ማህተቤን አልበጥስም


Channel's geo and language: not specified, not specified
Category: not specified


ውድ የዚ ማህተቤን አልበጥስም ቻናል ተከታታዮች እስከዛሬ ድረስ በዚ ቻናል የማስተላልፋቸውን ሁሉንም ፕሮግራሞች በመከታተል ከጎኔ ሰለነበራችሁ አመሰግናለሁ እያልኩ አሁን ግን ይሄኛው ቻናሌ በቴክኒክ ችግር ምክንያት ስለተቋረጠብኝ ወደዚኛው ወደ አዲሱ ቻናሌ ተቀላቀሉ ስል እጠይቃለሁ 🙏🙏🙏

Related channels

Channel's geo and language
not specified, not specified
Category
not specified
Statistics
Posts filter


Video is unavailable for watching
Show in Telegram




በነቃም ጊዜ እነዚያን የሮማን ፍሬዎች አገኛቸው ወዲያውኑ ወደ አባ ነካሮ ሄደ ከበር ቆሞ አገኘውና ወንድሜ ነካሮ ሆይ በዚች ሌሊት አይተኸኛልን አለው እርሱም አዎን አይቼሀለሁ ሶስት የሮማን ፍሬዎችን ሰጥቼህ የለምን አለው። በዚያንም ጊዜ ያ መነኩሴ ወደ ገዳሙ ሄዶ የሆነውን ሁሉ ለአበምኔቱና ለመነኩሳቱ ነገራቸው እነዚያንም የሮማን ፍሬዎች አሳያቸው መነኰሳቱም ከአባ ነካሮ ቅድስና የተነሳ አደነቁ ያን ጊዜም የበጋ ወራት ነበርና የሮማንም ጊዜው አልነበረምና።

በዝቅተኛ ማእረግ ላይ ስለአደረጉት መነኮሳቱ አዘኑ በከፍተኛም ማእረግ ሊያደርጉት አዘኑ በከፍተኛም ማእረግ ሊያደርጉት ሽተው ወደርሱ በሄዱ ጊዜ አጡት ታላቅ ኀዘንንም አዘኑ ከዚህም በኃላ በዚች እለት እንዳረፈ መፃተኞች ነገሩአቸው።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትኑር አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር እና #መዝገበ_ቅዱሳን)


በነቃም ጊዜ እነዚያን የሮማን ፍሬዎች አገኛቸው ወዲያውኑ ወደ አባ ነካሮ ሄደ ከበር ቆሞ አገኘውና ወንድሜ ነካሮ ሆይ በዚች ሌሊት አይተኸኛልን አለው እርሱም አዎን አይቼሀለሁ ሶስት የሮማን ፍሬዎችን ሰጥቼህ የለምን አለው። በዚያንም ጊዜ ያ መነኩሴ ወደ ገዳሙ ሄዶ የሆነውን ሁሉ ለአበምኔቱና ለመነኩሳቱ ነገራቸው እነዚያንም የሮማን ፍሬዎች አሳያቸው መነኰሳቱም ከአባ ነካሮ ቅድስና የተነሳ አደነቁ ያን ጊዜም የበጋ ወራት ነበርና የሮማንም ጊዜው አልነበረምና።

በዝቅተኛ ማእረግ ላይ ስለአደረጉት መነኮሳቱ አዘኑ በከፍተኛም ማእረግ ሊያደርጉት አዘኑ በከፍተኛም ማእረግ ሊያደርጉት ሽተው ወደርሱ በሄዱ ጊዜ አጡት ታላቅ ኀዘንንም አዘኑ ከዚህም በኃላ በዚች እለት እንዳረፈ መፃተኞች ነገሩአቸው።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትኑር አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር እና #መዝገበ_ቅዱሳን)


ይሰበሰባሉ፡፡ ይህቺ ሀገር ትልቅ ናትና እስከ ዓርብም ያስተምራቸዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ሰይጣን ቀና፡፡ አባ ሐዊም እንደልማዱ በዕለተ ዓርብ ወደ ሰማይ በሄደ ጊዜ ያ ሰይጣን በመቀመጫው ተቀምጦ በእርሱ በሐዊ ተመስሎ በቀዳሚት ሰንበት ቀንም ተገልጦ "ፈጣሪያችን የሚወዳትን ነገር እነግራችሁ ዘንድ ሁላችሁም ተሰብሰቡ" አለ፡፡ ሁላቸውም ተሰበሰቡ፡፡ "አባት ሆይ! ያለ ልማድህ ዛሬ ለምን መጣህና ጠራኸን?" አሉት፡፡ ያ ጠላት ዲያብሎስም "ጌታዬ ለሕዝቦቼ የዚያችን በቤትህ አንፃር ያለችውን እንጨት ቅጠል በጥርሳቸው ይጨምሩ ዘንድ፣ በአፋቸውም ያጤሱ ዘንድ ዛሬ ካልነገርሃቸው ወዳጄ አይደለህም አለኝ" አላቸው፡፡ ይህችንም እንጨት ባያት ጊዜ እንዲህ አደረገ፣ ሔዋንን በእንጨት እንዳሳታት አሳታቸው፡፡ ዛሬ እንደሚያደርጉትም የጥንባሆ ዕቃን አደረጉ፡፡ ቅጠሏንም አምጥተው ቀጥቅጠው በእሳት አጢሰው ትንሹም ትልቁም፣ የከበረውም የጎሰቆለውም ሁላቸውም ጠጡ፡፡

ሐዊም በሰማይ ሳለ በጸጋ አውቆ አዘነ፣ ነገር ግን ስለ ሰንበታት ክብር ብሎ አደረ፡፡ ሰኞ በነግህም ሐዊ መጣ፣ ሰይጣንም እንደ ጢስ በኖ ጠፋ፡፡ እርሱም ሰዎቹን ሰብስቦ "ይህን ማን አስተማራችሁ?" አላቸው፡፡ "አንተ ነህ" አሉት፡፡ "ሰይጣን ነው እንጂ እኔ አይደለሁም፣ ከዛሬ ጀምሮ ተው" አላቸው፡፡ "ትናንት ጠጡ፣ ዛሬ ተው" ይለናል ብለው እምቢ አሉት፡፡ እርሱም አወገዛቸው፡፡ "በእርሻው የዘራት፣ በአፉም የጠጣት፣ በእጁም የያዛት የተረገመ ይሁን" አላቸው፡፡ ጋኔኑም በቅሉ ውስጥ ሆኖ ይነጋገራል፣ በውጭ ያሉትንም አጋንንት ይጠራቸዋል፡፡ በዚህን ሰዓት የተውም አሉ፣ እምቢም ያሉ አሉ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያቺ እንጨት ተረገመች፡፡ ሰውም በጠጣት ጊዜ የአምስት ቀፎ ሙሉ ንቦችን የሚያህሉ አጋንንት ይመጣሉ፡፡ በሁለቱ ዓይኖቹ ውስጥ፣ በሁለቱ አፍንጫዎቹም፣ በሁለቱ ጆሮዎቹም፣ በአፉም፣ በታች በሰገራ መውጫም በእነዚህ ሁሉ እንደ ቀፎ ንብ ይገባሉ፣ ይወጣሉ፡፡ ትምክህትን፣ ትዕቢትን፣ መግደልን፣ ሥርቆትንም፣ ክፉውንም ሁሉ ይመሉታል፡፡ ወሶበ ይሰትያ ብእሲ ይመጽኡ አጋንንት ዘየአክሉ መጠነ ፭ቱ ቀፈዋት ዘመልኡ አንህብት ወይበውኡ ውስቴቱ፡፡ በ፪ አዕይንቲሁ፣ ወበ፪ አዕናፊሁ፣ ወበ፪ አዕዛኒሁ ወበመንፈሱ ዘታህት በአፉሁ በዝንቱ ኵሉ ከመ ንህብ ዘቀፎ ይበውኡ ወይወጽኡ፡፡ ወይመልእዎ ትምክህተ፣ ወትዕቢተ፣ ቀትለ፣ ወሠሪቀ ወኵሎ ዕከያተ እንዲል መጽሐፍ፡፡

