Imamu ahmed tube


Kanal geosi va tili: ko‘rsatilmagan, ko‘rsatilmagan
Toifa: ko‘rsatilmagan


قال البخاري باب: العلم قبل قول والعمل
ኢማሙ ቡኻሪ አሉ: አውቀት ከስራም ከንግግርም ይቀደማል
ይህቻናል ዋና አላማ ትክክለኛ ሱሀቦች እና ነብዪ ሰዐወ የነበሩበትን እምነት ከሽርክ እና ከቢድአ የጠራውን እምነት የምንማማርበት ነው ።ኒያ እያረጋቹ በተቻላቹ መጠን ሌላም ሰው እንዲያውቅ አስተዋፅኦ አድርጉ አላህ ዘንድ የአጅር ተከፋይ ትሆናላቹ
t.me/aladebs

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
ko‘rsatilmagan, ko‘rsatilmagan
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri




1.   በመፃህፍት ማመን

በመፃሕፍት ማመን ከእስልምና መሰረታዊ እምነቶች ውስጥ ሶስተኛው ነው።

o  ማስረጃ፡

·       ከሓዲስ

 عَنْ عُمَرَ قَالَ: "... فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ... أَنْ تُؤْمِنَ بِاَللَّهِ وَمَلَائِكَتِهِ وَكُتُبِهِ وَرُسُلِهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ، وَتُؤْمِنَ بِالْقَدَرِ خَيْرِهِ وَشَرِّهِ. ..."

رَوَاهُ مُسْلِمٌ

ነብዩ ሙሀመድ(ሰለላ ዐለይሂ ወሰላም)በሶሒሕ  ሐዲስ እንዲህ ብለዋል ፦ “ እምነት(ኢማን)ማለት በአላህ ማመን፣ በመፃሀፋት ማመን፣ በመልእክተኞች ማመን፣ በመጨረሻው  ቀን ማመን፣ በቀደር(በአላህ ውሳኔ) በጀም ከፋም ማመን ነው።

ሓዲሱን ሙስሊም ዘግቦታል።

·      ከቁርአን

አላህ በቁርአን ላይ እንዲህ ብሏል

 

۞ لَّيْسَ الْبِرَّ أَن تُوَلُّوا وُجُوهَكُمْ قِبَلَ الْمَشْرِقِ وَالْمَغْرِبِ وَلَٰكِنَّ الْبِرَّ مَنْ آمَنَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ وَالْمَلَائِكَةِ وَالْكِتَابِ وَالنَّبِيِّينَ وَآتَى الْمَالَ عَلَىٰ حُبِّهِ ذَوِي الْقُرْبَىٰ وَالْيَتَامَىٰ وَالْمَسَاكِينَ وَابْنَ السَّبِيلِ وَالسَّائِلِينَ وَفِي الرِّقَابِ وَأَقَامَ الصَّلَاةَ وَآتَى الزَّكَاةَ وَالْمُوفُونَ بِعَهْدِهِمْ إِذَا عَاهَدُوا ۖ وَالصَّابِرِينَ فِي الْبَأْسَاءِ وَالضَّرَّاءِ وَحِينَ الْبَأْسِ ۗ أُولَٰئِكَ الَّذِينَ صَدَقُوا ۖ وَأُولَٰئِكَ هُمُ الْمُتَّقُونَ   ﴿البقرة: ١٧٧﴾   

 

 

 

“መልካም ስራ ፊቶቻችሁን ወደ ምስራቅና ምዕራብ አቅጣጫ ማዞር አይደለም። ግን መልካም ስራ በአላህና በመጨረሻው ቀን፣ በመላክትም፣ በመፀሐፋም፣ በነብያትም፣ ያመነ ... ነው።”

አላህ እንዲህ አለ፦

  ﴿البقرة: ٢٨٥﴾    كُلٌّ آمَنَ بِاللَّهِ وَمَلَائِكَتِهِ وَكُتُبِهِ وَرُسُلِهِ

ሁሉም በአላህ፣ በመላዕክቱም፣ በመጻሕፍቱም፣ በመልክተኞቹም ከመልክተኞቹ «በአንድም መካከል አንለይም» (የሚሉ ሲኾኑ) አመኑ፡፡       ( 2: 285)

 




·      ሂወትን እንዲወስዱ የታዘዙ መላኢኮች እንዳሉ ማመን።

 

አላህ እንዲህ አለ፦

 

                     ۞ قُلْ يَتَوَفَّاكُم مَّلَكُ الْمَوْتِ الَّذِي وُكِّلَ بِكُمْ ثُمَّ إِلَىٰ رَبِّكُمْ تُرْجَعُونَ   ﴿السجدة: ١١﴾ 

 

«በእናንተ የተወከለው መልአከ ሞት ይገድላችኋል፡፡ ከዚያም ወደ ጌታችሁ ትመለሳላችሁ» በላቸው፡፡ (32: 11)

Ø በአጠቃላይ ይህንን ሁሉ ስራቸውን የሚሰሩት በአላህ ፍቃድ፣ ፍላጎት እና በአላህ ትእዛዝ እንደሆነ ማመን።

አላህ እንዲህ አለ፦

  ﴿الأنبياء: ٢٧﴾   لَا يَسْبِقُونَهُ بِالْقَوْلِ وَهُم بِأَمْرِهِ يَعْمَلُونَ

በንግግር አይቀድሙትም፤ (ያላለውን አይሉም)፡፡ እነርሱም በትእዛዙ ይሠራሉ፡፡   (21: 27)

