በአሜሪካ በእያንዳንዷ ደቂቃ ሞት እየተመዘገበ ነው
በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ150 ሺ አሻቅቧል፡፡
ይህም በእያንዳንዷ ደቂቃ አንድ ሰው እየሞተ መሆኑን የሚመለክት ነው፡፡
ትናንት ረቡዕ ብቻ 1 ሺ 461 ሰዎች ሞተዋል፡፡
ይህ ሮይተርስ እንደዘገበው ከሆነ 1 ሺ 484 ሰዎች ከሞቱበት እ.ኤ.አ ከግንቦት 27 2020 ወዲህ በአንድ ቀን የተመዘገበ ከፍተኛው ሪከርድ ነው፡፡
በቫይረሱ ክፉኛ ከተጠቁ 20 የዓለማችን ሃገራት ውስጥ ቀዳሚ የሆነችው አሜሪካ በሟቾች ቁጥር 6ኛ ነች፡፡
ከ1 መቶ ሺ ሰዎች መካከልም በአማካይ 45ቱ ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ ይሞታሉ፡፡
በእንዲህ ኣይነቱ የአማካይ ንጻሬ ዩናይትድ ኪንግደም፣ስፔን፣ጣሊያን፣ፔሩ እና ቺሊ ብቻ ናቸው አሜሪካን የሚቀድሙት፡፡
በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ150 ሺ አሻቅቧል፡፡
ይህም በእያንዳንዷ ደቂቃ አንድ ሰው እየሞተ መሆኑን የሚመለክት ነው፡፡
ትናንት ረቡዕ ብቻ 1 ሺ 461 ሰዎች ሞተዋል፡፡
ይህ ሮይተርስ እንደዘገበው ከሆነ 1 ሺ 484 ሰዎች ከሞቱበት እ.ኤ.አ ከግንቦት 27 2020 ወዲህ በአንድ ቀን የተመዘገበ ከፍተኛው ሪከርድ ነው፡፡
በቫይረሱ ክፉኛ ከተጠቁ 20 የዓለማችን ሃገራት ውስጥ ቀዳሚ የሆነችው አሜሪካ በሟቾች ቁጥር 6ኛ ነች፡፡
ከ1 መቶ ሺ ሰዎች መካከልም በአማካይ 45ቱ ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ ይሞታሉ፡፡
በእንዲህ ኣይነቱ የአማካይ ንጻሬ ዩናይትድ ኪንግደም፣ስፔን፣ጣሊያን፣ፔሩ እና ቺሊ ብቻ ናቸው አሜሪካን የሚቀድሙት፡፡