አባታችን ዘርዓ ቡሩክም ይህን ሰምቶ እጆቹን በትከሻው አመሳቅሎ አለቀሰ፣ በሥዕሉም አለ፣ በዚያን ጊዜ ወደ ዓለም ወጣ፡፡ ይህችን የተረገመች እንጨት እንዲህ ብሎ አወገዛት፡- "በአፉ የጠጣት፣ በእጁም የያዛት፣ የዘራት፣ የሸጣት፣ የገዛትም የጥምቀት ልጅ አይደለም፤ በሥጋው አይጠቀምም፣ ነፍሱም ወደ ሲዖል ትወርዳለች፡፡ ልጄ የሆነ ግን መድኃኔዓለምንና ኪዳነ ምሕረትን ያክብር፡፡ ጥንባሆንም አይጠጣ› አለ፡፡ የዚህ ጻዲቅ በረከቱ ያልታዘዝንውን ከመብላት ይጠብቀን አሜን" በማለት ተአምረ መድኃኔዓለም ወገድለ መባዓ ጽዮን ነገረ ጥንባሆን በሰፊው ዘግቦታል፡፡ በሌላም በኩል ትንባሆን በተመለከተ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ የሰጣቸው ቃልኪዳን በራሳቸው በዘርዐ ቡሩክ ገድል ላይ የተጻፈውን ወደፊት እናያለን፡፡ እንዲሁም ይህችን የተረገመች ዕፅ የሚጠቀሙባት ሁሉ የሰይጣን ማደሪያዎች እንደሚሆኑና ክፉውንም ሁሉ እንደሚያሠሩት በሌላም ቦታ በአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ገድል ላይ በሰፊው ተጽፏል፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱሳን_ሰባቱ_ደቂቅ

ዳግመኛም በዚህች ቀን ስማቸው አርሰሌዳስ ዱአሚዶስ አውጋንዮስ ድሜጥሮስ ብርጥስ እስጢፋኖስ ኪራኮስ የተባሉ ሰባቱ ደቂቅ አረፉ።

እሊህ ቅዱሳንም ሀይማኖታቸው ለቀና ለታላላቅ የሀገር ሰዎች ልጆቻቸው ናቸው እነርሱም ክርስቲያኖች እንደሆኑ በከሀዲ ንጉስ ዳኬዎስ ዘንድ ሰዎች ነገር ሰሩባቸው ወደርሱም አስቀርቦ ለጣኦት እንዲሰግዱ ግድ አላቸው እምቢ ባሉትም ጊዜ ከልባቸው ጋር ይመክሩ ዘንድ ቀጠሮ ሰጣቸውና እርሱ ወደ ተግባሩ ሄደ።

እሊህ የተባረኩ ሰባቱ ደቂቅም ወደ ቤታቸው ሄዱና ገንዘባቸውን ለድኆችና ለምስኪኖች በተኑ የቀረውንም ለስንቃቸው ይዘው ሄዱ ከከተማውም በስተምስራቅ በዋሻ ውስጥ ዱአሚዶስ ወደ ከተማ ሂዶ ምግባቸውን በመግዛት የሚያገለግላቸው ሆነ የሰማውንም ነገር ይነግራቸዋል።

ንጉስ ዳኬዎስም ከሄደበት በተመለሰ ጊዜ እሊህን ሰባት ልጆች ፈለጋቸው በዋሻ ውስጥ ተሸሽገው እንዳሉ በነገሩት ጊዜ የዋሻውን አፍ በደንጊያ እንዲደፍኑ አዘዘ የእነዚህንም ቅዱሳን ነፍሳቸውን በተኙ ጊዜ ጌታችን ወሰደ።

ሶስት መቶ ሰባ ሁለት አመትም እንዲአንቀላፉ አደረጋቸው ከንጉስ አሽከሮችም ስማቸው ቴዎድሮስና መቅዶስዮስ የተባሉ ሁለት የእርሳስ ሰሌዳዎች ወስደው የእሊህን የሰባቱ ደቂቅን ዜናቸውንና የዘመኑን ቁጥር ፅፈው ቀርፀው ከዋሻው አፍ አኖሩት።

ከዚህም በኃላ ዳኪዎስ ሞተ እስከ ደጉ ንጉስ እስከ ቴዎዶስዮስ ዘመነ መንግስት ብዙ ነገስታት ነገሱ በዚህም ደግ ንጉስ ዘመን ትንሳኤ ሙታን የለም የሚሉ ከሀዲያን ሰዎች ተነሱ እሊህም ሰባቱ ደቂቅ የሚነቁበት ጊዜ ሲቀርብ ለበጎቹ ማደሪያ ሊአሰራ ሽቶ ደንጊያ እየፈለገ የዋሻቸውን አፍ አንድ መኮነን ከፈተው።

እሊህ ቅዱሳንም በሶስት መቶ ሰባ ሁለት አመት በነቁ ጊዜ ምግባቸውን ይገዛ ዘንድ ዱአሚዶስን ላኩት የአገር ሰዎችም የዳኬዎስ ስም የተፃፈበትን ዲናር በእጁ ውስጥ በአዩ ጊዜ የተሸሸገ የወርቅ ሳጥን ያገኘ መስሎአቸዋልና ይዘው ወደዳኞቹና ኤጲስቆጶሳት አቀረቡት በመረመሩትም ጊዜ እነርሱ ሰባት ልጆች እንደሆኑ ነገራቸው።

በሄዱም ጊዜ ፊታቸው እንደ ፀሀይ ሲበራ አገኙአቸው ኤጲስቆጶሱም የእርሳስ ሰሌዳ አየ አንስቶም በላዩ የተፃፈውን ዜናቸውንና የዘመኑን ቁጥር አነበበ በዳኬዎስ ዘመን እንዳንቀላፉ ህዝቡ ሰምተው እጅግ አደነቁ እግዚአብሄርንም አመሰገኑት።

ከዚህም በኃላ ወደ ንጉስ ቴዎዶስዮስ ላኩ እርሱ መጥቶ እጅ ነሳቸው ከእነርሱም ተባረከ ከሰራዊቱ ጋር ከተነጋገሩም በኃላ ሁሉንም ባርኳቸውና በምድር ላይ ተኙ ነፍሳቸውንም በእግዚአብሄር እጅ ሰጡ በዚያችም ዋሻ ውስጥ ቀበሩአቸው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አባ_ነካሮ

በዚችም ቀን አባ ነካሮ አረፈ ይህም ቅዱስ ሰው ሳያውቀው በስውር የሚጋደል ሆነ እርሱም ከምንጣፉ በታች እሾህ ይጎዘጉዛል ጤና አግኝቶ እንዳይተኛ ነው በቀንና በሌሊትም ለፀሎት ይተጋ ነበር።

ከትሑትነቱም የተነሳ የበር ጠባቂ አደረጉት ።በዚያም ገዳም በመንፈስ ቅዱስ የተሰወሩ ነገሮችን የሚያይ ባህታዊ መነኮስ አለ በአንዲትም ሌሊት በህልሙ በከፍታ ቦታ ላይ ቆሞ አየ ከበታቹም ፍሬው በየአይነቱ የሆነ አትክልት አለ ወንዞችም ከበውታል አባ ነካሮም በመካከላቸው ሆኖ በወዲያና በወዲህ ያጠጣቸው ነበር ።

ያ መነኰስም ወንድሜ ነካሮ ሆይ ይህ አትክልት የማን ነው አለው አባ ነካሮም እኔ የተከልኃት ናት ብሎ መለሰለት መነኩሴውም ከፍሬዋ ትሰጠኝ ዘንድ እሻለሁ አለው አባ ነካሮም ሶስት የሮማን ፍሬ ቆርጦ ሰጠው በልብሱም ቋጠረው።


አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ሳይጠመቁ ለሚሞቱ አሕዛብም ጭምር ትልቅ ቃልኪዳን የተሰጣቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ይኸውም በቅዱስ ገድላቸው ላይ እንዲህ ተብሎ ተጽፏል- "በሥራው ሁሉ ፍጹም የሆነና ገድሉ ያማረ ቅዱስ አባታችንን በአድማስ ራስ ቆሞ ምሥራቁንና ምዕራቡን፣ ሰሜኑንና ደቡቡን እንዲባርክ በአፉ እስትንፋስም የምሕረት እስትንፋስን እፍ እንዲል እስትንፋሱንም ከአድማስ እስከ አድማስ ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይደርስ ዘንድ እግዚአብሔር አዘዘው፡፡ በእግዚአብሔር በቅዱስ ስሙ ያልተጠመቁ አሕዛብ በእስትንፋሱ ምክንያትና የምሕረት እስትንፋስን እፍ እንዲል እስትንፋሱንም ከአድማስ እስከ አድማስ ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይደርስ ዘንድ እግዚአብሔር አዘዘው፡፡ በእግዚአብሔር በቅዱስ ስሙ ያልተጠመቁ አሕዛብ በእስትንፋሱ ምክንያት ልጅነት አግኝተው እንዲከብሩ በቃል ኪዳኑ ተማፅነው ሳይጠመቁ በሚሞቱበት ጊዜ "ይህ ከእኔ የተቀበልከው ቃልኪዳን ከጎኔና ከሰውነቴ እንደፈሰሰው ደሜ ይሁንላቸው" በማለት ለዓለም መድኃኒት አድርጎ ቃልኪዳን ሰጠው፡፡

