Ethio Entrance


Гео и язык канала: не указан, не указан
Категория: не указана



Гео и язык канала
не указан, не указан
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


⬆️ ⬆️
🔈 #የነዋሪዎችድምፅ

“ ግድያና እገታ የሚፈጸመው መሀል ከተማ ላይ ነው፡፡ ለዛውም ፖሊስ ጣቢያ ባለበት አጠገብ፡፡ ዛሬ ህዝቡ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥቷል፡፡ ፖሊስና ሚሊሻ ወደ ህዝቡ ነው የተኮሰው ” - ነዋሪዎች

በአማራ ክልል፣ ጎንደር ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች በተለይ ከሦስት ወራት ወዲህ " በታጠቁ አካላት አማካኝነት ግድያ፣ እገታና ዝርፍያ " በመበራከቱ ሰቆቃ ላይ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ድርጊቱ የሚፈጸመው በከተማው ምንም አይነት የተኩስ ልውወጥ በማይደረግበትና አገር ሰላም በተባለበት ወቅት እንደሆነ፣ የጸጥታ አካላት ቅሬታው ከነዋሪዎቸ ቢቀርብላቸውም ለጉዳዩ ትኩረት ባለመስጠታቸው ጥቃቱ እንደተባባሰ አስረድተዋል፡፡

ነዋሪዎቹ ምን አሉ ?

- ኧረ የፍትህ ያለህ ! አገራችን ይሄው ሆነ፡፡ ታዲያ አገራችንን ትተን የት እንሂድ ? ሞትና እገታ በቃ እንደ ደና አደርክ ሁሌም የምንሰማው ቃል ሆነብን እኮ፡፡

- የታጠቁ አካላት ሌሊት የተኩስ ሩምታ ይከፍታሉ፡፡ የነዋሪዎችን ቤትም ሰብረው ይገባሉ፡፡ ከዚያ ሰዎቹን በማስፈራራት አግተው ይወስዳሉ፡፡ እንደገና ታጋቾቹን ለመልቀቅ እስከ 3 ሚሊዮን ብር ይጠይቃሉ፡፡ ገንዘቡ ተልኮም ታጋቾቹን ይገድሏቸዋል፡፡

- ሁሌም ሌሊት ላይ በጣም ይተኮሳል፡፡ እናም ተኩስ ከተሰማ የሆነ ሰው እየታገተ እንደሆነ ይታወቃል ከድርጊቱ መደጋገም ተነሳ፡፡

- የ ‘ፋኖ’ ታጣቂዎች በከተማው የሉም። ከተማው ላይ ያለው ሚሊሻ ነው፡፡ ፖሊሶች ራሱ ከተማ ላይ ሲንቀሳቀሱ አይታዩም፡፡

- ጎንደር ላይ ፋኖም፣ መከላከያም የለም፤ ስለዚህ ጦርነት የለም፡፡ እገታ፣ ግድያና ዝርፊያው የሚፈጸመው በከተማው ጦርነት እየተካሄደ ሆኖ እንኳ አይደለም፡፡

- እንዲህ የሚያደርጉትን አካላት ማንነት ሌሊት ስለሚመጡ በደንብ ማወቅ አይቻልም፡፡

- በየቀኑ በመኪና እየመጡ አጥር ዘለው ይገባሉ፡፡ ግቢ ከበው ሌሎች ሙሉ አባበሎቻቸውን አስገብተው ነዋሪዎቹን አግተው ይወስዳሉ፡፡ እንደዚህ መሆን ከጀመረ ሦስት ወራት አስቆጥሯል፡፡

- አጋቾቹ ገንዘብ ሲጠይቁ የታጋች ቤተሰብ በባንክ ነው ገንዘብ የሚልከው፡፡ በባንክ ነው የሚላክላቸው። ስለዚህ እነርሱን ማግኘት ለምን አልተሻለም ? ሙሉ መረጃው ባንክ ላይ አለ።

