የኒካሕ መስፈርቶች /ሸርጦች/
1. የተጋቢዎቹን ስም ለይቶ መግለፅ፡- ከአንድ በላይ ልጆች ባሉበት ሁኔታ “ልጄን አጋብቼሃለሁ” ወይም ለልጅህ አጋብቼያለሁ” ቢል በቂ አይሆንም፡፡ ስለዚህ ስም ተጠቅሶ ለምሳሌ “ልጄን ፋጢማን ለዐብደላህ አጋብቼያለሁ” ሊል ነው፡፡
2. የሁለቱ ተጋቢዎች ስምምነት፡- የግዴታ ጋብቻ ተቀባይነት የለውም፡፡ [ቡኻሪ፡ 5136፣ ሙስሊም፡ 1419]
3. ለሴቷ ወልይ መኖር፡፡ ነብዩ ﷺ “ያለ ወልይ ኒካሕ የለም” ብለዋልና፡፡ [ሶሒሕ ኢብን ማጃህ፡ 1537]
4. ኒካሑ ሲታሰር ሁለት ብቁ ምስክሮች መኖራቸው፡፡ [ሶሒሕ ኢብን ሒባን፡ 4075]
5. ተጋቢዎቹን እንዳይጋቡ የሚከለክል ነገር (ቅርብ ዝምድና፣ አማችቻ፣ ጥቢ፣ የእምነት ልዩነት፣ …) አለመኖር፡፡
የኒካሕ ማእዘናት፡-
1. ጋብቻን ከሚከለክሉ ነገሮች ነፃ የሆኑ ተጋቢዎች
2. ከሴቷ ወልይ በኩል “አጋብቻለሁ” ወይም መሰል የይሁንታ ቃል
3. የአግቢው ወይም ወኪሉ “ተቀብያለሁ” ወይም መሰል የመስማማት ቃል
(ከአልፊቅሁል ሙየስሰር ኪታብ የተወሰደ ገፅ፡404-406)
http://t.me/Menhaj_Salafiya
1. የተጋቢዎቹን ስም ለይቶ መግለፅ፡- ከአንድ በላይ ልጆች ባሉበት ሁኔታ “ልጄን አጋብቼሃለሁ” ወይም ለልጅህ አጋብቼያለሁ” ቢል በቂ አይሆንም፡፡ ስለዚህ ስም ተጠቅሶ ለምሳሌ “ልጄን ፋጢማን ለዐብደላህ አጋብቼያለሁ” ሊል ነው፡፡
2. የሁለቱ ተጋቢዎች ስምምነት፡- የግዴታ ጋብቻ ተቀባይነት የለውም፡፡ [ቡኻሪ፡ 5136፣ ሙስሊም፡ 1419]
3. ለሴቷ ወልይ መኖር፡፡ ነብዩ ﷺ “ያለ ወልይ ኒካሕ የለም” ብለዋልና፡፡ [ሶሒሕ ኢብን ማጃህ፡ 1537]
4. ኒካሑ ሲታሰር ሁለት ብቁ ምስክሮች መኖራቸው፡፡ [ሶሒሕ ኢብን ሒባን፡ 4075]
5. ተጋቢዎቹን እንዳይጋቡ የሚከለክል ነገር (ቅርብ ዝምድና፣ አማችቻ፣ ጥቢ፣ የእምነት ልዩነት፣ …) አለመኖር፡፡
የኒካሕ ማእዘናት፡-
1. ጋብቻን ከሚከለክሉ ነገሮች ነፃ የሆኑ ተጋቢዎች
2. ከሴቷ ወልይ በኩል “አጋብቻለሁ” ወይም መሰል የይሁንታ ቃል
3. የአግቢው ወይም ወኪሉ “ተቀብያለሁ” ወይም መሰል የመስማማት ቃል
(ከአልፊቅሁል ሙየስሰር ኪታብ የተወሰደ ገፅ፡404-406)
http://t.me/Menhaj_Salafiya