ዳግመኛም በቅዱስ አባታችን ዘርዐ ቡሩክ ስም ከእግዚአብሔር ምሕረትን ለምነው በሚሞቱበት ጊዜ በውኃና በመንፈስ ቅዱስ እንደተጠመቁ ይሁንላቸው ብሎ ነገረው፡፡ በከበረና በገናና ስሙ የተጠመቁ ሕዝቡም በኃጢአታቸው በወደቁ ጊዜ በሥራቸውም በረከሱ ጊዜ በጻድቁ ጸሎት ቢማጸኑ በቃልኪዳኑ ቢያምኑ ይህ እስትንፋሱ የኃጢአት ማስተሠርያ ይሁናቸው ብሎታል፡፡ ጻድቁ አባታችንም የእግዚአብሔርን ትእዛዝ በሰማ ጊዜ ከዚያ በፊት ለሌሎች ያልተሰጠ ቃልኪዳን ተቀብሎ በአድማስ ላይ ቆመ፡፡ በዚያም ቆሞ መንፈሳዊ እስትንፋሱን በምድር ላይ እፍ አለ፡፡ ያም የሕይወት እስትንፋስ በአራቱ ማዕዘን ደርሶ በኃጢአታቸው መከራ የተቀበሉ ለበደላቸውም የተገዙ ሰዎች በፈጣሪያቸው ስም እንዲከብሩ ዓለሙን ሁሉ ባረከ" ይላል ቅዱስ ገድላቸው፡፡ ይህም የሚያሳያየው መድኃኔዓለም ክርስቶስ የሰውን ልጆች ምን ያህል እንደወደዳቸውና በትንሽ ምክንያት የመዳንን መንገድ ያዘጋጀላቸው መሆኑን ነው፡፡

ሌላው አቡነ ዘርዐ ቡሩክ እሳቸው በባረኳት ምድርና በልጆቻቸው ላይ ችግርና ርኀብ እንደማይደርስባቸው ቃልኪዳን የተሰጣቸው ድንቅ አባት ናቸው፡፡ ይኸውም በቅርቡ እንኳን በ1977ቱ የርሃብ ዘመን በግልጽ ስለታየ ታሪክ ይመሰክረዋል፡፡ በዚህ ወቅት ከወሎና ከሌሎችም ቦታዎች በርሃብ ተሰዶ ጎጃም ለመጣው የሀገራችን ሕዝብ የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ በረከት ከበቂ በላይ ነበር፡፡

ጻድቁ በጎጃም ባሕር ዳር አካባቢ ሁለት ቤተ ክርስቲያን አላቸው፡፡ የዓባይ ምንጭ መነሻ የሆነው ፈለገ ግዮን ግሽ ዓባይ ከባሕር ዳር ከተማ 174 ኪ.ሜ የሚርቅ ሲሆን ከባሕር ዳር ቲሊሊ፣ ከቲሊሊ ሠከላ በመሳፈር በቦታው ላይ ለብዙ ዘመን ቆመው በመጸለይ ታላቅ ቃልኪዳን የተቀበሉበትን እጅግ ተአምረኛና ፈዋሽ የሆነውን ጸበላቸውን ማግኘት ይቻላል፡፡ ቦታው መጽሐፋቸውን ለዓባይ ወንዝ አደራ የሰጡበት ነው፡፡

ሌላኛው ቤተ ክርስቲያናቸው ከባሕር ዳር የሁለት ሰዓት የመኪና መንገድ ርቀት ላይ በምትገኘውና አዴት በምትባለው ቦታ የሚገኘው ነው፡፡ የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ መካነ መቃብራቸውና ከሰማይ የወረደላቸው መስቀል እዚህ ይገኛሉ፡፡ ቦታውን የረገጠ ሁሉ ከመካነ መቃብራቸው ላይ እምነት ይወስዳል፣ በመስቀሉም ይባረካል፡፡ ነገር ግን ጻድቁ በቃል ኪዳናቸው መሠረት በዚህ መስቀላቸው የተባረከ ሁሉ ዲቁናን፣ ክህነትን መቀበል ስለሚችል ሴቶች አይባረኩበትም፡፡ መካነ መቃብራቸው ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ከመቅደሱ ውጭ የሚገኝ ሲሆን ከመቃነ መቃብራቸው ላይ ያለው አፈር ሁልጊዜ እየፈላ መጠኑ ይጨምራል፡፡ ይህን የእምነቱን አፈር ቢዝቁት አያልቅም፣ ባዶ እንኳን ቢደረግ በተአምራት ሞልቶ ይገኛል፡፡ ለብዙ ሕመምተኞች ፍጹም ፈውስ የሆነው ይህ እምነት አጠቃላይ ሁኔታው ለዕይታ አመቺ ስለሆነ ይህንን ማንኛውም ሰው ወንዶችም ሆኑ ሴቶች ማየትና እምነቱን ወስደው መጠቀም ይችላሉ፡፡

ጻድቁ አባታችን በ482 ዓመታቸው በዚህች ዕለት ጥር 13 ቀን በታላቅ ክብር ያረፉበት በዓላቸው በድምቀት ይከበራል፡፡ በዕረፍታቸው ዕለት ከቤተ ክርስቲያኑ አደባባይ ላይ አትሮንስ ወጥቶ ገድላቸው ይነበባል፡፡ ገድላቸው ሲነበብም ከአትሮንሱ ሥር ሰባት ጠርሙሶችና አንድ ማሰሮ ይቀመጥና በጠርሙሶቹ ውስጥ አንድ አንድ ስኒ ውኃ ይደረግባቸዋል፡፡ የአባታችን ቅዱስ ገድላቸው ሲነበብ ውኃው ይፈላል፣ ገድሉ ተነቦ እንዳለቀ ጠርሙሶቹና ማሰሮው በተአምራት ተሞልተው ይገኛሉ፡፡

ጌታችን ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ትንባሆን ስለሚጠጡ ሰዎች ታላቅ ምሥጢርን እንደነገራቸው በቅዱስ ገድላቸው ላይ ተጽፏል፡፡ ቅዱስ አባታችን በየቀኑ ለሰባት ሰዓት ያህል በሲኦል ውስጥ ቆመው በመጸለይ ብዙ ነፍሳትን ከእሳት ያወጡ ነበር፡፡ አንድ ቀን ብዙ ነፍሳትን ካወጡ በኋላ አንዲት ነፍስ ግን ከሲኦል ግደግዳ ጋር እንደ ሰም ተጣብቃ እምቢ አለቻቸው፡፡ አባታችንም ያቺን ነፍስ አወጣለሁ ሲሉ ቆመው ይጸልዩበት የነበረው የሲኦል እሳት አሁን ያችን ነፍስ አወጣላሁ ባሉ ሰዓት ግን አቃጠላቸው፡፡ እሳቸውም ያችን ነፍስ እዚያው ሲኦል ጥለው በመውጣት ጌታችንን "የዚያች ነፍስ ኃጢአቷ ምንድን ነው?" አሉት፡፡ የዚህን ጊዜ ነው ጌታችን ትንባሆን ስለሚጠጡ ሰዎች ታላቅ ምሥጢርን የነገራቸው፡፡ ይኸውም አባ ሐዊ የሚባሉ ጻድቅ ያስተላለፉትን ውግዘትና ግዝት የጸና እንደሆነ ነው ጌታችን ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ የነገራቸው፡፡

ዝርዝር ታሪኩም በድርሳነ መድኃዓለም ላይ እንዲህ ተጽፎ ይገኛል፡- ትንባሆ የሚጠጡ ሰዎች ለምን ለማቆም እንደሚቸገሩና መጨረሻቸውም ምን እንደሆነ፡- "ይቅርታውና ምሕረቱ ከሁላችን የጥምቀት ልጆች ጋር ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መድኃኔዓለም ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡- አባታችን ዘርዓ ቡሩክ መድኃኔዓለምን እንደወደደውና በየወሩ በሃያ ሰባት ቀን በዓሉን እንደሚያከብር በአሥራ ስድስት ቀንም ኪዳነ ምሕረትን እንደሚያከብር እነሆ እንነግራችኋለን፡፡ ባለሟልነትን ባገኘ ጊዜና መድኃኔዓለም የእሳት ፈረስንና የመስቀል ምልክት ያለበት የወርቅ በትርን በሰጠው ጊዜ "ወደ ሲዖል ሂድና መሸከም የምትችለውን ያህል ነፍሳትን አውጣ› አለው፡፡ ሄዶም ወደ ሲዖል ገባ፣ ነፍስ በነፍስ ላይ እንደ ንብ እየተጨናነቁ በሰውነቱ ላይ ታዘሉ፡፡ ነፍሳትንም ይዞ ሲወጣ አንድ ኃጢአተኛ ‹ዘርዓ ቡሩክ ብቻዬን ቀረሁ፣ አውጣኝ" አለው፡፡ ዘርዓ ቡሩክም ወደ እርሱ ተመልሶ ሳበው፡፡ ሰም ከፈትል ጋራ እንደሚጣበቅ ከሲዖል ጥልቅ ጋራ ተጣብቆ እምቢ አለው፡፡ የእሳቱ ነበልባልም ዘርዓ ቡሩክን አቃጠለው፣ እርሱም ተወው፡፡ ክብር ይግባውና እነዚያን ነፍሳት ይዞ ወደ ጌታው ወደ መድኃኔዓለም ሄደ፡፡