- የጸጥታ አካላት በቀበሌ ሰብስበውን ነበር፡፡ ሁሉም ሰዎች ‘ እናንተ የምታመጧቸው ሚሊሾች ናቸው እንዲህ የሚያደርጉን፡፡ ' ነው ያሉት።

- ትላንት ከሚሊሻ በተተኮሰ ጥይት አንድ ልጅ ተገድሏል፡፡

- ግድያና እገታ የሚፈጸመው መሀል ከተማ ላይ ነው፡፡ ለዛውም ፖሊስ ጣቢያ ባለበት አጠገብ፡፡ ዛሬ ህዝቡ ሰላመዊ ሰልፍ ሲወጣ ፖሊስና ሚሊሻ ወደ ህዝቡ ተኩሷል ፒያሳ ላይ። ሰዎችም ተጎድተዋል። ተገለዋል።

- እንዲህ የሚያደረገው የነዋሪው ሥነ ልቦና እንዲጎዳ፣ ተስፋ እንዲቆርጥ ነው፡፡ ፍላጎታቸው ገንዘብ ብቻ አይደለም፤ ምክንያቱም ገንዘብ ከተላከ በኋላም ታጋቾቹን ይገድሏቸዋል፡፡

- ጡት እንኳን ጠብታ ያልጨረሰች ኖላዊት የተባለች ህፃን ልጅ በአጋቾች ታግታ አጋቾቹ 1 ሚሊዮን ተጠየቀባት ፤ አቅም የለንም ሲሉ 500 ሺህ አደረጉ ከዛ  200 ሺህ ብር ከተቀበሉ በኃላገድለዋት አስክሬኗን በር ላይ ጥለዋል። ለማን እንጩህ ፤ የት እንሂድ ?

- በቅርቡ ደግሞ እናት እና ልጅን ለማፈን ብለው ለሊት ቢመጡም አልመች ስላላቸው ገለዋቸው ሂደዋል። የፍትህ ያለህ።

- ባለሃብቱ ከከተማው እየወጣ ነው ፤ ሌላውም ይህን ሽሽት በቻለው አቅም ወደ አዲስ አበባ እየገባ ነው። እዚህ የቀረው መሄጃ ቢያጣ ነው።

- ባለሀብቱ እየወጣ ሲያስቸግራቸው አጋቾቹ ያገኙትን አፍነው ለምናቹ አምጡ ማለት ጀምረዋል። የሚጠይቁት 1 እስከ 3 ሚሊዮን ብር ነው ሚጠይቁ ደሀም ያዙ ሀብታም ይህን ነድ የሚጠይቁት።

ጉዳዩን በተመለከተ ምላሽ ለማግኘት ወደ ከተማው እና የክልሉ ጸጥታ አካላት ሙከራ ብናደርግም ስልክ ላመንሳት ፈቃደበኛ አልሆኑም፡፡

ምላሽ ከሰጡ በድጋሚ የምንጠይቃቸው ይሆናል፡፡
@ethio_entrance




#EthiopianAirlines

ወደ አስመራ የሚያደርገው በረራ ከነገ ጀምሮ ይቋረጣል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ የሚያደርገውን በረራ ከነገ ጀምሮ እንደሚያቋርጥ አስታውቋል፡፡

አየር መንገዱ በረራውን የሚያቋርጠው በኤርትራ ውስጥ አገልግሎቱን ለመስጠት ባጋጠመው ከአቅም በላይ በሆነ የአሰራር ችግር እንደሆነ ገልጿል።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመብረር ትኬት የቆረጡ መንገደኞች ያለምንም ተጨማሪ ወጪ በሌሎች አየር መንገዶች ጉዟቸውን እንዲያደርጉ ጥረት እንደሚያደርግ አሳውቋል።

" የትኬት ገንዘብ ይመለስልን " የሚሉ ካሉም ለቲኬታቸው ሙሉ ገንዘብ ተመላሽ እንደሚያደረግ ገልጿል።

በበረራው መቋረጥ ምክንያት ለሚፈጠረው መጉላላት ይቅርታ ጠይቋል።

@ethio_entrance


#Breaking

   🚨 LOSTDOGS
 
🔥 Hojiin Kun xumuramuuf guyyaa 11 qofatu Hafee maarree namootii ammallee hin jalqabnee dafaa jalqabaa!!

