" በቦምብ ጥቃቱ 31 ተማሪዎች ተጎድተዋል " - ፖሊስ
ዛሬ በፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ዳሞት መሰናዶ ቁጥር 1 ት/ቤት ላይ በተፈፀመ የቦምብ ጥቃት በ31 ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የፍኖተ ሰላም ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ገለጸ።
በት/ቤቱ በተፈፀመው የቦምብ ጥቃት 6 ተማሪዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል ብሏል።
የቦምብ ጥቃቱ (ቦምቡ የተጣለው) ጥዋት 2፡30 ሰዓት ተማሪዎች በፈተና ላይ እንዳሉ መፈፀሙን የገለጸው ፖሊስ ፤ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው 6ቱ ተማሪዎች ለከፍተኛ ህክምና ሪፈር ተፅፎላቸዋል ህክምና ላይ ናቸው ብሏል።
15 ተማሪዎች ደግሞ በፍኖተ ሰላም ጠቅላላ ሆስፒታል ህክምና እያገኙ ሲሆን 10 ተማሪዎች ላይ ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው አመልክቷል።
አደጋውን ተከትሎ አንድ ተጠርጣሪ #ተማሪ መያዙን ፤ እጁና እግሩ ላይም መቁሰሉን ያሳወቀው ፖሊስ ሌሎች በድርጊቱ የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ስር ለማዋል እየሰራ እንደሆነ ገልጿል።
@tikvah2024
ዛሬ በፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ዳሞት መሰናዶ ቁጥር 1 ት/ቤት ላይ በተፈፀመ የቦምብ ጥቃት በ31 ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የፍኖተ ሰላም ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ገለጸ።
በት/ቤቱ በተፈፀመው የቦምብ ጥቃት 6 ተማሪዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል ብሏል።
የቦምብ ጥቃቱ (ቦምቡ የተጣለው) ጥዋት 2፡30 ሰዓት ተማሪዎች በፈተና ላይ እንዳሉ መፈፀሙን የገለጸው ፖሊስ ፤ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው 6ቱ ተማሪዎች ለከፍተኛ ህክምና ሪፈር ተፅፎላቸዋል ህክምና ላይ ናቸው ብሏል።
15 ተማሪዎች ደግሞ በፍኖተ ሰላም ጠቅላላ ሆስፒታል ህክምና እያገኙ ሲሆን 10 ተማሪዎች ላይ ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው አመልክቷል።
አደጋውን ተከትሎ አንድ ተጠርጣሪ #ተማሪ መያዙን ፤ እጁና እግሩ ላይም መቁሰሉን ያሳወቀው ፖሊስ ሌሎች በድርጊቱ የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ስር ለማዋል እየሰራ እንደሆነ ገልጿል።
@tikvah2024