አላህ እንዲህ አለ፦

 

  ﴿التحريم: ٦﴾    لَّا يَعْصُونَ اللَّهَ مَا أَمَرَهُمْ وَيَفْعَلُونَ مَا يُؤْمَرُونَ

 

አላህን ያዘዛቸውን ነገር (በመጣስ) አያምጹም፡፡ የሚታዘዙትንም ሁሉ ይሠራሉ፡፡ (66: 6)

 

   ለዚህም  ነው አላህ በቁርአን ላይ አንዳንድ ጊዜ ስራን ወደራሱ ያስጠጋዋል ( ለምሳሌ፦ “....ነገሩን ሁሉ የሚያስተናብር ሲሆን .....” ) አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ወደ መላኢኮች ያስጠጋዋል ( ለምሳሌ፦ “ ... ነገርንም አስተባባሪዎች በሆኑት (መላእክት) እምላለሁ፤ ... )

Ø በቡድንና በአጠቃላይ የተጠቀሱ ካሉ በነሱ ማመን።

ለምሳሌ፦ -> የጀነት ጠባቂዎች

           -> የዓርሽ ተሸካሚዎች. . . .

           -> በይተል መዕሙን 75 000 መላኢኮች እየገቡ ዒባዳ እንደሚያደርጉና አንድ ግዜ የደረሰው ደግሞ እንደማይደግም።

Ø በስም የተጠቀሱመላኢኮችን ካሉ በስማቸው ማመን። በነጠላ የተጠቀሰ መላኢካ ካለ በነጠላ ማመን። ስለ እያንዳንዳቸው የተጠቀሰ ባህሪ ካለ በዛ ማመን።

 

ለምሳሌ ፦  ጂብሪል

አላህ እንዲህ አለ፦

  ﴿النحل: ١٠٢﴾   قُلْ نَزَّلَهُ رُوحُ الْقُدُسِ مِن رَّبِّكَ بِالْحَقِّ

(ቁርኣንን) ቅዱሱ መንፈስ (ጂብሪል) እውነተኛ ሲኾን ከጌታህ አወረደው በላቸው፡፡ (16: 102)

    ጅብሪል 600 ክንፍ አለው አንዱ ክንፉ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ አድምሱን ይሞላዋል።

   ነብዩ ሙሀመድ(ሰለላ ዓለያሂ ወሰለም) እንዲህ ብለው ተናግረዋል ፦ ጅብሪል ስራው መልእክትን (ዋሒን) ከ አላህ ወደ ነብያት ማድረስ ነው።

አላህ እንዲህ አለ፦

  ﴿النحل: ١٠٢﴾   قُلْ نَزَّلَهُ رُوحُ الْقُدُسِ مِن رَّبِّكَ بِالْحَقِّ

(ቁርኣንን) ቅዱሱ መንፈስ (ጂብሪል) እውነተኛ ሲኾን ከጌታህ አወረደው በላቸው፡፡ (16: 102)

 

Ø በቡድን (ባጠቃላይ) የተነገሩ ባህሪይ፣ ስራ ወይንም መገለጫ ከተነገረ ማመን።

 

ለምስሌ፦

 

አላህ እንዲህ አለ፦

 

    الْحَمْدُ لِلَّهِ فَاطِرِ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ جَاعِلِ الْمَلَائِكَةِ رُسُلًا أُولِي أَجْنِحَةٍ مَّثْنَىٰ وَثُلَاثَ وَرُبَاعَ ۚ يَزِيدُ فِي الْخَلْقِ مَا يَشَاءُ ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ   ﴿فاطر: ١﴾

ምስጋና ሰማያትንና ምድርን ፈጣሪ፣ መላእክትን ባለ ሁለት ሁለት፣ ባለ ሶስት ሶስትም፣ ባለ አራት አራትም ክንፎች የኾኑ መልክተኞች አድራጊ ለኾነው አላህ ይገባው፡፡ በፍጥረቱ ውስጥ የሚሻውን ይጨምራል፡፡ አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነውና፡፡ (35: 1)

አላህ እንዲህ አለ፦

 

    وَلَوْ تَرَىٰ إِذْ يَتَوَفَّى الَّذِينَ كَفَرُوا ۙ الْمَلَائِكَةُ يَضْرِبُونَ وُجُوهَهُمْ وَأَدْبَارَهُمْ وَذُوقُوا عَذَابَ الْحَرِيقِ   ﴿الأنفال: ٥٠﴾

እነዚያንም የካዱትን መላእክት ፊቶቻቸውንና ጀርባዎቻቸውን እየመቱ «የቃጠሎንም ስቃይ ቅመሱ» (እያሉ) በሚገድሏቸው ጊዜ ብታይ ኖሮ (አስደንጋጭን ነገር ታይ ነበር)፡፡ (8: 50)

አላህ እንዲህ አለ፦

    جَنَّاتُ عَدْنٍ يَدْخُلُونَهَا وَمَن صَلَحَ مِنْ آبَائِهِمْ وَأَزْوَاجِهِمْ وَذُرِّيَّاتِهِمْ ۖ وَالْمَلَائِكَةُ يَدْخُلُونَ عَلَيْهِم مِّن كُلِّ بَابٍ

    سَلَامٌ عَلَيْكُم بِمَا صَبَرْتُمْ ۚ فَنِعْمَ عُقْبَى الدَّارِ   ﴿الرعد:   ٢٣ - ٢٤﴾

 