👉 Hojiin Kun Airdrop Hundeessaa Notcoin waan hundaa'eef Qarshii irraa argamuu Baayyee guddaa ta'a
 
  Namootii Dogs isiniin darbeef Kun furmaatadha🔥🔥

🖇️ Link:: 👇👇👇👇

https://t.me/lost_dogs_bot/lodoapp?startapp=ref-u_1087152512__s_573809


#ETHIOPIA🇪🇹

የቀን ቅዠት ነው !!!

" እንደ አንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ምንም ዓይነት የፀጥታ ሥጋት እንዲኖር አልፈልግም ነገር ግን በኢትዮጵያ አቅም በተለይም በሕዝቦቿ ስለምተማመን እንቅልፍ አልባ ሌሊት የለኝም፡፡ #ግብፅ በሶማሊያ በኩል መጥታ ኢትዮጵያን አጣቢቂኝ ውስጥ መክተት ትችላለች ማለት የቀን ቅዠት ነው። " - አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ (የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር)

@ethio_entrance


#GERD🇪🇹

ፕ/ር አታላይ አየለ ምን ነበር ያሉት ?

ኢትዮጵያ የሁለተኛውን የታላቁ የህዳሴ ግድብ ሙሌት ባከናወነችበት ወቅት በግብፅ ጉዳይ አንድ አስተያየት ሰጥተው ነበር።

ፕ/ር አታላይ አየለ ፦

" ግብፆች ' ግድቡን እንመታለን ' ምናምን የሚሉት ፣ የሚያስፈራሩት ነገር አለ።

የግድቡ ግዝፈት እንዲሁም ሚሰራበት ጥራት እውነት ለመናገር መቼውንም ቢሆን ተመቶ ይፈርሳል ተብሎ የሚታሰብ አይደለም።

እንደው ተሳክቶላቸው እንኳ ቢሆን የውሃ ሙሌቱ ልክ እንደ #ኒውኩሌር_ቦምብ ማለት ነው ለራሳቸው የሚሆነው ፤ ጠራርጎ ሜዴትራንያን ባህር ውስጥ ነው የሚጨምራቸው።

የቀድሞ ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት ' ግድቡን እኛ ሳንሆን እነሱ ናቸው የሚጠብቁት ' ብለዋል።

ስለዚህ ከዚህ አንፃር ኢትዮጵያ ብዙ የሚያስጨንቃት አይደለም።

ቢፈልጉ ይደራደሩ በአካሄድ በሌሎች ጉዳዮች ፣ የውሃ ፣ አካባቢ ጥበቃና በሌሎች የመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ።

@ethio_entrance


https://t.me/major/start?startapp=6502333636

👑 Join me in @Major game and earn $MAJOR token soon!
⭐️ 750 rating bonus for you.
⭐️ 1000 rating bonus if you are Premium.


" ልንከተለው የሚገባው ፖሊሲ አለመፍራት ነው ፤ ... አለመፍራት ሲባል ማንቀላፋት ማለት አይደለም " - አቶ መልስ ዜናዊ (የቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ)

የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት ፓርላማ ቀርበው ማብራሪያ ሲሰጡ በግብፅ ጉዳይ ተናግረው ነበር። ንግግራቸው የፓርላማ አባላትን ፈገግ ያሰኘ ደግሞም ጠንከር ያለ ነበር።

ምን ነበር ያሉት ?