ሄዶም "ጌታዬ ሆይ! አንዲት ነፍስ ስሜን እየጠራች ቀርታለች ማርልኝ" አለው፡፡ መድኃኔዓለምም "ዘርዓ ቡሩክ ሆይ! በእኔ ዘንድ ባለሟልነትን ብታገኝ ትንባሆ የሚጠጣውን ማርልኝ ትለኛለህን?" አለው፡፡ እርሱም "ጌታዬ ሆይ! ይህቺ እንጨት በምን ትከፋለች?፣ ከሁሉ ኃጢአትስ በምን ትበልጣለች?" አለው፡፡ ወይቤሎ መድኅን ኢሰማዕከኑ ግብራ ለዛቲ ዕፅ ዘከመ ዘርዓ ሰይጣን ውስተ ገራህተ ዓለም፡፡ መድኃኔዓለምም "የዚህችን እንጨት ሥራ በዓለም እርሻ ሰይጣን እንደዘራት አልሰማህምን?" አለው፡፡ እነሆም እንነግራችኋለን፣ ስሙ ሐዊ የሚባል የፈጣሪውንም ሕግ የሚጠብቅ አንድ መምህር ነበረ፡፡ በዓርብ ቀንም ወደ ሰማይ ይሔዳል፤ በቀዳሚት ሰንበትና በእሑድ ከፈጣሪው ጋር ይነጋገራል፡፡ በሰኞ ቀንም ወደ ቦታው ይመለሳል፡፡ ለሀገር ሰዎችም በጉባኤ ይነግራቸዋል፣ በአዋጅ ነጋሪ ቃልም


#ጥር_13

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም

ጥር አስራ ሶስት በዚች ቀን #አቡነ_ዘርዓ_ቡሩክ ኢትዮዽያዊ አረፉ፣ #ቅዱሳን_ሰባቱ_ደቂቅ አረፉ፣ #አባ_ነካሮ አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አቡነ_ዘርዐ_ቡሩክ_ኢትዮዽያዊ

ጥር አስራ ሶስት በዚች ቀን አቡነ ዘርዓ ቡሩክ ኢትዮዽያዊ እረፍታቸው ነው። ከመወለዳቸው አስቀድሞ ትንቢት ተነግሮላቸው ነበር፡፡ አባታቸው ደመ ክርስቶስ ዐይነ ሥውር የነበረ ሲሆን አቡነ ዘርዐ ቡሩክ በተወለዱ ጊዜ ግን የአባታቸውን ዐይን አብርተውለታል፡፡ አባታችን ዘርዐ ቡሩክ ገና በሰባት ዓመታቸው ነው ረቡዕና ዓርብ መጾም የጀመሩት፡፡ በዚሁ በሰባት ዓመታቸውም ‹‹ይህን ዓለም ክፋቱን እንዳላይ ዐይኖቼን አሳውርልኝ›› በማለት ዐይናቸውን እንዲያጠፋላቸው አምላካቸውን ለምነው እንደፈቃዳቸው ዐይነ ሥውር ሆነዋል፡፡ ነገር ግን ከሰባት ዓመት በኋላ በ12 ዓመታቸው ጌታችን "ለዓለም የምታበራ ብርሃን አደርግሃለሁና ዐይንህም ይብራ" በማለት ዐይነ ብርሃናቸውን መልሶላቸው እንዲያዩ አድርጓቸዋል፡፡ በዚህም ዕድሜያቸው (በ12 ዓመታቸው) ሰባቱንም አጽዋማት ይጾሙ ነበር፡፡

ከዚህም በኋላ ጌታችን የቅዱሳት መጻሕፍትን ምሥጢር ሁሉ ገለጠላቸው፡፡ መጻሕፍተ ብሉያትን፣ መጻሕፍተ ሐዲሳትን፣ መጻሕፍተ ሊቃውንትን፣ መጻሕፍተ መነኮሳትን፣ አዋልድ መጻሕፍትን ሁሉ ገልጦላቸዋል፡፡ ከሟርት መጻሕፍት በቀር ያስቀረባቸው ነገር አልነበረም፤ የቅዱስ ያሬድንም ዜማ እንዲሁ ገለጠላቸው፡፡
ጻድቁ ከሁሉ ቅዱሳን በበለጠ ሁኔታ ዐሥራ ሁለት ክንፍ የተሰጣቸው ሲሆን በ12 ክንፎቻቸውም የሰማይን ደጆች ሁሉ ገሃነመ እሳትንም አልፈው በመሄድ ቀጥታ በሥሉስ ቅዱስ ዙፋን ፊት ይቆሙ እንደነበር ቅዱስ ገድላቸው ይናገራል፡፡ እጅግ በሚደንቅና ከአእምሮ በላይ በሆነ ሁኔታ አባታችን ለሰባት ቀናት በየቀኑ ለሰባት ሰዓት ያህል በሲኦል ውስጥ ቆመው ይጸልዩ ነበር፡፡ ብዙዎቹ ቅዱሳን በምልጃቸው ነፍሳትን ከሲኦል ሲያወጡ ነው የምናውቀው እንጂ እንደ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ በሲኦል ውስጥ ገብቶ ጸሎት የጸለየ ጻድቅ እስካሁን እኔ አላጋጠመኝም፡፡

አቡነ ዘርዐ ቡሩክ እንደ አባታችን ተክለሃይማኖት ለጸሎት በመቆም ብዛት አንድ እግራቸው እስኪሰበር ድረስ በብዙ መከራ ተጋድለዋል፡፡ ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር መንበሩን ያጥኑ ዘንድ ከፈጣሪአቸው ታዘው አጥነዋል፡፡ ጌታችን ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ፍጥረታትን ከመፍጠር በቀር ያልሰጣቸው ሥልጣን የለም፡፡ "እግዚአብሔር ብፁዕና ቅዱስ ለሚሆን አባታችን ዘርዐ ቡሩክ "እኔ ከሥልጣኔ ሥልጣንን፣ ከክብሬም ክብርን፣ ከጥበቤም ጥበብን፣ ከተአምራቴም ተአምራትን፣ ከስጦታዬም ስጦታን፣ ከትዕግስቴም ትዕግስትን፣ ከፍቅሬም ፍቅርን፣ ከትሕትናዬም ትሕትናን፣ ከባለሟልነቴም ባለሟልነትን ሰጥቼሃለሁና ሁሉ ከሥልጣንህ በታች ሆኖ ይታዘዝልህ" የሚል እጅግ ድንቅ ቃልኪዳን ነው የሰጣቸው፡፡ ልዩ ልዩ ሀብታትን ሁሉ ሰጣቸው፡፡ "ለሥላሴ ከሚገባ ከስግደትና በቃልና በሥልጣን ፍጥረታትን ለመፍጠር በቀር ምንም ያልሰጠሁህ የለም" ብሎ ጌታችን በማይታበል ቃሉ እንደነገራቸውና ቃል እንደገባላቸው በቅዱስ ገድላቸው ላይ ተጽፏል፡፡ (የአባታችን ገድላቸው ከመጥፋቱ የተነሣ በአሁኑ ሰዓት አንዳንድ ነጋዴዎች አንዱን ፍሬ ከ3 ሺህ ብር በላይ እየሸጡት ነበር፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ ቲሊሊ የሚገኘው ገዳማቸው በድጋሚ አሳትሞታል፡፡

አቡነ ዘርዐ ቡሩክ በወቅቱ በነበረው ገዥ ፊት በሐሰት ተከሰው ለ5 ዓመታት ያህል በእስርና በእንግልት ሲኖሩ በእነዚህ ጊዜያት ሁሉ ምግብ የሚባል አይቀምሱም ነበርና ከእስር ሲፈቱ አምስት ዓመት ሙሉ ሲሰጣቸው ያጠራቅሙት የነበረው ምግብ ትኩስ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ያሳሰራቸውንም ንጉሥ ገና ሕፃን ሳለ እናቱ ልታስባርከው ወደ አባታችን ዘንድ ወስዳው ነበር፡፡ አቡነ ዘርዐ ቡሩክም ሕፃኑን ከባረኩት በኋላ ለእናቱ "ይህ ልጅሽ ወደፊት ይነግሣል በንግሥናው ዘመንም እኔን ያስርና ያንገላታኛል" ብለው ይህ እንደሚሆን አስቀድመው ትንቢት ተናግረው ነበር፡፡ እንዳሉትም ልጁ አድጎ ሲነግሥ ጭፍሮቹ "ንጉሥ ሆይ አንተን የማይወድ ለቃልህም የማይታዘዝ አንድ መነኩሴ አለ" በማለት ምንም እንኳን ንጉሡ ባያውቃቸውም በሐሰት ነገር ስለከሰሱለት በግዞት እንዲኖሩና እንዲታሰሩ አድርጓቸዋል፡፡ ጻድቁ በግዞት ሲወሰዱ "እነዚህን መጻሕፍቶቼን ለሰዎች አደራ ብሰጣቸው ይክዱኛል፣ ቤተ ክርስቲያን ባስቀምጣቸው ይጠፉብኛል" በማለት ሰባት መጽሐፎቻቸውን ለግዮን (ለዓባይ) ወንዝ አደራ የሰጡ ሲሆን ከ5 ዓመት በኋላ ከእስር ተፈተው ሲመለሱ በወንዙ አጠገብ እንደደረሱ ጸሎት ካደረጉ በኋላ "ግዮን ሆይ በእግዚአብሔር ፊት በአደራ የሰጠሁሽን መጽሐፎቼን ግሺ (ትፊ)" ብለው እጃቸውን ወደ ወንዙ ሰደው መጽሐፎቻቸው ሳይረጥቡና ሳይበሰብሱ ከወንዙ ውስጥ አውጥተዋቸል፡፡ እንዲያውም አቧራውን ከመጻሕፍቶቻቸው ላይ እፍ ብለው አራግፈውታል፡፡