   (እርሷም) የመኖሪያ ገነቶች ናት፡፡ ይገቡባታል፡፡ ከአባቶቻቸውም፣ ከሚስቶቻቸውም፣ ከዝርያቸውም መልካም የሠራ ሰው (ይገባታል)፡፡ መላእክትም በእነርሱ ላይ ከየደጃፉ ሁሉ ይገባሉ፡፡  «ሰላም ለእናንተ ይኹን፡፡ (ይህ ምንዳ) በመታገሳችሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም አገር ምን ታምር!» (ይሏቸዋል)፡፡ (13: 23 - 24)

 






·      የሚረገዝ እና የተረገዘ ልጅን በተመለከተ የሚሰሩ መላኢኮች እንዳሉ ማመን።

 عَنْ أَبِي عَبْدِ الرَّحْمَنِ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ مَسْعُودٍ t قَالَ: حَدَّثَنَا رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم -وَهُوَ الصَّادِقُ الْمَصْدُوقُ-: " ... ثُمَّ يُرْسَلُ إلَيْهِ الْمَلَكُ فَيَنْفُخُ فِيهِ الرُّوحَ، وَيُؤْمَرُ بِأَرْبَعِ كَلِمَاتٍ: بِكَتْبِ رِزْقِهِ، وَأَجَلِهِ، وَعَمَلِهِ، وَشَقِيٍّ أَمْ سَعِيدٍ؛ ... "

رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ ، وَمُسْلِمٌ.

ዓብደላህ ኢብን መስዑድ እንዲህ አለ። እውነት ተናጋሪ እና እውነት የተነገራቸው የአላህ መልእክተኛ rእንዲህ አሉ። “ ... ከዛም መልእክተኛ ይላክና ሩሕ ይተነፍስበታል። መልእክተኛውም በአራት ነገሮች ላይ ይታዘዛል። ሲሳዩን፣ ፍጻሜውን፣ ስራውን፣ የተከፋ ወይንም ደስተኛ መሆኑን እንዲጽፍ ይታዘዛል። ...”  ሓዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

 


አላህ ከወንጀሎች ይጠብቀን


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


የሸይኽ ዓብዱል ዓዚዝ አልቡረዒ ያማረ እና የጠነከረ ምክር : አላህን በማመፅ ላይ የሚውሉ ፀጋዎችን መሸከም ከንቱ ሥለመሆኑ ....
አንዳንድ ፀጋዎች ከኛ ጋር ከመቆየታቸው ይልቅ መወገዳቸው የተሻለ ነው ! ይላሉ ሸይኹ ...
እናዳምጣቸው !

በዓረብኛ


1.   በመላኢኮች ማመን

 

   በመላኢኮች  ማመን ከእስልምና መሰረቶች እምነቶች ውስጥ ሁለተኛው ነው።

ማስረጃ፦

·      ከሓዲስ

 عَنْ عُمَرَ قَالَ: "... فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ... أَنْ تُؤْمِنَ بِاَللَّهِ وَمَلَائِكَتِهِ وَكُتُبِهِ وَرُسُلِهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ، وَتُؤْمِنَ بِالْقَدَرِ خَيْرِهِ وَشَرِّهِ. ..."

رَوَاهُ مُسْلِمٌ

ነብዩ ሙሀመድ(ሰለላ ዐለይሂ ወሰላም)በሶሒሕ  ሐዲስ እንዲህ ብለዋል ፦ “ እምነት(ኢማን)ማለት በአላህ ማመን፣ በመፃሀፋት ማመን፣ በመልእክተኞች ማመን፣ በመጨረሻው  ቀን ማመን፣ በቀደር(በአላህ ውሳኔ) በጀም ከፋም ማመን ነው።

ሓዲሱን ሙስሊም ዘግቦታል።

·      ከቁርአን

አላህ በቁርአን ላይ እንዲህ ብሏል

 

۞ لَّيْسَ الْبِرَّ أَن تُوَلُّوا وُجُوهَكُمْ قِبَلَ الْمَشْرِقِ وَالْمَغْرِبِ وَلَٰكِنَّ الْبِرَّ مَنْ آمَنَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ وَالْمَلَائِكَةِ وَالْكِتَابِ وَالنَّبِيِّينَ وَآتَى الْمَالَ عَلَىٰ حُبِّهِ ذَوِي الْقُرْبَىٰ وَالْيَتَامَىٰ وَالْمَسَاكِينَ وَابْنَ السَّبِيلِ وَالسَّائِلِينَ وَفِي الرِّقَابِ وَأَقَامَ الصَّلَاةَ وَآتَى الزَّكَاةَ وَالْمُوفُونَ بِعَهْدِهِمْ إِذَا عَاهَدُوا ۖ وَالصَّابِرِينَ فِي الْبَأْسَاءِ وَالضَّرَّاءِ وَحِينَ الْبَأْسِ ۗ أُولَٰئِكَ الَّذِينَ صَدَقُوا ۖ وَأُولَٰئِكَ هُمُ الْمُتَّقُونَ   ﴿البقرة: ١٧٧﴾   

 

 

 

“መልካም ስራ ፊቶቻችሁን ወደ ምስራቅና ምዕራብ አቅጣጫ ማዞር አይደለም። ግን መልካም ስራ በአላህና በመጨረሻው ቀን፣ በመላክትም፣ በመፀሐፋም፣ በነብያትም፣ ያመነ ... ነው።”

