.me/IbnuHashm


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ቁርአን የልብ ብርሀን!!

@IbnuHashm


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ተጋበዙልኝ መልካም ለይል....!

=
@IbnuHashm


እንደ ወንድምነት አንድ ምክር ልምከራችሁ:- ለሁሉም ነገር መልስ አይሰጥም ለሁሉም ነገር መልስ አትስጡ ስቃችሁ ማለፍ ልመዱ። ስማችሁን ቢያጠፉት፣ ቢበድሏችሁ፣ የእናንተ ያልሆነ ስም ቢሰጧችሁ፣ ቢከዷችሁ ወ.ዘ.ተ እየከፋችሁም ቢሆን ስቃችሁ ፈገግ ብላችሁ እለፉት!!

ዝምታ ከመልስም በላይ መልስ ነዉ!!

t.me/IbnuHashm


አሏህንና መልዕክተኛዉን መከተል!

የነብዩ ﷺ ሱና መያዛችን የግድ ነዉ። የሳቸዉን ፈለግ አርዐያ አድርገንም መከተል የግድ ነዉ። ስለዚህ ነብዩ ﷺ ይዘዉ የመጡትን መንገድ በትክክል፣ በአግባብ፣ በኢኽላስ አሏሁ አዘልወጀል ፈርተን ልክ እሳቸዉ ባመጡት አይነት መስመር ላይ መጓዝ የግድ ይለናል። ምክንያቱም የአሏሁ ሱብሀነሁ ወተዐላ ትዕዛዝ ነዉ። የነብዩም ትዕዛዝ ነዉ።
አሏህ እንዲህ ይላል:-

وَمَا آتَاكُمُ الرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَاكُمْ عَنْهُ فَانتَهُوا ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۖ إِنَّ اللَّهَ شَدِيدُ الْعِقَابِ

መልክተኛውም የሰጣችሁን (ማንኛውንም) ነገር ያዙት፡፡ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና፡፡(59:7) ምንም እንኳን ይህ አንቀፅ አገባቡ ረሱል ﷺ እና ሶሀባዎች ካለ ምንም ጦርነት ያገኙትን ገንዘብ በተመለከተ ቢሆንም መልዕክቱ ሁሉንም የሸሪዐ ጉዳይ እንደሚያካትት ዑለማዎች ሁሉ ይስማማሉ። መልዕክተኛዉ ﷺ የሰጧችሁን ያዙ ተቀበሉ አሳምራችሁም ያዙት እንዲሁም ደግሞ የከለከሏችሁን ተከልከሉ ይላል አሏህን ፍሩ።

ያዘዙንን እንድንታዘዝ የከለከሉንን ለመከልከል አሏህን መፍራት ያስፈልጋል። አሏህን ካልፈራን እና ተቃራኒዉ ከሆነ ግን የአሏህ ቅጣት ብርቱ መሆኑን ማወቅ አለብን። ''አሏህ ቅጣቱ ብርቱ ነዉ'' ይላል።

መልዕክተኛውን ﷺ መከተል አሏህ እንዳለዉ ''እሳቸዉን የምትታዘዙ የምትከተሉ ከሆነ ቀናዉ መንገድ የተመራችሁና የቀናችሁ ትሆናላችሁ'' ይላል። አሏህ አዘልወጀል ለመዉደዳችን እሱ እኛን ለመዉደዱ ምልክት መለኪያ ሚዛን ያደረገዉ አሏህን እና መልዕክተኛዉን ﷺ መከተል ነዉ።

አሏህ እንዲህ ይላል:- ''እንዲህ በላቸዉ መልዕክተኛዪ ሆይ! እዉነት አሏህን የምትወዱት ከሆነ እኔን ተከተሉኝ በላቸዉ''። ዉጤቱ ምን ይሆናል? አሏህ ይወዳቹሀል።

አሏህ እኛን ለመዉደዱ እኛም እሱን ለመዉደዳችን መለኪያዉ ምንድን ነዉ ከተባለ? የነብዩን ﷺ ሱና መከተላችን ነዉ። የሳቸዉን ፈለግ መከተል ነዉ። የሳቸዉን እምነት መከተላችን ነዉ። የሰሩትን በመስራት፤ የከለከሉትን በመተዉ፤ የተናገሩትን በመናገር፤ ያልተናገሩትን በመተዉ፤ ያመኑትን ትክክለኛ እምነት በመቀበል ያላመኑትን የተቃወሙትን በመተዉ ነዉ።

ወዳጆቼ እኛ የነብዩን ﷺ ሱና በተከተልን መጠንና ልክ አሏህ እንደሚወደንና ለአሏህ ያለን ዉዴታ የላቀ መሆኑን ማወቅ እንችላለን።

t.me/IbnuHashm


أعوذ بالله من الشيطان الرجيم
                                   
ዛሬ ኢንሻአሏህ ሱረቱል ኒሳእ እንቅራ

📔ከቁጥር - 95-105
📔ምዕራፍ - 4
📔ገፅ - 94-95

t.me/IbnuHashm


ከሸቀጥ ዕቃዎች የሚወጣ ዘካ

የሸቀጥ ዕቃዎች ማለት ትርፍ ለማግኘት ለሽያጭ የተዘጋጁ ዕቃዎች ናቸው:: ከሸቀጥ ዕቃዎች ዘካ ማውጣት ዋጂብ ለመሆኑ ማስረጃው አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፡-