በመጽሐፍ ቅዱስ እንደተጠቀሰው የጠለቀው ምሳር እየተንሳፈፈ ወደ ኤልሳዕ እንደመጣ ሁሉ አሁንም እንዲሁ የቅዱስ አባታችን መጽሐፎች አብሯቸው ከነበረውና ዘሩባቤል ከሚባለው ደቀ መዝሙራቸው ጋር ወዳሉበት ተንሳፈው ሊመጡ ችለዋል፡፡ መጽሐፎቻቸውንም አብሯቸው ለነበረው ደቀ መዝሙራቸው ካሳዩት በኋላ እንዲይዛቸው ሰጥተውታል፡፡

የግዮን ወንዝ "ግሺ ዓባይ" ወይም "ዓባይ" እየተባለ መጠራት የጀመረው አቡነ ዘርዐ ቡሩክ "ግዮን ሆይ በእግዚአብሔር ፊት በአደራ የሰጠሁሽን መጽሐፎቼን ግሺ (ትፊ)" ብለው እጃቸውን ወደ ወንዙ ሰደው መጽሐፎቻቸው ሳይረጥቡና ሳይበሰብሱ ከወንዙ ውስጥ ካወጡበት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ አባታችን በቦታው ላይ 30 ዓመት ሙሉ ቆመው ጸልየው ቦታውን የባረኩት ሲሆን ጌታችንም በቦታው ላይ ትልቅ ቃልኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ "ብፁዕ አባታችን ለግዮን ወንዝ መጽሐፎቹን በአደራ ሰጥተው በኋላም ከደቀ መዝሙራቸው ከዘሩባቤል ጋር መጽሐፎቹን ከግዮን ምንጭ ውስጥ ከተቀበለ በኋላ "በግዮን ውኃ ውስጥ ሳይረጥቡ በደረቅ መጽሐፎቼን የጠበቀ እግዚአብሔር ይመስገን" ብሎ ፈጣሪውን አመሰገነ፡፡ "ያንጊዜም በውስጥሽ ታላቅ ድኅነት ይደረግብሽ፣ ሕመምተኞች ሁሉ ይዳኑብሽ፣ መካኖች ይውለዱብሽ" ብሎ ግዮንን በቃሉ መረቃት፣ በእጁም ባረካት፡፡ ብፁዕ አባታችንም በዚህች ቦታ ላይ ፈውስ፣ ረድኤት፣ በረከት ይደረግብሽ ብሎ ብዙ ዘመን ቆሞ ጸለየ፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰምቶ "ይህ በረከት፣ ረድኤት፣ ሀብት፣ ፈውስ እንደወደድህ እስከዘለዓለሙ በዚህ ቦታ ይሁንልህ" አለው" ተብሎ ነው በቅዱስ ገድላቸው ላይ የተጻፈው፡፡

ጻድቁ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ሌላው የሚታወቁበት "ብሄሞትና ሌዋታን" የተባሉ እጅግ ግዙፍ የሆኑ ሁለት ዘንዶዎችን ጥርሳቸውን ቆጥረው ምላሳቸው ሲጣበቅ የዓለም ፍጻሜ እንደሚሆን አስቀድመው ያወቁ ድንቅ ነቢይ የሆኑ አባት በመሆናቸው ነው፡፡ እነዚህም እጅግ ግዙፍ የሆኑ ሁለት እንስሳት ሴትና ወንድ ሆነው ምድርን እንደመቀነት ከበው የያዙ ናቸው፡፡ ዝርዝር ታሪካቸው በመጽሐፈ አክሲማሮስ (ሥነ ፍጥረትን በሚያስረዳው መጽሐፍ) ላይ በስፋት ተጠቅሰዋል፡፡




የወይ ብላ ማርያምን ታቦት ወደ መንበሯ እንዳትመለስ ፖሊስ ከለከለ።
የሺ ደበሌ አካባቢ የምትገኘውን የወይ ብላ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ዛሬ ወደ መንበሯ ስትመለስ ፖሊስና በአካባቢው ያሉ ወጣቶች በፈጠሩት ግርግር ሰላምን የሚያደፈርስ ችግር በመከሠቱ ታቦቱ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እንዳያልፍ ተደርጓል። በመሆኑም አሁን ወደ ኋላ ተመልሶ በቀራንዮ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን እንዲገባ ተደርጓል።
በሥፍራው ከነበሩ የዐይን እማኞች ምስክርነት ማወቅ እንደተቻለው ፖሊስ በአንገታቸው እና በክንዳቸው ላይ ባሠሯቸው፣ በቲሸርት መልክ ያሰፉትን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለም ያላቸውን ነገሮች ሁሉ ካላወለቃችሁ አታልፉም በማለት ፖሊስና ፖሊስ ያደራጃቸው ያካባቢው ወጣቶች በፈጠሩት ማዋከብ ነው ችግሩ የተከሰተው። የቤተ ክርስቲያን አርማ ያለበትን ሰንደቅ እንጂ ሌላ ነገር ያልያዙት ታቦት የሚያጅቡ ምእመናን ወደ ኦሮሚያ ክልል ማለፍ የምትችሉት የለበሳችሁትን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቲ ሸርት ካውልቃችሁ ብቻ ነው የሚለውን የፖሊስ ሕገ ወጥ ትእዛዝ በመቃወማቸው ለድብደባ ተዳርገዋል። ፖሊስ በምእመናንን ላይ አስለቃሽ ጭስ ተኩሷል። የተጎዱ አገልጋዮች እና ምእመናን እንዳሉም የዐይን እማኞቹ ተናግረዋል።

ጴጥሮሳውያን የቤተ ክርስቲያን ክብርና መብት አስጠባቂ ኅብረት




በዓለ ጥምቀት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።



በዓለ ጥምቀት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሚከበሩት በዓላት አንዱና ዋናው የጥምቀት በዓል ነው። የጥምቀት በዓል ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፍጹም ትሕትና ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ተጉዞ በአገልጋዩ በቅዱስ የሐንስ እጅ የተጠመቀበትን ዕለት የምናስብበት ከጌታችን ዓበይት በዓላት አንዱ ገናና በዓል ነው፡፡

በአፍ መነገሩ፣ በልብ መታሰቡ፣ ምስጋናውም ሁሉ ከፍ ከፍ ይበልና ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕለቱን ተፀንሶ ዕለቱን ተወልዶ ማድግና የወደደውን ሁሉ ማድረግ ሲቻለው ፍጹም አምላክ ብቻ ያይደለ ፍጹም ሰውም በመሆኑ ዘመን የማይቆጠርለት እርሱ ከብቻዋ ከሐጢአት በቀር በሰው ሥርዓትና ጠባይዕ ቀስ በቀስ በማደጉ 30 ዓመት ሲሆነው ሊጠመቅ ወደርዳኖስ ወንዝ ሔደ ትብሎ ዘመን ተነገረለት፡፡ ዮርዳኖስ እንደደረሰ ጌታችን ተለይቶ የሚታወቅበት ምልክት ሳይኖረው ቅዱስ ዮሐንስ በመገልጥ አወቀው። ይህንንም ራሱ ሲመሰክር «እኔም አላውቀውም ነበር፥ ዳሩ ግን በውኃ አጠምቅ ዘንድ የላከኝ እርሱ፦ መንፈስ ሲወርድበትና ሲኖርበት የምታየው፥ በመንፈስ ቅዱስ የሚያጠምቅ እርሱ ነው አለኝ» (ዮሐ. ፩፥፴፫) ይላል። ዮሐንስ የንስሐ ጥምቀት በውሃ ያጠምቅ እንደነበረና ልጅነት የሚገኝበት የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ምሉዑ የድኅነት ምሥጢር የሚገኘውና የሚታወቀው ግን ከእርሱ በኋላ ከሚመጣው ከክርስቶስ የተነሣ እንደሆነ መስክሯል።

ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ባመሰገነበት በአንቀጸ–ብርሃን ድርሰቱ የአብን ነገር የነገረን ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ የውልድንም ነገር አጎልቶና አስፍቶ የነገረን አብ እንደሆነ ሲያስረዳ «ልጅህ ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አንተ ብቻ አባቱ እንደሆንክ እርሱም ብቻ ልጅህ እንደሆነ አስተማረን።በሰማይ እናት በምድርም አባት የለውም ብለን እናምናለን። መምጣቱን ካአባቱና ከእውነት መንፈስ ከጰራቅሊጦስ በቀር የሚያውቅ ሳይኖር ከሰማይ ወረደ ብለን እናምናለን» ሲል ተናግሯል። ይህም የጥምቀት መንሠረቱ ነው። አባቱን አብን ሕይወቱን መንፈስ ቅዱስንና እሱን ወልድን ማወቅ እና ማመን ከሌለ በውሃና በመንፈስ ቅዱስ አንዲቱን ጥምቀት መጠመቅና ልጅነትን ማገኘት አይቻልም።

ቅዱስ ዮሐንስ በመንፈስ ቅዱስ ተልኮ «እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸ ከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል» (ማቴ.፫፥፲፩)። እያለ የላቀ ጥቅም የምታሰጠው ጥምቀት ከእርሱ የትገኝ የጌታችንን መምጣት በጉጉት እየጠበቀ፣ ትንቢት እየተናገረ፣ የተጠራለትንና የተመረጠለትን ሥራውን እያከናወነ ሕዝቡን እያዘጋጀ ሳለ አስቀድሞ የተናገረለት ክርስቶስ በሥፍራው ተገኝቶ የጽድቅ ሥራውን ተመለከተከለት ወደደለት። አጥምቀኝ ብሎ ሲጠይቀው እውነተኛ ሥራውን እንደወደደለትና እንዳጸደቀለት ያጠይቃል።

ዛሬ እያንዳንዳችን ወደምንገኝምበት ዮርዳኖስ ጌታችን ቢመጣና ቢጎበኘን በቅዱስ ዮሐንስ ምትክ የተሾመለትን ሥራ፣ የተጠራለትን አገልግሎት በተሰጠው ጸጋ እያከናወነ የሚያገኘው ነቢይ፣ ሐዋርያ፣ ጳጳስ፣ ካህን፣ ዲያቆን፣ ዘማሪና ምእመን ያገኝ ይሆን? እውነቱን እንናገር ካልን እንዲያ ሲያደርግ የሚገኝ በጎ አገልጋይ በጭንቅ ካልሆነ በቀላሉ በሩቅ ካልሆነ በቅርቡ ማግኘት ከባድ ነው


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Video is unavailable for watching
Show in Telegram








አራተኛ ተአምር ስለ ሥራው ሁሉ የሚቈጥር ጠንቋይ ከቶ በአቈጣጠሩ የማይሳሳት ቅዱስ ባስልዮስም በታመመ ጊዜ የሚሞትበትን ጊዜ ዐውቆ ይህን ጠንቋይ ጠርቶ መቼ እሞታለሁ አለው ጠንቋዩም ማታ ነፍስህ ከሥጋህ ትለያለች አለው። የከበረ ባስልዮስም እስከ ጥዋት ካልሞትኩ ክርስቲያን ትሆናለህን አለው ጠንቋዩም አዎን አለ። የከበረ ባስልዮስም የክብር ባለቤት ጌታቻንን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመነውና በዕድሜው ላይ ሦስት ቀኖችን ጨመረለት ያም ጠንቋይ አመነ ከቤተሰቦቹ ሁሉ ጋር ተጠምቆ ክርስቲያን ሆነ።

አምስተኛ ተአምር ክርስትናውን ክዶ ክህደቱንም ጽፎ ለሰይጣን ስለ ሰጠ ባርያ ዜና ነው ቅዱስ ባስልዮስም በዋሻ ውስጥ ይህን ባርያ ዘጋበት የክህደቱንም ደብዳቤ ሰይጣን እስከ መለሰለት ድረስ ስለርሱ ወደ እግዚአብሔር ለመነ ያንንም ባርያ አዳነው።

ስድስተኛ ተአምር ድንግል ስለሆነ ቄስ ዜና እርሱም ሚስቱም ከእነርሳቸውም በቊስል ደዌ የታመመ አለ የከበረ ባስልዮስም እንደ አወቀባቸው በዚያችም ሌሊት ከታመመው ዘንድ እንደ ተኛ ስለርሱም እግዚአብሔርን እንደለመነውና ከደዌው እንዳዳነው።

ሰባተኛ ተአምር ስለ አንዲት የከበረች ሴት ዜና እርሷም ኋጢአቷን ሁሉ ጽፋ በክርታስ አሽጋ ኃጢአቷ ሁሉ እስከሚደመሰስ እንዲጸልይላት ቅዱስ ባስልዮስን ለመነችው ከአንዲት በደል በቀር ኃጢአቶቿ ሁሉ እስከተደመሰሱ ድረስ ጸለየላት። ወደ ቅዱስ ኤፍሬምም እንድትሔድ አዘዛት ቅዱስ ኤፍሬምም ወደ ቅዱስ ባስልዮስ ሳይሞት ፈጥነሽ ተመለሽ የካህናት ሁሉ አለቃ ስለሆነ የሚደመስስልሽ እርሱ ነውና ብሎ ነገራት በተመለሰችም ጊዜ ሙቶ በዐልጋ ተሸክመው ወደሚቀብሩበት ሲወስዱት አገኘችው መሪር ልቅሶም አልቅሳ ያንን ክርታስ ከአስክሬኑ ላይ ጣለችው በደሏም ተደመሰሰላት ሕዝቡም ሁሉ ይህን ድንቅ ሥራ አይተው እጅግ አደነቁ ለሚፈሩት ይህን ታላቅ ጸጋ የሚሰጥ እግዚአብሔርን አመሰገኑት።

ይህ የከበረ ባስልዮስ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ከጻፍነው ሌላ ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶችን አድርጓል ብዙዎችንም ተግሣጾችንና ድርሳናትን ለመነኰሳትም ትምህርቶችን ደርሷል። ከብሉይና ከሐዲስም አምላካውያን የሆኑ ብዙ መጻሕፍቶችን ተርጒሟል ሥርዓቶችንም ሠራ እነርሱም በሁሉ ቦታ ይገኛሉ ከዚህም በኋላ በሰላም አርፎ በክብር በብዙ ምስጋና ቀበሩት።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ሰማዕት_ቅድስት_አርሴማ

ዳግመኛም በዚህች ዕለት የታላቋ ሰማዕት የቅድስት አርሴማ ልደቷ ነው፡፡ የቅዱስት አርሴማ አባቷ ቴዎድሮስ ከሌዋውያንና ከኃያላን ነገሥታት ወገን ሲሆን እናቷ አትኖስያ ደግሞ ከጳጳሳት አለቆች ወገን ናት፡፡ ወላጆቿ በሃይማኖት በምግባር ያጌጡ በበጎ ትሩፋት የተመሰገኑ ደጋግ ቅዱሳን ናቸው፡፡ በጾም፣ በጾሎት፣ በምጽዋትና ዓሥራት በኩራትን በማውጣት በመንፈሳዊ ሥራ ሁሉ እየተጉ ቢኖሩም ነገር ግን እስክ እርጅናቸው ዘመን ድረስ ልጅ ስላልነበራቸው ያዝኑ ነበር፡፡ እናቷ ቅድስት አትኖስያ እንደ ነቢዩ ሳሙኤል እናት ሐና ጠዋት ማታ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በእግዚአብሔር ፊት ታለቅስ ነበር፡፡ እግዚአብሔር የልቧን ፈቃድ ይፈጽምላት ዘንድ ወደደና የቂሣርያውን ሊቀ ጳጳሳት ልድዮስን ስለ እርሷ ይጸልይላት ዘንድ አዘዘው፡፡

ሊቀ ጳጳሳቱም ስለ ቅድስት አትኖስያ ጸለየላት፡፡ እግዚአብሔር አምላክም የሊቀ ጳጳሳቱንና የቅድስት አትኖስያን ጸሎት ሰምቶ መልኳ እጅግ ያማረችን ሴት ልጅ ቅድስት አርሴማን ሰጣት፡፡ እናቷም እየተንከባከበች አሳድጋት ዕድሜዋ ከፍ ሲል አምላክን በወለደች በእመቤታችን ስም ወደተሠራች ቤተ ክርስቲያን ታገለግል ዘንድ ሰጠቻት፡፡ ቅድስት አርሴማ ወጣት በሆነች ጊዜ ወላጆቿ ባል ያጋቧት ዘንድ ወደዱ ነገር እርሷ ይህንን ፈጽሞ አልወደደችምና ወላጆቿን "እኔ የሰማያዊው የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ እንጂ ምድራዊ ሙሽራ አይደለሁም" አለቻቸው፡፡