አላህ እንዲህ አለ፦

  ﴿البقرة: ٢٨٥﴾    كُلٌّ آمَنَ بِاللَّهِ وَمَلَائِكَتِهِ وَكُتُبِهِ وَرُسُلِهِ

ሁሉም በአላህ፣ በመላዕክቱም፣ በመጻሕፍቱም፣ በመልክተኞቹም ከመልክተኞቹ «በአንድም መካከል አንለይም» (የሚሉ ሲኾኑ) አመኑ፡፡       ( 2: 285)

በመላኢኮች ማመን የሚመለከቱትን ነጥቦች አጠቃሎየያዘ ነው።

Ø መላኢኮች አሉ ብሎ ማመን።

 

ቁርአንና ሐዲስ እንደሚታወቀው  ስለ መላኢኮች ብዙ ነገሮችን ይነግራሉ። ይህ ስለመኖራቸው ማስረጃ ነው። ለምሳሌ፦

 

አላህ እንዲህ አለ፦

  ﴿البقرة: ٢٨٥﴾    كُلٌّ آمَنَ بِاللَّهِ وَمَلَائِكَتِهِ وَكُتُبِهِ وَرُسُلِهِ

ሁሉም በአላህ፣ በመላዕክቱም፣ በመጻሕፍቱም፣ በመልክተኞቹም ከመልክተኞቹ «በአንድም መካከል አንለይም» (የሚሉ ሲኾኑ) አመኑ፡፡

 

Ø መላኢኮች ከብርሀን (ከኑር) ነው የተፈጠሩት ብሎ ማመን።

 

ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ ነብዩ  መሓመድ ( ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ ፦

“መላኢኮች ከብርሃን (ከኑር) ተፈጠሩ። ጂኒዎችም ከእሳት ከሆነ ነበልባል ተፈጠሩ። አደምም ደግሞ ከተገለፀላችሁ ነገር (ከአፈር) ተፈጠረ።”

 

Ø አላህ መላኢኮችን እንዲገዙትና ትእዛዛቱን እንዲፈፅሙ እንደፈጠራቸውና እነሱም እንደሚገዙትና ትእዛዛቱን እንደሚፈፅሙ ማመን።  ማስረጃ፦

 

አላህ እንዲህ አለ፦

إِنَّ الَّذِينَ عِندَ رَبِّكَ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِ وَيُسَبِّحُونَهُ وَلَهُ يَسْجُدُونَ ۩     ﴿الأعراف: ٢٠٦﴾

እነዚያ እጌታህ ዘንድ ያሉት (መላእክት) እርሱን ከመገዛት አይኮሩም፡፡ ያወድሱታልም፡፡ ለእርሱም ብቻ ይሰግዳሉ፡፡ (7: 206)

አላህ እንዲህ አለ፦

 

فَإِنِ اسْتَكْبَرُوا فَالَّذِينَ عِندَ رَبِّكَ يُسَبِّحُونَ لَهُ بِاللَّيْلِ وَالنَّهَارِ وَهُمْ لَا يَسْأَمُونَ ۩  ﴿فصلت: ٣٨﴾

ቢኮሩም እነዚያ በጌታህ ዘንድ ያሉት (መላእክት) በቀንም በሌሊትም ለእርሱ ያወድሳሉ፡፡ እነርሱም አይሰለቹም፡፡ (41: 38)

 

Ø መላኢኮች የተከበሩ የአላህ ባሪያዎች ናቸው ብሎ ማመን።

 

አላህ እንዲህ አለ፦

  ﴿الأنبياء: ٢٦﴾    سُبْحَانَهُ ۚ بَلْ عِبَادٌ مُّكْرَمُونَ

«አልረሕማንም (ከመላእክት) ልጅን ያዘ» አሉ፡፡ ጥራት ተገባው፡፡ አይደለም (መላእክት) የተከበሩ ባሮች ናቸው፡፡ (21: 26)

ክብራቸው ከሚያመለክት  ውስጥ፤ አላህ ከእርሱ ጋር አብሮ ያነሳቸዋል።

አላህ እንዲህ አለ፦

  ﴿البقرة: ٢٨٥﴾    كُلٌّ آمَنَ بِاللَّهِ

 

ሁሉም በአላህ፣ ... አመኑ ፡: (2: 285)

Ø መላኢኮች ከፍ ያሉና ወደ አላህ ቅርብ እንደሆኑ አላህ መናገሩን ማመን።

አላህ እንዲህ አለ፦

  ﴿الصافات: ٨﴾   لَّا يَسَّمَّعُونَ إِلَى الْمَلَإِ الْأَعْلَىٰ 

ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡ (37: 8)

አላህ እንዲህ አለ፦

  ﴿المطففين: ٢١﴾   يَشْهَدُهُ الْمُقَرَّبُونَ

ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡ (83: 21)

 

Ø መላኢኮች አላህ ያዘዛቸውን እንደሚፈፅሙ እና ሁሉም የየራሳቸው ስራ እንዳላቸው ማመን።

የተወሰኑት የሚከተሉት ናቸው ፦

·      ዓርሽን የተሸከሙ መላኢኮች እንዳሉ ማመን።

አላህ እንዲህ አለ፦

 

  ﴿غافر: ٧﴾   الَّذِينَ يَحْمِلُونَ الْعَرْشَ وَمَنْ حَوْلَهُ 

እነዚያ ዐርሹን የሚሸከሙት እነዚያም በዙሪያው ያሉት በጌታቸው ምስጋና ያወድሳሉ፡፡ በእርሱም ያምናሉ፡፡ (40: 7)