خُذْ مِنْ أَمْوَالِهِمْ صَدَقَةً تُطَهِّرُهُمْ وَتُزَكِّيهِم بِهَا

ከገንዘቦቻቸው ስትኾን በእርሷ የምታጠራቸውና የምታፋፋቸው የኾነችን ምጽዋት ያዝ።(አት-ተዉባ 103)

وَالَّذِينَ فِي أَمْوَالِهِمْ حَقٌّ مَّعْلُومٌ,لِّلسَّائِلِ وَالْمَحْرُومِ

እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት። ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡(አል-መዓሪጅ 24-25)። አብዛኛው ገንዘብ የሸቀጥ እቃ ስለሆነ በአንቀጹ ጥቅላዊ ትርጓሜ ዉስጥ ይገባል፡፡ ይህ ከሰሓቦችም ተዘግቧል፡፡

ሸይኹልኢስላም ኢብኑ ተይሚያ “አራቱ ኢማሞችና ሌላውም ኡመት - ጥቂት ያፈነገጠ ሰው ሲቀር - ዘካ ከሸቀጥ እቃ እንደሚወጣ ተስማምተዋል” ብለዋል፡፡

ከሸቀጥ እቃዎች ዘካ ማውጣት ዋጂብ የሚሆነው በሚከተሉት ሸርጦች ነው:-

1) እቃዎቹ ከሁለቱ ገንዘቦች ማለትም ከወርቅና ከብር ባንዱ ተገምተው ኒሳብ መሙላት።

2) አንድ ዓመት መሙላት - ለዚህም ማስረጃው ቀደም ሲል ተወስቷል፡፡ ነገር ግን በገንዘብ ወይም በሸቀጥ ኒሳብ ግምቱ ኒሳብ የሚሞላ ሸቀጥ ከገዛ የሚታሰበው የገዛበት ገንዘብ ዓመት ነው [እንጂ የተገዛው እቃ ከተገዛበት ቀን ጀምሮ ዓመት እንዲሞላ አይጠበቅም]።

ማስገንዘቢያ፡- የሸቀጥ እቃዎች ዘካ አወጣጥ፡- ዓመት ሲሞላቸው ከሁለቱ ገንዘቦች - ከወርቅና ከብር ባንዱ ይገመታሉ፡፡ በዚህ ላይ ለድሆች ይበልጥ የሚጠቅመው ግምት ይወሰዳል - (ከወርቅ ወይም ከብር ግምት)፡፡ ከሁለቱ ገንዘቦች ባንዱ ተገምቶ ግምቱ ኒሳብ ከሞላ የግምቱ አንድ አስረኛ ሩብ ይወጣል፡፡ የተገዛበት ገንዘብ መጠን ግምት ዉስጥ አይገባም፡፡ የሚታየው ዓመቱ ሲሞላ የተገመተበት የገንዘብ መጠን ነው፡፡ ለባለሸቀጡም ሆነ ለዘካ ተቀባዩ ፍትሃዊ የሚሆነው ይህ ነው፡፡

ዘካ የሚያወጣው ሙስሊም ባለሸቀጥ ከሸቀጡ ዘካ ሲያወጣ ሸቀጡን በትከክል መቁጠርና ስስታም የሆነ ሸሪክ ሸሪኩን በሚተሳሰበው ዓይነት ራሱን መተሳሰብ ዋጂብ ይሆንበታል፡፡ ያሉትን ሸቀጦች በሙሉ በዓይነታቸው መቁጠርና ፍትሃዊ የሆነ ግምት መገመት ይጠበቅበታል፡፡ ለምሳሌ የአንድ ሱቅ ባለቤት በሱቁ ዉስጥ በፓኬቶችና በዓይነቶች ተከፋፍለው ለሽያጭ የተዘጋጁትን ሁሉንም መቁጠር ይኖርበታል፡፡ ለሽያጭ የቀረቡ የተለያዩ ማሽኖች፣ የማሸኖችና የመኪናዎች መለዋወጫዎች ባለቤት በትክከል ይቆጥራቸውና በጅምላ የሚሸጥ ከሆነ በጅምላ ዋጋ በችርቻሮ የሚሸጥ ከሆነ በችርቻሮ ዋጋ ይገምታቸዋል፡፡

ማስገንዘቢያ፡- ለኪራይ የተዘጋጁ ቤቶችና መኪናዎች በራሳቸው ዉስጥ ዘካ የለባቸውም፡፡ ዘካ ማውጣት የሚወጅበው ባለቤቱ ከነዚህ ከሚያገኘው ኪራይ ዉስጥ ነው - ከኪራይ ዉሉ ቀን ጀምሮ ዓመት ከሞላው፡፡