ቅድስት አርሴማ ከእርሷ በፊትም ሆነ ከእርሷ በኋላ በመልክና በውበት የሚመስላት የለም፡፡ ይህን ዓለም እንደትቢያ በመቁጠርና ፍጹም በመናቅ ጌታችንን ከተከተሉት ቅዱሳት ደናግል አንስት ውስጥ በመልክና በውበት ቅድስት አርሴማን የሚመስል የለም፡፡ አምላክን ከወለደች ከእመቤታችን በቀር የሚበልጣት ማንም የለም፡፡ እርሷም በምግባር በሃይማኖት ያጌጠች በመንፈሳዊ ተጋድሎ የበረታች በትሩፋት የበለጸገች ናት፡፡ ብሉይን ከሐዲስ አጠናቃ ተማረች፡፡ የአገሮችንም (የሮምያን፣ የጽርዕን፣ የሶርያን፣ የኪልቅያን) ቋንቋዎች ታውቅ ስለነበር ቅዱሳት መጻሕፍትንም ወደ ተለያዩ አገራት ቋንቋዎች ትተረጉማለች፡፡

ቅድስት አርሴማ 15 ዓመት በሆናት ጊዜ ከሃዲውን ዲዮቅልጥያኖስን ሰይጣን አስነሥቶት ነገሠ፡፡ ከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን እርሱ መልኳ ውብ የሆነ ብላቴና ድንግል ሊአገባ ሽቶ በየሀገሩ ሁሉ ሒደው መርጠው ያመጡለት ዘንድ አሽከሮቹን አዘዘ። ይችንም የሚመስላት የሌለ ቅድስት አርሴማን በሮሜ አገር በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ አገኙዋት። ሥዕሏንም ሥለው ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ላኩለት ንጉሡም ሥዕሏን በአየ ጊዜ እጅግ ደስ አለውና ለሠርግ እንዲመጡ ወደ መኳንንቱ ላከ።

እሊያ ደናግልም ይህን ነገር በአወቁ ጊዜ ይረዳቸው ዘንድ ድንግልናቸውንም ይጠብቅ ዘንድ አልቅሰው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ። ከዚህም በኋላ ተነሥተው በሥውር ሸሹ የንጉሥ ድርጣድስ ግዛት ወደ ሆነ ወደ አርማንያ ሀገርም ደርሰው በአንድ ቦታ ተቀመጡ ከእርሳቸውም ጋር የተሰደዱ ቁጥራቸው ሰባ አምስት የሆነ ወንዶች፣ ሴቶችም ሠላሳ ዘጠኝ የሆኑ ከእርሳቸው ጋራ አሉ። ምግባቸውን አያገኙም ነበርና በታላቅ ችግር ውስጥ ኖሩ ከእነርሱም መብራት የምትሠራ አንዲት ሴት ነበረች ከእርሷም የእጅ ሥራ ከሚገኘው በየጥቂቱ ይመገባሉ።

ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም የከበረች አርሴማን በፈለጋት ጊዜ አላገኛትም ግን በአርማንያ አገር እንዳለች ስለርሷ ሰማ። ደግሞ ለአርማንያ ንጉሥ ለድርጣድስ ስለርሷ ከዲዮቅልጥያኖስ ሸሽታ እንደ መጣች የአርሴማን ሥራ ነገሩት እርሱም አንዱን የአርማንያ መኰንን ለእኔ ጠብቃት ወደ እኔም ላካት ብሎ አዘዘው።

ደናግሉም ይህን በሰሙ ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ተሠወሩ ወደ ንጉሥም ወነጀሉአቸው ንጉሡም ቅዱስት አርሴማን በክብር አድርገው ያመጧት ዘንድ አዘዘ እርሷም ወደ እርሱ መምጣትን እምቢ በአለች ጊዜ እየጎተቱ ወስደው ወደርሱ አደረሷት።

የቅድስት አርሴማንም ላህይና ደም ግባቷን በአየ ጊዜ ድንግልናዋን ሊያረክስ ሽቶ እናቷ አጋታን አባብላ እሺ ታሰኝለት ዘንድ አዘዛት አጋታም ወደርሷ ሒዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት። ዕወቂ ይህ ርኲስ አረሚ እንዳያረክስሽና ሰማያዊ ሙሽራሽን እንዳትተዪ እርሱም ክብር ይግባውና የእግዚአብሔር ልጅ ሕያው ክርስቶስ ነው።
ንጉሡም ይዞ ወደ እልፍኙ ሊአስገባት ከአደባባይ መካከል ተነሥቶ ድንግል አርሴማን ያዛት። በዚያንም ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለ ነበር በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ ያን ጊዜ አፈረ። ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧት ከዚህም በኋላ ደናግሉን ሁሉ ከእናታቸው አጋታ ጋር ይገድሏቸው ዘንድ አዘዘ።

አንዲት የታመመች ድንግል ነበረች በዐልጋዋ ላይም እንደተኛች ወደ ወታደሮች ጮኸች መጥተውም እንደ እኅቶቿ ራሷን ቆረጡ ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነዚያንም ከሮሜ አገር አብረው የመጡ ወንዶችን ገደሏቸው ቁጥራቸውም ሰባ አምስት ናቸው ሥጋቸውም በተራራ ላይ የተጣለ ሁኖ ቀረ።


ኤልያስም ሕዝቡን የእግዚአብሔር ነቢይ እኔ ብቻዬን ቀርቻለሁ የጣዖቱ ነቢያት አራት መቶ ሃምሣ በዛፉም መስገጃ የተሾሙት እነሆ አራት መቶ ናቸው። ሁለት ወይፈኖችንም ይስጡን እነርሳቸውም አንዱን መርጠው አርደው በየብልቱ አወራርደው በዕንጨቶቹ ላይ ይከምሩት እሳትን ግን አያንድዱ። እኔም ሁለተኛውን ወይፈን አርዳለሁ እሳትንም አላነድም እነርሱም የጣዖቶቻቸውን ስም ይጥሩ እኔም የፈጣሪዬን የእግዚአብሔርን ስም እጠራለሁ ከእርሱም እሳትን ከሰማይ ያወረደ ፈጣሪ ነው አላቸው ሕዝቡም መልካም ቃል ተናገርክ ብለው መለሱለት።

እነርሱም የመረጡትን በሬ ለአማልክቶቻቸው አስቀድመው መሥዋትነትን አቀረቡ ግን የተቀበላቸው የለም ኤልያስም መሥዋዕቱን በአቀረበ ጊዜ ከእግዚአብሔር ታዝዛ እሳት ከሰማይ ወርዳ መሥዋዕቱን ዕንጨቱን በጒድጓድ ያለ ውኃውንም አቃጠላቸው መሬቱንም ላሰችው።

ኤልያስም ሕዝቡን እንዲህ አላቸው ጣዖቱን የሚያገለግሉ ነቢያተ ሐሰትን ያዝዋቸው ከእነርሱም የሚያመልጣችሁ አይኑር አላቸው ሕዝቡም ነቢያተ ሐሰትን ያዙ ኤልያስም ቂሶን ወደ ሚባል ወንዝ አውርዶ እየወጋ ጣላቸው። ከዚህም በኋላ ዝናብ ዘነበላቸው ደስ ብሏቸውም ምስጉን እግዚአብሔርን አመሰገኑት።

አክአብም ለሚስቱ ኤልዛቤል ኤልያስ ያደረገውን ሁሉ አሳፋሪዎች ነቢያቶችንም በጦር ወግቶ እንደ ገደላቸው ነገራት ባልኖርባት አንተ ኤልያስ ኑረህባት አንተ ባትኖርባት እኔ ኤልዛቤል ኑሬባት ነገ ይህን ጊዜ ሰውነትህን ከነሳቸው እንዳዱ ሰውነት ባላደርጋት የያዘችውን ጥላ አማልክቶቼ እንዲህ ይጣሉኝ እንዲህም ይግደሉኝ ብላ ወደ ኤልያስ ላከች።

ስለዚህም ኤልያስ እጅግ አዝኖ እንዲህ አለ አቤቱ ነቢያቶችህን ገደሉ መሠዊያዎችህንም አፈረሱ እኔም ብቻዬን ቀርቻለሁ ነፍሴንም ሊገድሏት ይሿታል። እግዚአብሔርም ለጣዖት ያልሰገዱ ለኔ ሰባት ሽህ ሰዎችን አስቀርቻለሁና አትፍራ ያንተንም ነፍስ ማንም ሊወስዳት የሚችል የለም። ነገር ግን በሥጋህ ሕያው እንደሆንክ ወደ ሰማይ አወጣሃለሁ አለው።