·      የጀሀነም ሰዎችን የሚቀጡ መላኢኮች እንዳሉ ማመን።

አላህ እንዲህ አለ፦

 

             عَلَيْهَا مَلَائِكَةٌ غِلَاظٌ شِدَادٌ لَّا يَعْصُونَ اللَّهَ مَا أَمَرَهُمْ وَيَفْعَلُونَ مَا يُؤْمَرُونَ   ﴿التحريم: ٦﴾

በእርሷ ላይ ጨካኞች፣ ኀይለኞች የኾኑ መላእክት አልሉ፡፡ አላህን ያዘዛቸውን ነገር (በመጣስ) አያምጹም፡፡ የሚታዘዙትንም ሁሉ ይሠራሉ፡፡ (66: 6)

·      በዚች ዓለም ላይ የአደም ልጆችን የሚጠብቁ እንዳሉ ማመን።

 

አላህ እንዲህ አለ፦

 

  ﴿الرعد: ١١﴾   لَهُ مُعَقِّبَاتٌ مِّن بَيْنِ يَدَيْهِ وَمِنْ خَلْفِهِ يَحْفَظُونَهُ مِنْ أَمْرِ اللَّهِ ۗ 

 

ለእርሱ (ለሰው) ከስተፊቱም ከኋላውም በአላህ ትዕዛዝ (ከክፉ) የሚጠብቁት ተተካኪዎች (መላእክት) አሉት፡፡  (13: 11)

·      የባሪያዎችን ስራ መከታተል እና መፃፍ ስራቸው የሆኑ መላኢኮች እንዳሉ ማመን ።

 

አላህ እንዲህ አለ፦

 

وَإِنَّ عَلَيْكُمْ لَحَافِظِينَ  * كِرَامًا كَاتِبِينَ  ﴿الإنفطار: ١٠ -١١ ﴾

 

 በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤ የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡    (82: 10 - 11)

 




ከኢብኑ መስዑድ በዘገቡት ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል አሉ፦

"ከአላህ በስተቀር (እውነተኛ) አምላክ እንደሌለ እና እኔም የአላህ መልእክተኛ እንደሆንኩ የሚመሰክር የሆነ ሙስሊም ደም (ህይወት) ከሶስት ነገሮች በአንዱ እንጂ አይፈቀድም (አይደፈርም)። (እነሱም፦) አግብቶ የሚያውቅ ዝሙተኛ፣ ነፍስ በነፍስ (አውቆ ነፍስ ያጠፋ) እና ሃይማኖቱን ትቶ ከሙስሊሙ ህብረት ያፈነገጠ ናቸው።"

ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል


አሰላሙ አለይኩም ያ ጀመአ በዚህ ቻናል ለይ የሚለቀቁ የአቂዳ ትምህረቶች ለጊዜው በሳምን አንድ ቀን ነው ያረግነው ቀኑ እንዲጨመር የምትፈልጉ ካላቹ በውስጥ ንገሩን እንጨምረዋለን ኢንሸአላህ


1- ተውሒድ ኣል-ኣስማኡ ወስ-ሲፋት

   ተውሒድ ኣል-ኣስማኡ ወስ ሲፋት ማለት የአላህ ስምና ባህርያትን ትርጉም ሳናበላሽ፣ ቃሉን ሳናራቁት፣ እና ሳናመሳስል ለአንድ አላህ ብቻ ማድረግ ማለት ነው።

አላህ በቁርአኑ እንዲህ ብሏል

لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ   سورة الشورى 11

የሚመስለው ምንም ነገር የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡  (42 : 11)

ð አላህ መልካምንና ያማሩ ስሞች አሉት

አላህ በቁርአኑ እንዲህ ብሏል

وَلِلَّهِ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ فَادْعُوهُ بِهَا ۖ   سورة الأعراف  180

 

ለአላህም መልካም ስሞች አሉት፡፡ (ስትጸልዩ) በእርሷም ጥሩት፡፡  (7 : 180)

   ለኛ ያሳወቀን 99 ስሞች አሉ። ለፈለጋቸው ባሮች ያስተማራቸው ስሞች አሉ። እርሱ ብቻ የሚያቃቸው ስሞችም አሉ።

   የአላህ ስሞች ትርጉም አላቸው። እነዚህ ትርጉሞች የአላህን ባህርያት ይገልጹልናል። ለምሳሌ አር-ራሕማን ከአላህ ስሞች ውስጥ አንዱ ነው። ትርጉሙም እጅግ በጣም ርኅሩህ ማለት ነው።

አላህ በቁርአኑ እንዲህ ብሏል

الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ   سورة الفاتحة   3

እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ    (1 : 3)

ስለዚህ አር-ራሕማን የአላህ ስሞ ነው። ርኅሩህነት ደግሞ የአላህ ባህሪ ነው።

ሁልግዜ መረሳት የለለበት ነጥብ --- የአላህ ስምና ባህርያት ከሰው ልጅ ስምና ባህርያት ፈጽሞ አይመሳሰሉም።

 

    አላህ ሰብሓነሁ ወተዓላ ከፍ ያሉና ለርሱ ብቻ የሚገቡ ባህርያት አሉት። በቁርአንና ሓዲስ የተጠቀሱ የአላህ ስምና ባህርያት መቀበል የአህለ ሱና መንገድና አካሄድ ነው። የአላህ ስምና ባህርያትን በቀጥታ መቀበል ግዴታ ነው። የአላህ ስምና ባህርያትን እንቀበላለን በማለት ወሰንን አልፎ አላህን ከፍጥራን ጋር ማመሳሰልም አይፈቀድም። ደግሞ አላህን ከፍጡራን ጋር ላለማመሳሰል በሚል ምክንያት (ሰበብ) የአላህን ስምና ባህርያትን የሚያመለክቱ የቁርአን አንቀጾችን እና ሓዲሶችን ትርጉም መቀየር (ተሕሪፍ) ወይን ደግሞ ትርጉም አልባ ማድረግም (ተዕጢል) አይፈቀድም።