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ፦

" ... የግብፅ መንግሥት #የጥፋት_መንገድ ለማንም እንደማይጠቅም ፤ ተከባብሮ እና ተጠቃቅሞ መኖር እንደሚቻል እንዲገነዘብ ማድረግ ነው ዋናው ስትራቴጂያችን

አንዱ የግብፅ ስትራቴጂ ትልቅ ወታደር አስቀምጦ ማስፈራራት ነው ፤ ይሄን በተመለከተ ልንከተለው የሚገባው ፖሊሲ አለመፍራት ነው የሚሆነው ማለት ነው።

አለመፍራት ሲባል የቀረርቶ ጋጋታ ማስቀመጥ ማለት አይደለም፤ አለመፍራት ሲባል ማንቀላፋት ማለት አይደለም፤ አለመፍራት ሲባል በተጨባጭ በሀገራችን ላይ ሊቃጣ የሚችለው ወረራ ምን ያህል ነው ? ብሎ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መፈተሽ ማለት ነው

ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ሲፈተሽ የግብፅ ወረራ አደጋ በኢትዮጵያ ላይ በጣም ትንሽ ነው። ዜሮ ነው ማለት ግን አይቻልም። ነገር ግን በጣም ትንሽ ነው
ስለዚህም በዚህ በጣም ትንሽ በሆነ አደጋ ምክንያት እንቅልፍ የምናጣበት ምክንያት የለም። ይሄ ማለት ዜሮ ሳላልሆነ ያቺ ትንሿን አደጋ ለመቋቋም ተጨማሪ የአቅማችንን ያህል ዝግጅት ማድረግ ያስፈልጋል።

ይሄን የምናደርገው ግብፅ ይወረናል ብለን ቡራ ከረዮ ለማለት አይደለም። አደጋው በጣም ትንሽ ነው መፍትሄው በጣም ቀላል ነው ፤ መፍትሄው ተደጋግፎ መኖር ነው።

ዋናው ስትራቴጂያችን ላይ እየተረባረብን ምናልባት 5በመቶ እድልም ቢሆን 5በመቶ ትኩረት ሰጥቶ ለዚህ ጉዳይ የመከላከል አቅማችንን መገንባት


የግብፅ ነገር #2 ?

ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋር በባህር በር ጉዳይ የመግባቢያ ስምምነት በተፈራረመች ወቅት ሰዓታት ሳይቆጠር ተቃውሞ ያሰማችው ግብፅ ነበረች

ከሶማሊያ ጋር ተደዋውላም  " አይዞሽ እኔ አለሁልሽ፤ በማንኛውም መንገድ አብሬሽ ቆማለሁ " ብላት ነበር

ባለስልጣናቶቿም ኢትዮጵያ ለሶማሊያን ስንትና ስንት የደም ዋጋ እንዳልከፈለች ዛሬ ደፍረው " ኢትዮጵያን እንዳለመረጋጋት ምንጭ " አድርገው ለመሳልም ሞክረዋል

የኢትዮጵያን ስም እያነሱ ሲለፈልፉ ከርመዋል።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ከኢትዮጵያ ጋር መቃቃር ውስጥ ገብተው ወደ ግብፅ ሲመላለሱ ነው የከረሙት።

በቅርብ ደግሞ " ከግብፅ ጋር ወታደራዊ ስምምነት ተፈራረምን " ብለው ብቅ ብለዋል

ይህ ተሰምቶ ብዙ ሳይቆይ የተለያዩ የጦር መሳሪያ ቁሳቁሶችን የያዙ የግብፅ ፕሌኖች ሞቃዲሾ ሲያርፉ እና ቁሳቁስ ሲያራግፉ ነው የከረሙት።

ሶማሊያ ደም አፍስሶ ዋጋ የከፈለላትን የኢትዮጵያ መከላከያ በATMIS እንዲቀጥል አልፈልግም ማለቷ ፤ ግብፅ ደግሞ በሶማሊያ ወታደሮቼን ማሰማራት ፈልጋለሁ ማለቷ አስገራሚ ነገር ሆኗል።