አክአብም ከሞተ በኋላ የሞአብ ሰዎች አመፁ አካዝያስም ታሞ በሰማርያ ባለ እልፍኝ ተኛ ከዚች በሽታዬ እድን እሞትም እንደሆነ ወደ አቃሮን ጣዖት ወደ ዝንቡ ካህን ሔዳችሁ ጠይቁልኝ ብሎ መልክተኞችን ላከ እነርሱም ሊጠይቁለት ሔዱ።

ነቢዩ ኤልያስም መልክተኞቹን በዚህ ደዌ እንደምትሞት ዕወቅ ብላችሁ ለንጉሣችሁ ንገሩት አላቸው። ንጉሡም ኤልያስ እንደሆነ ዐውቆ ይጠሩት ዘንድ ከኃምሳ ወታደሮች ጋር የኃምሣ አለቃውን ላከ ሔደውም በተራራው ራስ ተቀምጦ አገኙት አለቃውም ነቢየ እግዚአብሔር ሆይ ንጉሥ ይጠራሃል ፈጥነህ ውረድ ና አለው ኤልያስም የእግዚአብሔር ነቢይ ከሆንኩ እሳት ከሰማይ ወርዳ አንተንና ወገኖችህን ታቃጥላችሁ አለው እሳትም ወርዳ እርሱንና ኃምሳውን ወታደሮች አቃጠለቻቸው።

ንጉሡም ዳግመኛ ከአለቃቸው ጋራ ኃምሳ ሰዎችን ወደርሱ ላከ አለቃቸውም የእግዚአብሔር ነቢይ ንጉሥ ይጠራሃልና ፈጥነህ ውረድ አለው ኤልያስም እኔ የእግዚአብሔር ነቢይ ከሆንኩ እሳት ከሰማይ ወርዳ ታቃጥልህ ከአንተ ጋር ያሉትን ኃምሳውንም አለው እሳትም ከሰማይ ወርዳ አቃጠለቻቸው።

ከዚህም በኋላ ንጉሡ ሦስተኛ የኃምሣ አለቃ ላከ እርሱ ግን ወደ ነቢዩ ኤልያስ በትሕትና መጥቶ ሰገደለት የእግዚአብሔር ነቢይ ሆይ ተገዛሁልህ ሰውነቴ በፊትህ ትክበር የእነዚህም የባሮችህ ሰውነት ትክበር አለው። ኤልያስም ተነሥቶ ወረደ ከእሳቸውም ጋር ወደ ንጉሡ ሔደ ንገሡንም እንዲህ ብሎ ተናገረው እግዚአብሔር እንዲህ አለ ቃልን ከጣዖት ትጠይቅ ዘንድ የእስራኤል ፈጣሪ የለምን ወደ አቃሮን ጣዖት ወደ ዝንቡ ካህን እንዴት ላክህ ነገሩ እንዲህ አይደለም በዚያ ሞትን ትሞታለህ እንጂ ከተኛህበት መኝታህ አትነሣም አለው ወዲያውኑ ሞተ።

ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር ኤልያስን ወደ ሰማይ በሚያወጣበት ጊዜ ኤልሳዕና ኤልያስ ከገልገላ ተነሥተው ሔደው ወደ ዮርዳኖስ ደረሱ ኤልያስም መጠምጠሚያውን አውርዶ ጠቅሎ የዮርዳኖስን ውኃ መታበት ውኃውም ተከፍሎ ወዲያና ወዲህ ቆመ ሁለቱም ሁሉ በደረቅ ተሻገሩ ወጥተውም በምድር በዳ ቆሙ።

ኤልያስ ኤልሳዕን ካንተ ተለይቼ ወደ ሰማይ ሳልወጣ አደርግልህ ዘንድ የምትሻውን ለምነኝ አለው ኤልሳዕም ኤልያስን በአንተ ያደረ ሀብተ መንፈስ ቅዱስ ዕጥፍ ሁኖ የደርብኝ አለው።

ኤልያስም ኤልሳዕን ድንቅ ነገርን ለመንከኝ ነገር ግን ካንተ ተለይቼ ወደ ሰማይ ሳርግ ብታየኝ ይሁንልሀ ባታየኝ ግን አይሆንልህም አለው። በዚያንም ጊዜ የእሳት ሠረገላና የእሳት ፈረስ መጣ ወደ መካከላቸውም ገብቶ አራራቃቸው ኤልያስም እንደዚህ በንውጽውጽታና በጥቅል ነፋስ ወደ ሰማይ ዐረገ። ኤልሳዕም አይቶ የእስራኤል ኃይላቸውና ጽናታቸው አባ አባ ብሎ ጮኸ ከዚህ በኋላ ዳግመኛ አላየውም ልብሶቹንም ለሁለት አድርጎ ከፈላቸው ኤልያስም ለኤልሳዕ መጠምጠሚያውን ጣለለት በኤልሳዕም ራስ ላይ ወረደ የኤልያስም ሀብተ መንፈስ ቅዱስ በኤልሳዕ ላይ ዕጥፍ ሁኖ አደረ ኤልያስም የሠራውን ተአምራት ኤልሳዕ ዕጥፍ አድርጎ ሠራ።

ይህም ኤልያስ በኋላ ዘመን ከኄኖክ ጋር ይመጣ ዘንድ አለው ሐሳዊ መሢሕንም ይቃወሙታል እርሱም ይገድላቸዋል በድናቸውም በአደባባይ ተጥሎ ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት ይቆያል ከዚህም በኋላ ይነሣሉ የሙታን ትንሣኤም ይሆናል ይህም ኤልያስ ዕውነተኛ ነቢይ አስቀድሞ የነበረ በኋላም የሚገለጽ ነው በብሉይ ዘመንም ኑሮው በበረሀ ውስጥ ነበር።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ታላቁ_ቅዱስ_ባስልዮስ_ዘቂሣርያ

በዚህችም ዕለት የከበረና ታላቅ የሆነ አባት የቂሣርያ ኤጲስቆጶስ ባስልዮስ አረፈ። የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም ኤስድሮስ ይባላል እርሱም ከአንጾኪያ አገር ሰዎች ንጹሕና ቅዱስ የሆነ ቄስ ነው አምስት ልጆችንም ወልዶአል እነርሱም ባስልዮስ፣ ጎርጎርዮስ፣ ጴጥሮስ፣ ኬርዮን፣ መክርዮን ናቸው ሁሉም ከፍጹማንነት የደረሱ ቅዱሳን ናቸው።

በዚህ በከበረ ባስልዮስ ላይ መንፈስ ቅዱስ መልቶበት በሁሉ ዘንድ የታወቀች ቅዳሴውን ደረሰ እግዚአብሔርም በእጆቹ ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ በገድሉ መጽሐፍ እንደተጻፈ። ከእርሳቸውም ሰባቱ እሊህ ናቸው አንደኛው የስብስጥያ ኤጲስቆጶስ የወንድሙ የጴጥሮስ ዜና ነው እርሱ አንዲት ሚስት እንደነበረችው ሕዝቡም ስለዚህ ነገር እንዳሙት ወሬውም ወደ ቅዱስ ባስልዮስ በደረሰ ጊዜ ከሚስቱ ጋር ያለውን ምሥጢሩንና ገድሉን እነርሱ ንጹሐን ደናግል እንደሆኑ ለሕዝቡ ገለጠላቸው። የእግዚአብሔር መልአክም በክንፎቹ ሲጋርዳቸው እንዳየ አስረዳቸው በዚያንም ጊዜ በቅዱስ ጴጥሮስ ላይና በከበረች ሚስቱ ላይ የእግዚአብሔር መልአክ ክንፎቹን ሲጋርድ ሕዝቡ አዩ እጅግም አደነቁ የክብር ባለቤት ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስንም አመሰገኑት በደላቸውንም ይቅር ይላቸው ዘንድ ከእግሩ በታች ወድቀው ቅዱስ ጴጥሮስን ለመኑት።

ሁለተኛው ተአምር ሃይማኖት ለዋጮች መናፍቃን በግፍ ስለወሰዱዋት ቤተ ክርስቲያን በርዋን መክፈት እንዳልተቻላቸው ቅዱስ ባስልዮስ በጸሎቱ ዘግቷታልና ከዚህም በኋላ ሃይማኖታቸው ለቀና ምእመናን ተከፍታላቸው ገቡ።

ሦስተኛ የቅዱስ ኤፍሬም ዜና ነው ከምድር እስከ ሰማይ የሚደርስ የብርሃን ምሰሶ በአየ ጊዜ ይህ የቂሣርያ ሊቀ ጳጳሳት ባስልዮስ ነው የሚል ቃልን ሰማ። ቅዱስ ኤፍሬምም ወደ ቂሣርያ በደረሰ ጊዜ የቅዱስ ባስልዮስን ደግነቱንና ትሩፋቱን አየ ከእርሱም ዲቁና ደግሞ ቅስና ተሾመ በቅዱስ ኤፍሬም ላይም ቅዱስ ባስልዮስ ጸልዮ በዮናኒ ቋንቋ እንዲናገር አደረገው።

20 last posts shown.

197

subscribers
Channel statistics