   የአህለ ሱና አቋም መካከለኛ ነው። የአላህ ስምና ባህርያትን የሚያመለክቱ የቁርአን አንቀጾችን እና ሓዲችን በቀጥታ ይቀበላሉ። ትርጉም አልባ አያደርጉም። ትርጉሙንም በፍልስፍናና በስሜታቸው አያጠማዝዙትም። እነዚህን የአላህ ስምና ባህርያትን ደግሞ  ሁኔታ አያስቀምጡላቸውም፥ ከፍጡራን ጋርም አያመሳስሏቸውም።

 

 

ð ሰለፎቻችን በአላህ ስምና ባህርያት ያምኑ ነበር።

   ታላቁ የቁርአን ተፍሲር ዓሊም ኢብኑ ከሲር እንዲህ አሉ “ እኛ የምንከተለው (የአላህ ስምና ባህርያትን በተመለከተ) የሰለፎችን መንገድ ነው። እንደ ኢማሙ ማሊክ፣ አውዘዒ፣ ሰውሪ፣ ለይስ፣ ሻፍዕይ፣ አሕመድ፣ ኢስሓቅ እና የመሳሰሉትን ቀደምት(ሰለፎች)ሙስሊሞችን እንከተላለን። እነሱም ያሉት የአላህ ስምና ባህርያትን የሚመለከቱ የቁርአን አንቀጾችን እና ሓዲሶችን እንዳሉ ካለማመሳሰል፣ ሁኔታን ካለማበጀትና ካለመጠየቅ፣ እንዲሁም ትርጉም ካለማራቆት ማሳለፍ (ማመን) ነው።”

   ኢማሙ ማሊክ ዘንድ አንድ ሰው ገባና “አላህ ከዓርሽ በላይ ነው። እንዴት ?” ብሎ  ጠየቃቸው። እሳቸውም “አላህ ከዓርሽ በላይ መሆኑ የታወቀ ነው። እንዴት ለሚለው፥ አይታወቅም ነው መልሱ። በዚህ ማመን ደግሞ ግዴታ ነው። እንዴት ብሎ መጠየቅ ደግሞ ቢድዓ(አዲስ መጠ ነገር) ነው። አንተን ደግሞ ከሙብተዲዕ እንጂ ከሌላ አልቆጥርህም። ” በማለት መለሱለት። ከመጅሊሳቸውም እንዲወጣ አደረጉት።

ከአላህ ስምና ባህርያት ውስጥ የሚከተሉት የተወሰኑት ናቸው።

1。 አላህ ከ 7 ሰማይ በላይ፥ ከዓርሽ በላይ ነው።

አላህ በቁርአኑ እንዲህ ብሏል

الرَّحْمَٰنُ عَلَى الْعَرْشِ اسْتَوَىٰ -  سورة طه  5

አላህ ከዓርሽ በላይ ነው። (20: 5)

   ሁልግዜ መረሳት የለለበት ነጥብ --- የአላህ ስምና ባህርያት ከሰው ልጅ ስምና ባህርያት ፈጽሞ አይመሳሰሉም።

2。 አላህ ሰሚና ተመልካች ነው።

አላህ በቁርአኑ እንዲህ ብሏል

لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ  - سورة الشورى  11  

የሚመስለው ምንም ነገር የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ (42: 11)

   ሁልግዜ መረሳት የለለበት ነጥብ --- የአላህ ስምና ባህርያት ከሰው ልጅ ስምና ባህርያት ፈጽሞ አይመሳሰሉም።

3。አላህ ይናገራል።

وَإِذْ قَالَ اللَّهُ يَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ أَأَنتَ قُلْتَ لِلنَّاسِ اتَّخِذُونِي وَأُمِّيَ إِلَٰهَيْنِ مِن دُونِ اللَّهِ ۖ  -  سورة المائدة  116

አላህም፡- «የመርየም ልጅ ዒሳ ሆይ! አንተ ለሰዎቹ፡- እኔንና እናቴን ከአላህ ሌላ ሁለት አምላኮች አድርጋችሁ ያዙ ብላሃልን» በሚለው ጊዜ (አስታውስ)  

وَكَلَّمَ اللَّهُ مُوسَىٰ تَكْلِيمًا - سورة النساء  164

አላህም ሙሳን ማነጋገርን አነጋገረው፡፡ ( 4: 164)

   ሁልግዜ መረሳት የለለበት ነጥብ --- የአላህ ስምና ባህርያት ከሰው ልጅ ስምና ባህርያት ፈጽሞ አይመሳሰሉም።

 

4。 አላህ አዋቂ ነው። አላህ ጥበበኛ ነው።

وَهُوَ الْعَلِيمُ الْحَكِيمُ   سورة التحريم  2

እርሱም(አላህ) ዐዋቂው ጥበበኛው ነው፡፡ ( 66: 2)