" እኛ የግብፅ ወታደር እንዲመጣ አንፈልግም፣ የኢትዮጵያ ወታደሮች ዋጋ ከፍለውልናል ፤ እንዳይወጡ " ያሉ የሶማሊያ የምክር ቤት ሰዎች እና ነዋሪዎች አደባባይ ወጥተው ድምጻቸውን አሰምተዋል

ፕሬዝዳንቱ " ኢትዮጵያን በአቋማችሁ ደገፋችኋል " ያላቿውን ሰዎችን ከስራ ማባረር እንደተያያዙ ተሰምቷል

ይኸው ቀጠናዊ ጉዳይ እንዳለ ደግሞ ግብፅ ሆዬ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብን ጉዳይ በማንሳት " ማንኛውም አይነት እርምጃ ውስዳለሁ " ብላ ዛቻ ማሰማት ጀምራለች ፤ ምንም እንኳን የግብፅ ዛቻ አዲስ ባይሆንም

እዛው ባለችበት በርቀት ሆና መዛት ፤ መጮህ ፣ ማውራት መብቷ ነው ኢትዮጵያን መንካት ግን ፈጽሞ አትችልም
@ethio_entrance


#Ethiopia🇪🇹

" #ኢትዮጵያ ሶማሊያ እንደ አገር ትቆም ዘንድ ብዙ መስዋዕትነትን ከፍላለች፡፡ ብዙ ሺሕ የሚቆጣጠሩ ወንዶችና ሴቶች መስዕዋት አድርገናል ገብረናል፡፡

የቆጠብነው ነገር የለም ሕይወት ሰጥተናል፣ ደም ሰጥተናል፣ ላብ ሰጥተናል፣ ጉልበት ሰጥተናል፡፡ ነገር ግን በሶማሊያ በኩል ይህንን አስተዋጽኦ ከቁብ ላለመቁጠርና ውለታ ለማስቀረት የሚደረግ መግለጫ መስማት እንደ ኢትዮጵያዊ ይኮሰኩሳል።

እንደ አፍሪካዊና ሰላም ወዳድ እንደሆነው የሶማሊያ ሕዝብ ደግሞ ያማል።

በሶማሊያ በኩል የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ያደረገውን ተጋድሎ በማንኳሰስ፣ የወሬያቸውና የንግግራቸው ሁሉ ማዋዣ ብቻ ሳይሆን ማዕከል እያደረጉት ነው ፤ ይህ ነውር ነው !!

ኢትዮጵያ ለዘመናት ያደረገችውን አስተዋጽኦ እና የከፈለችውን ዋጋ በማጣጣል፣ የኢትዮጵያን ጥቅም የሚፃረሩ ኃይሎችን ሶማሊያ መጋበዟን ልታቆም ይገባል።

ኢትዮጵያ የደኅንነት ሥጋት የሚፈጥርባትን አካል ዝም ብላ አትመለከትም። " - አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ (የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር)
@ethio_entrance


የግብፅ ነገር ?

ሀገራችን ኢትዮጵያ " እኔ ማንንም ሳልጎዳ የራሴን ሃብት እጠቀማለሁ " ብላ በራሷ የዓባይ ወንዝ ላይ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት መሰረት ከጣለችበት ጊዜ አንስቶ ስትጮህ ፣ ስትዝት፣ ለማስፈራራት ስትሞክር የነበረችው ግብፅ ዛሬም ግድቡ ወደ መጠናቀቁ ደርሶም ዛቻና ቀረርቶዋን አላቆመችም።

ዛሬ ወደ ተመድ ፀጥታው ምክር ቤት አንድ ደብዳቤ ልካለች።

ሀገሪቱ በቅርቡ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ግድቡን ከጎበኙና ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ መግባታቸውን ካበሰሩ በኃላ ስለ ግድቡ ውሃ መያዝ እና ከሞላ ጎደል የሲቪል እና ኤሌክትሮ መካኒካል ስራ ወደ መጠናቀቁ መድረሱን በተመለከተ የሰጡት ማብራሪያ እጅግ አናዷታል፤ አንጨርጭሯታል።

