#ልሳነ_ግዕዝ
#ክፍል_1
#ፊደል
ኢትዮጵያ የራሷ የሆነ ፊደልና አኀዝ ያላት ብቸኛ አፍሪካዊት ሀገር ናት ። ፊደል ማለት የነገር ፣ የቃል ምልክት፣ አምሳል መግለጫ ወይም ማስታወቂያ ማለት ነው ። የግዕዝ ፊደላት ቅጥያዎች ከካዕብ እስከ ሳብዕ ድረስ ስድስት ኆኄዎች ናቸው ።ለምሳሌ ፦ ኡ፣ኢ፣አ፣ኤ፣እ፣ኦ(ኡ=ካዕብ ኢ=ሣልስ ኣ=ራብዕ ኤ=ኃምስ እ=ሳድስ ኦ=ሳብዕ) የ(ጰ) ና የ(ፐ) ፊደላት ተፅዕኖ የመጣው በአባ ሰላማ ፍሬምናጦስ አማካኝነት መጻሕፍት ከጽርእ ወደ ግዕዝ ሲተረጎሙ ተጨምረዋል ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትውፊት አሌፋት ፊደል መገኛ መሰረት የሚከተለውን ይተርካል ። ጻድቁ አቤል በወንድሙ ተገድሎ ከሞተ በኀላ የሰው ልጆች ደመ አቤል ያጥፍአነ ፣ደመ አቤል ያስጥመነ እያሉ ሲምሉ እግዚአብሔር በሩቅ ብእሲ ደም መማል እንደማይገባ በ3ኛው ትውልድ በሄኖስ አማካኝነት 22ቱን ፊደላት በ22ቱ ሥነፍጥረታት አምሳል በጸፍጸፈ ሰማይ ቀርጾ እንደሰጠው ይተርካል ።ከ81 መጽሐፍት ውስጥ መጽሐፈ ሔኖክና መጽሐፈ ኩፋሌ ስለ አሌፋት ፊደል በሰፊው ያትታል ።የግዕዝ መሰረታዊ ፊደሎች 26 ሲሆኑ እያንዳንዳቸውም 7 የጽሑፍ ሆሄ አላቸው ። ስለዚህ 26ቱ ፊደሎች በሰባት ቅርፆቻቸው ሲባዙ 182 ይሆናሉ ። በተጨማሪም 4 ዲቃላ ፊደሎች (ጎ፣ኈ፣ኰ፣ቔ) እነዚህም እያንዳንዳቸው 5 ሆሄያት በአንድነት 20 ይሆናሉ። የግዕዝ ፊደላት ቅደም ተርታ የሚጀምረው አ፣በ፡ገ፡ደ... በማለት ሲሆን የአማርኛ ደግሞ ሀ፣ለ፡ሐ፡መ... በማለት ነው ። በመሆኑም የሁለቱን ቋንቋዎች ፊደል ተርታ በጥንቃቄ በመለየት መጠቀም ያስፈልጋል።
💚 @lesangeez128💚
💛 @lesangeez128💛
❤️ @lesangeez128 ❤️
#ክፍል_1
#ፊደል
ኢትዮጵያ የራሷ የሆነ ፊደልና አኀዝ ያላት ብቸኛ አፍሪካዊት ሀገር ናት ። ፊደል ማለት የነገር ፣ የቃል ምልክት፣ አምሳል መግለጫ ወይም ማስታወቂያ ማለት ነው ። የግዕዝ ፊደላት ቅጥያዎች ከካዕብ እስከ ሳብዕ ድረስ ስድስት ኆኄዎች ናቸው ።ለምሳሌ ፦ ኡ፣ኢ፣አ፣ኤ፣እ፣ኦ(ኡ=ካዕብ ኢ=ሣልስ ኣ=ራብዕ ኤ=ኃምስ እ=ሳድስ ኦ=ሳብዕ) የ(ጰ) ና የ(ፐ) ፊደላት ተፅዕኖ የመጣው በአባ ሰላማ ፍሬምናጦስ አማካኝነት መጻሕፍት ከጽርእ ወደ ግዕዝ ሲተረጎሙ ተጨምረዋል ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትውፊት አሌፋት ፊደል መገኛ መሰረት የሚከተለውን ይተርካል ። ጻድቁ አቤል በወንድሙ ተገድሎ ከሞተ በኀላ የሰው ልጆች ደመ አቤል ያጥፍአነ ፣ደመ አቤል ያስጥመነ እያሉ ሲምሉ እግዚአብሔር በሩቅ ብእሲ ደም መማል እንደማይገባ በ3ኛው ትውልድ በሄኖስ አማካኝነት 22ቱን ፊደላት በ22ቱ ሥነፍጥረታት አምሳል በጸፍጸፈ ሰማይ ቀርጾ እንደሰጠው ይተርካል ።ከ81 መጽሐፍት ውስጥ መጽሐፈ ሔኖክና መጽሐፈ ኩፋሌ ስለ አሌፋት ፊደል በሰፊው ያትታል ።የግዕዝ መሰረታዊ ፊደሎች 26 ሲሆኑ እያንዳንዳቸውም 7 የጽሑፍ ሆሄ አላቸው ። ስለዚህ 26ቱ ፊደሎች በሰባት ቅርፆቻቸው ሲባዙ 182 ይሆናሉ ። በተጨማሪም 4 ዲቃላ ፊደሎች (ጎ፣ኈ፣ኰ፣ቔ) እነዚህም እያንዳንዳቸው 5 ሆሄያት በአንድነት 20 ይሆናሉ። የግዕዝ ፊደላት ቅደም ተርታ የሚጀምረው አ፣በ፡ገ፡ደ... በማለት ሲሆን የአማርኛ ደግሞ ሀ፣ለ፡ሐ፡መ... በማለት ነው ። በመሆኑም የሁለቱን ቋንቋዎች ፊደል ተርታ በጥንቃቄ በመለየት መጠቀም ያስፈልጋል።
💚 @lesangeez128💚
💛 @lesangeez128💛
❤️ @lesangeez128 ❤️