   ሁልግዜ መረሳት የለለበት ነጥብ --- የአላህ ስምና ባህርያት ከሰው ልጅ ስምና ባህርያት ፈጽሞ አይመሳሰሉም።

5。 አላህ መልካሞች ሰዎችን ይወዳል።

قُلْ إِن كُنتُمْ تُحِبُّونَ اللَّهَ فَاتَّبِعُونِي يُحْبِبْكُمُ اللَّهُ وَيَغْفِرْ لَكُمْ ذُنُوبَكُمْ ۗ   سورة آل عمران - 31

በላቸው፡- «አላህን የምትወዱ እንደኾናችሁ ተከተሉኝ፤ አላህ ይወዳችኋልና፡፡ ኀጢኣቶቻችሁንም ለናንተ ይምራልና፡፡  ( 3: 31)

   ሁልግዜ መረሳት የለለበት ነጥብ --- የአላህ ስምና ባህርያት ከሰው ልጅ ስምና ባህርያት ፈጽሞ አይመሳሰሉም።

 

6.  አላህ ከሃድያንን ይጠላል።

ذَٰلِكَ بِأَنَّهُمُ اتَّبَعُوا مَا أَسْخَطَ اللَّهَ وَكَرِهُوا رِضْوَانَهُ فَأَحْبَطَ أَعْمَالَهُمْ   سورة محمد - 28

ይህ እነርሱ አላህን ያስቆጣውን ነገር ስለ ተከተሉ ውዴታውንም ስለ ጠሉ ነው፡፡ ስለዚህ ሥራዎቻቸውን አበላሸባቸው፡፡  (47: 28)

   ሁልግዜ መረሳት የለለበት ነጥብ --- የአላህ ስምና ባህርያት ከሰው ልጅ ስምና ባህርያት ፈጽሞ አይመሳሰሉም።






"ወንጀል ከሱና አያስወጣም " እየተባለ .. ውሸት ፣ ማጭበርበር እና ሌሎችም አስከፊ ወንጀሎች ዉስጥ በግዴለሽነት መነከር አሳፋሪ መባል የሚያንሰው ክፉ ና ፀያፍ ምግባር ነው .. ወቅታችን ላይ ደግሞ ይሄው ክፉ ደዌ ብዙዎችን አጥቅቷል ---- ወንጀል አይጎዳ ይመስል በቀጥታም ባይሆን ባዙሪት ቀላልነቱ ይሰበክ ይዟል - በአንዳንዶቻችን ...
ነብዩን እና ባልደረቦቻቸውን እከተላለሁ የሚል ግለሠብና ወገን ወንጀልን የሚመለከትበት አይን ኢርጃእን የተጎራበተ መሆኑ ወይም የተጎራበተ ሊሆን መቃረቡ ይሳዝናል ...
የአላህን፡ ህግጋቶች ማክበርና አግዝፎ መመልከት የተቅዋ እና የአላህን ቅጣት መጠንቀቅ መገለጫ ነው ...

وَمَن يُعَظِّمْ شَعَائِرَ اللَّهِ فَإِنَّهَا مِن تَقْوَى الْقُلُوبِ

የአላህንም የሃይማኖት ምልክቶች (ትእዛዦች ፣ ክልከላዎች ) የሚያከብር ሰው እርሷ ከልቦች የኾነች ጥንቃቄ ናት፡፡
ተቃራኒው እንዝላልነት የልብን መጥቆር አጉልቶ ይሳያል .....
ዓብዱላህ ኢብኑ መስዑድ ሙእሚን ወንጀልን አግዝፎ እንደሚመለከት፣ ሙናፊቅ ግን እጅጉን አቅልሎና አሳንሶ እንደሚያየው ተናግረዋል .....

በወንጀሎች ላይ መዘውተር የከሃዲያን መገለጫ መሆኑንም ልንዘነጋ አይገባም ... አላህ እነሱን ሲገልፃቸው እንዲህ ይላል

وَكَانُوا يُصِرُّونَ عَلَى الْحِنثِ الْعَظِيمِ

(በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና )

ሌላው ነገር፦ ወንጀል (በተለይ የድብቅ ወንጀል ) መጨረሻን (አሟሟትን) ከሚያበላሹ ነገሮች ውስጥ አንዱ ነውና የዛሬውን ሱና ላይ መሆን ብቻ ሣይሆን የወንጀል ብዛት ሊያስከትል የሚችለውን መንሸራተትና ክፉ ውጤት እናስብ... አላህን እንፍራ ... ወደሱም እንመለስ ።
ጥፋትና ወንጀል ከሁላችንም ሊመነጭ የሚችል መሆኑን አልዘነጋሁም ። ከላይ በተጠቀሰው መጠን ወንጀል ላይ ቸልተኛ መሆን ግን እጅጉን አደገኛ ነው።
አላህ፡ ይመልሰን !

ቻናሉን ይቀላቀሉ። ሌሎችንም ይጋብዙ። መልእክቱን ለሌሎች በማሰራጨት የአጅሩ ተቋዳሽ ይሁኑ።
t.me/Muhammedsirage


1-    ተውሒድ አል-ኡሉህያ

 

ተውሒድ አል-ኡሉህያ ማለት አላህን  በአምልኮ አንድ ማድረግ ማለት ነው። ማለትም ሶላት ፣ ስግደት፣ ፀሎት ፣ ምልጃን መጠየቅ ፣ ...... የመሳሰሉትን አምልኮዎች ሁሉን ለአንድ አላህ ብቻ ማድረግ። ለፉጡሩን ማድረግ አይፈቀድም ብሎ ማመን።

 

       ባጠቃላይ አምልኮ ሁሉ ለአላህ ብቻ ነው የሚገባው።

 