ለጸጥታው ም/ቤት በጻፈችው ደብዳቤ ላይም " በግብፅ መንግሥት ዘንድ ተቀባይነት የለውም " ብላለች።

ሀገሪቱ ግድቡን ምክንያት በማድረግ ኢትዮጵያን ጎረቤቶቿን ተንኳሽ አድርጋ ለማቅረብም ሞክራለች።

ኢትዮጵያ ስንት አመት ሙሉ ለሁሉም ጠቃሚ በሆነ መንገድ መፍትሄ ለማምጣት እንነጋገር እንስማማ ፤ መፍትሄ እንዲመጣ ቁርጠኛ ነኝ ስትል እንዳልከረመች ግብፅ እንደሁል ጊዜ ክሷ " ኢትዮጵያ ሌሎችን አግልላ የአንድ ወገን ፖሊሲ ታራምዳለች፣ መፍትሄ እንዲመጣም አትፈልግም " ብላለች።

ግብፅ ለጸጥታው ምክር ቤት በጻፈችው በዚህ ደብዳቤ ፤ " ኢትዮጵያ እየተከተለች ነው ያለችው ህገወጥ ፖሊሲ በታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ማለትም በግብፅ እና በሱዳን ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽእኖ ያሳድራል " የሚል የተለመደውን ክሷን አቅርባለች።

" ጥቅሜን ለማስጠበቅ ሁሉንም አይነት ህጋዊ እርምጃዎችን ለመውሰድ ተዘጋጅቻለሁ " ስትልም ዛቻዋን ገልጻለች።

" ሁኔታዎችን በቅርብ እየተከታተልኩ ነው " ያለችው ሀገሪቱ " ህልውናዬን እና የህዝቤን ጥቅም ለማረጋገጥ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተር የተረጋገጡ ሁሉንም አይነት እርምጃዎችን ለመውሰድ ተዘጋጅቻለሁ ነው " ያለችው።

ግብፅ እንዲህ አይነት ዛቻ ስታሰማ ይህ የመጀመሪያ አይደለም። ገና ግድቡ መገንባት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እንዲሁ ስትል ነው የኖረችው።

ምንም እንኳን በቀጥታ ሞክራው ባታውቅም ኢትዮጵያን ይጠላሉ፣ ወይም ያዳክሙልኛል የምትላቸውን ኃይሎች በግልፅና በህቡ ስትደግፍ ፤ የግድቡን ስራም ለማደናቀፍ ስትሰራ ነው የኖረችው።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ ላይ ዓለም አቅፍ ጫና ለማሳደር ሁሌም እንደተሯሯጠች ነው ፤ ግድቡ ግን ኃይል ማመንጨት ጀምሯል። አሁን ላይም ወደመጠናቀቁ ነው። ግብፅ ዛቻዋን አላቆመችም፤ አርፋም አልተቀመጠችም። በምንም አይነት መንገድ ለኢትዮጵያ የምትተኛም አይመስልም። " ኢትዮጵያን ይጎዳል " የምትለውን ክፍተት ሁሉ ከመጠቀም ወደኃላ የምትመለስም አይደለችም።

የፈለገችውን ብትሞክር ፣ ብትዝት፣ ብታወራ በተግባርና በቀጥታ ግን ኢትዮጵያን መንካት ፈጽሞ አትችልም።
@ethio_entrance




#ሀዋሳ_ዩኒቨርሲቲ

አድራሻ  ❓

📚 ሃዋሳ ከአዲስ አበባ ቅርብ ርቀት ላይ የምትገኝ ውብ ከተማ የሲዳማ ክልል ፈርጥ ስትሆን የመናገሻ ከተማም ነች ።



የአየር ሁኔታ ❓

📚 ብዙ ግዝ በቀኑ ክፍለ ጊዜ ሞቃታማ ሁና አመሻሽ ላይ ደስ የሚል አየር አላት ፤ ከተማዋ በራሱ የሆነ ደስ የሚል ነገር አላት ።