ማስገንዘቢያ፡- መኖሪያ ቤቶችና (ለንግድ ሳይሆን) ለመጠቀም የተያዙ መኪናዎች ዘካ የለባቸውም፡፡ እንደዚያውም የቤት ቁሳቁሶች፣ የሱቅ ቁሳቁሶች፣ የነጋዴው መጠቀሚያ እቃዎች - እንደ መለኪያዎች፣ መስፈሪያዎች፣ ሚዛኖች፣ መያዣ እቃዎች እነዚህ ሁሉ ዘካ የለባቸውም - የሽያጭ እቃዎች አይደሉምና፡፡ አቡ ሁረይራ ባስተላለፉት ሐዲሥ ነብዩ ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም “አንድ ሙስሊም በባሪያውና በፈረሱ ዉስጥ ሰደቃ (ዘካ) የለበትም፡፡” ብለዋልና - ሙት-ተፈቁን ዐለይህ፡

ወሏሁ አዕለም

t.me/IbnuHashm




ከባድ የተባለው ሰንሰለት!

በአለም ላይ ለመበጠስ ከባድ የተባለው ሰንሰለት የብረት ሰንሰለት አይደለም የሰው-ለሰው ሰንሰለት ነው፡፡

1.  የቁሳቁስ ሰንሰለት

ከሰዎች ጋር በቁሳቁስና በገንዘብ ጥገኝነት ከተሳሰራችሁና የእነዚያን ሰዎች ድጎማ ካላገኛችሁና ከእነሱ ውጪ መኖር እንደማትችሉ በማሰብ መንቀሳቀስ ካልቻላችሁ ይህንን ሰንሰለት የቁሳቀሱ ሰንሰለት ብለን እንጠራዋለን፡፡

ለተወሰነ ጊዜ የሰዎችን ድጋፍ ማግኘት ችግር ባይኖረውም፣ ሃሳባችን የተያዘው ግን በራሳችን መቆም እንደማንችል በመፍራት ከሆነ ይህንን ሰንሰለት የመበጠስን እርምጃ ዛሬውኑ መጀመርና ቀስ በቀስ በራሳችን ወደመቆም እንድናድግ እንመከራለን፡፡

2.  የስሜት ሰንሰለት

ከሰዎች ጋር በስሜት ንክኪ ከተሳሰራችሁና ከእነሱ ውጪ በፍጹም ማሰብም ሆነ መኖር ካቃታችሁ ይህንን ሰንሰለት የስሜት ሰንሰለት ብለን እንጠራዋለን፡፡ ከተቃራኒ ጾታ ጋር በሀራም ፍቅር መተሳሰርም ሆነ ከአቻዎቻችን ጋር በጓደኝነት መቀራረብ ትክክለኛ ልምምድ ቢሆንም፣ እነዚህ ሰዎች ከእኛ ጋር ያላቸውን ትስስር ያቆሙ ጊዜ መኖር እስከሚያስጠላን ድረስ ቀውስ ውስጥ የምንገባ ከሆነ፣ ይህንን ሰንሰለት የመበጠስን እርምጃ ዛሬውኑ መጀመርና ቀስ በቀስ የትኩረት ለውጥ እንድናመጣ እንመከራለን፡፡

ከጌታችሁ ጋር ከቆማችሁ ሙሉ ሰው ናችሁ!!!

መልካም ቀን!

t.me/IbnuHashm


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ቁርአን የልብ ብርሀን!!

@IbnuHashm


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ተጋበዙልኝ መልካም ለይል....!

=
@IbnuHashm


6 ለሰዎች መናገር የሌለብህ እውነታዎች

አንድ መቼም ቢሆን እቅድህን ለማይመለከታቸው ሰዎች እንዳትናገር። በተሳሳተ አመለካከታቸው የተነሳ ወደሁዋላ ሊያስቀሩህ ይችላሉ።

ሁለት መቼም ቢሆን ድክመትህን በእርግጠኝነት ለማይረዱህ ሰዎች እንዳትናገር አንዳንዶች አንተን ለማጥቃት ሊጠቀሙበት ስለሚችሉ።

ሶስት መቼም ቢሆን ውድቀቶችህን ለማያነሱህ እንዳትናገር አንዳንድ ሰዎች ሁሌም የማትችል እንደሆንክ ሊያስቡ ይችላሉ።

አራት መቼም ቢሆን የወደፊት እቅድህን ደጋፊ ላልሆኑ ሰዎች እንዳትናገር። በጸጥታ ማድረግ ያለብህን አድርግ።  ውጤቱን ብቻ አሳያቸው።

አምስት መቼም ቢሆን ሚስጥርህን ለማትተማመንባቸው እንዳትናገር። ምንግዜም ጅሎች ብቻ ሚስጥራቸውን ያካፍላሉ።

ስድስት መቼም ቢሆን የገቢህን መጠን እና የገቢህን ምንጭ እንዳትናገር። ያ ጠላት ሊያፈራብህ ስለሚችል።

t.me/IbnuHashm

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.