ማስረጃ፦

 

አላህ እንዲህ አለ ፦

  ﴿الذاريات: ٥٦﴾   وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ

ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡ (51: 56)

 

አላህ እንዲህ አለ፦

 

  ﴿الجن: ١٨﴾    وَأَنَّ الْمَسَاجِدَ لِلَّهِ فَلَا تَدْعُوا مَعَ اللَّهِ أَحَدًا

እነሆ መስጊዶችም የአላህ ብቻ ናቸው፡፡ (በውስጣቸው) ከአላህ ጋር አንድንም አትገዙ (ማለትም)፡፡ (72: 18)

አላህ እንዲህ አለ፦

 

    لَقَدْ أَرْسَلْنَا نُوحًا إِلَىٰ قَوْمِهِ فَقَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُم مِّنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ إِنِّي أَخَافُ عَلَيْكُمْ عَذَابَ يَوْمٍ عَظِيمٍ    ﴿الأعراف: ٥٩﴾

 

 

ኑሕን ወደ ወገኖቹ በእርግጥ ላክነው፡፡ አላቸውም፡- «ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ለእናንተ ከርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም፡፡ እኔ በእናንተ ላይ የከባድ ቀንን ቅጣት እፈራላችኋለሁ፡፡» (7: 59)

ð አምልኮን ከአላህ ውጪ ለፍጡርን ማድረገግ ሽርክ (ማጋራት) ይባላል። ይህ ደግሞ ከእስልምና ያሚያስወጣ ትልቅ ወንጀል ነው። አምልኮን ለፍጡራን ማድረግ የተከለከለ እና ከእስልምና የሚያስወጣ ተግባር ነው። ለዚህ ማስረጃችን

 

አላህ እንዲህ አለ፦

 

  ﴿الجن: ١٨﴾    وَأَنَّ الْمَسَاجِدَ لِلَّهِ فَلَا تَدْعُوا مَعَ اللَّهِ أَحَدًا

እነሆ መስጊዶችም የአላህ ብቻ ናቸው፡፡ (በውስጣቸው) ከአላህ ጋር አንድንም አትገዙ (ማለትም)፡፡ (72: 18)

 

አላህ እንዲህ አለ፦

فَلَا تَجْعَلُوا لِلَّهِ أَندَادًا وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ   ﴿البقرة: ٢٢﴾

 

 

እናንተም (ፈጣሪነቱን) የምታውቁ ስትኾኑ ለአላህ ባላንጣዎችን አታድርጉ፡፡ (2: 22)

  

ð  ሽርክን የሚሰራ ሰው ወደ አላህ ካልተመለሰና ስራውን ካልተወ አላህ አያምረውም። 

ማስረጃውም ፦


አላህ እንዲህ አለ፦

إِنَّ اللَّهَ لَا يَغْفِرُ أَن يُشْرَكَ بِهِ وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَٰلِكَ لِمَن يَشَاءُ ۚ وَمَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدِ افْتَرَىٰ إِثْمًا عَظِيمًا   ﴿النساء: ٤٨﴾

አላህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡ ከዚህ ሌላ ያለውንም (ኀጢአት) ለሚሻው ሰው ይምራል፡፡ በአላህም የሚያጋራ ሰው ታላቅን ኀጢአት በእርግጥ ቀጠፈ፡፡ (4: 48)

ð ሽርክ ከሁሉም በደሎች የበለጠ ትልቅ በደል ነው።

አላህ እንዲህ አለ፦

إِنَّ الشِّرْكَ لَظُلْمٌ عَظِيمٌ   ﴿لقمان: ١٣﴾

« ... ማጋራት ታላቅ በደል ነውና» ያለውን (አስታውስ)፡፡ (31: 13)

 

ð ሽርክን ሁላችንም መራቅና መፋራት አለብን።

አላህ እንዲህ አለ፦

وَإِذْ قَالَ إِبْرَاهِيمُ رَبِّ اجْعَلْ هَٰذَا الْبَلَدَ آمِنًا وَاجْنُبْنِي وَبَنِيَّ أَن نَّعْبُدَ الْأَصْنَامَ   ﴿ابراهيم: ٣٥﴾

   ኢብራሂምም ባለ ጊዜ (አስታውስ) «ጌታዬ ሆይ! ይህንን አገር (መካን) ጸጥተኛ አድርገው፡፡ እኔንም ልጆቼንም ጣዖታትን ከመገዛት አርቀን፡፡ (14: 35)

ሽርክ ከሁሉም በደሎች የበለጠ ትልቅ በደል ስለሆነና  ሽርክን የሚሰራ ሰው ወደ አላህ ካልተመለሰና ስራውን ካልተወ አላህ አይምረውም።

 

ð መልእክተኞች የተላኩበት ዋና ምክንያትም ሰው አላህን ብቻ እንዲያመልክ ለማድረግ እና ሰውን ከሽርክ ለማራቅ ነው። ማስረጃው፦

አላህ እንዲህ አለ፦

وَلَقَدْ بَعَثْنَا فِي كُلِّ أُمَّةٍ رَّسُولًا أَنِ اعْبُدُوا اللَّهَ وَاجْتَنِبُوا الطَّاغُوتَ ۖ  ﴿النحل: ٣٦﴾  

 

በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ «አላህን ተገዙ፤ ጣዖትንም ራቁ» በማለት መልክተኛን በእርግጥ ልከናል፡፡  (16: 36)



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

194

obunachilar
Kanal statistikasi