የካንፓሶቹ ብዛት ❓

📚 በውስጡ ያሉ ግቢዎች ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በውስጡ ብዙ ግቢዎች ያሉ ሲሆን ከነሱም ውስጥም ጥቂቱን እንይ ፦


✅ Main campus
📍Location: Hawassa town (found on the enterance of the city)
       
   ዲፓርትመንት 💡

🎯 governance
🎯 Engineering
🎯 social others
🎯 art
🎯 architect
🎯 touris
🎯 hotel management
🎯  Sport
🎯 law
🎯 Computational science ..
               
✅ Techno campus ፦

📍Location:beside the main campus connected with the main campus though bridge ፦

                   ዲፓርትመንት

             -->  Engineering
             --> information system
            --> programming
            --> Enla,discrit,
           --> for engineering and computer science students until 3rd year wait here after that the student will be transfered to main campus..!

  ✅ Agri campus 
📍Location:  located on the middle o fthe city around piyasa

                 ዲፓርትመንት
              --> animal

✅ Yirgalem campus
📍Location: Yirgalem  town (near hawassa city..)

           ዲፓርትመንት

  🎯FB faculty of business -
  🎯 marketing management
🎯 logistic
🎯 Accounting
🎯 Cooperative
🎯  management
🎯economics 

✅ 5 Referral campus

📍Location:
located around the lake hawassa amazing view from the dorm nice sunset ...

              ዲፓርትመንት ፦

               --> Medicine
               --> HO
               --> nursing
               --> environmental health
               --> radiology
               --> ophtometry
               --> psychiatry

✅ ወንዶ ገነት  agriculture
📍 Location:wendo genet

   Dep'    --> plant...



ውሃ፤መብራት፤ WIFI❓

📚 መብራት እና ውሃ አይጠፋምኀለአንዳንድ ግቢዎች ለልሎች ይጠፋል ። አሪፍ የሆነ WIFI በግቢ የተለያየ ቦታ ላይ ይገኛል ።

ስለ ዮኒቨርሲቲው ❓

📚 ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሀገራችን ላይ አሉ ከሚባሉ ዩኒቨርሲቲዎች በትምህርት ጥራቱም ሆነ በግቢ ውበቱ አንደኛ ደረጃ ከሚባሉት ተርታ የሚመደብ ግቢ ነው።
ትምሮ በተወሰነ መልኩ ሊያጨናንቅ ይችላል ግን በግቢው ውበትና በከተማው ማብለጭለጭ
ካልተሸነፋቹህ የትምህርቱ ነገር ሙድ አለው።


የካፌ ምግብ ❓

📚በጣም ጥሩ የሚባል ምግብ ያቀርባሉ ..!፤ ከብዙ ዮኒቨርሲቲዎች ጥሩ ምግብ የሚሰጥ ካንፓስ ነው ።

ከካፌ ውጪ ያሉ የምግብ ቤቶች ዋጋ ❓

📚የምግብ ዋጋ በaverage ከ25-40 ብር ይደርሳል፥ የሁሉም ግቢዎች ዋጋ ይለያያል ።ቡና ምናምን 5 ብር
ለተማሪዎች fair በሆነ ዋጋ የሸጣሉ ትንሽ ቢወደድም ።

ሽንት ቤት ❓

📚 ጥሩ የሚባል ሽንት ቤት አለው ፤ ከብዙ ግቢዎች የሚሻል አይነት ባኞ አለው ።

➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

@Ethio_entrance


🏢 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 🏬


አድራሻ....❓

💬 በኢትዮጽያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ውስጥ ይገኛል ።

የአየር ሁኔታ ...❓

💬 የመጀመሪያዎቹ ወራቶች መጠነኛ ብርዳማ ሆነው ወደ ኋላ ላይ ግን ሞቃታማ የአየር ንብረት አለው ።


የካንፓሶች ብዛት ❓

📚 በጣም ብዙ ማለትም አስራ ሰባት ይደርሳሉ ። እያንዳንዱ ካንፓስ  የተለያየ ፊልድ ይሰጣል ።
ያሉት  ካንፓሶች ፦
6 ኪሎ ፣
5 ኪሎ ፣
4 ኪሎ ፣
ሜክሲኮ ፣
ልደታ ፣
18 ማዞሪያ
ጥቁር አንበሳ ( hospital)
ቃሊቲ ፤
ቢሾፍቱ (ደብረዘይት) ፤
ላምበረት ......ካንፓሶችን ያካትታል ።


በካንፓሶች የሚሰጡ ፊልዶች ❓

🏠6 kilo

  💡 ለሶሻል ተማሪዎች ብቻ የሶሻል ዘርፍ ትምህርቶችን ይሰጣል ።

🏠5 kilo

💡 ለኢንጂነሪግ ( Software , electrical ,   biomedical , mechanical , civil , chemical ..የሚሰጥበት ካንፓስ ነው ።

✅ biomedical engineering ከሚሰጥባቸው ጥቂት ዩንቨርሲቲዎች ውስጥ አንዱ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነው።

🏠4 kilo

💡 በዚ ካንፓስ computer science እና computer engineering ይሰጣል ።

🏠 18 ማዞሪያ

💡 የሜዲሲን ዘርፎች በ Other health የሚካተቱትን ይሰጣል ።

🏠 ጥቁር አንበሳ

💡 ይህ ካንፓስ አንጋፋ ሲሆን በውስጡም የMedicine ኮርስን ይሰጣል ፤ ተማሪዎች አፓረንትም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ይወጣሉ ።


🏠 ላም በረት

💡 በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ላይ ብቻ አተኩሮ የሚሰራ ካንፓስ ነው ፤ AASTU የሚገኝበት ሲሆን APPLIED እና Enginering ኮርሶችን ይሰጣል ።


🏠ልደታ

💡በልደታ ካንፓስ  የሚሰጡት ፊልዶች architecture ፤ cottom ፤ urban plannig እና የመሳሉትን ያካትታል ።

  🏠 ሜክሲኮ

💡 ይህ ካንፓስ የcommerce ግቢ ነው ።  ( marketing management , business administration, management የሚሰጥበት ካንፓስ ነው ።)

🏠 ሰፈረ ሰላም

📚 የጤና ዘርፍ ግቢ ነው ፤ ሜዲስን ነርሲንግ እና የመሳሰሉት ወደ ጥቁር አንበሳ 3ተኛ አመት ላይ ከመሄዳቸው በፊት የማሩበት ግቢ ነው ።


🏠 ቢሾፍቱ ካንፓስ
 
📚 AAU ደብረዘይት ላይ Veterinary medicine & Science collage አለው ። ደብረዘይት ነው የሚገኘው ካንፓሱ በጤና እና ሳይንስ ዘርፍ ይሰጣል ..!


💬ለኢንጅነሪግ ተማሪዎች ፧

➡ የdrawing መሳሪያዎች መያዝ አለባችሁ
➡ Mathematics and Mechanics Statics guide books ይዛቹህ ብትሄዱ መልካም ነው ።

የካፊው ምግብ ❓

📚 ምግቡ ለክፉ የሚሰጥ አይደለም ከሌሎች ዮኒቨርሲቲዎች የተሻለ ነው ፤ በተለይ ደግሞ ሰፈረ ሰላም ካንፓስ ደስ የሚል ነው ።


በሳምንት ውስጥ ካፌ የሚሰጡ ምግቦች ዝርዝር ስኬጁል  ❓

📚 ከሌሎች ዮኒቨርስቲዎች የተለየ አይደለም ቁርስ ፍርፍር ፤ ሩዝ ፤ ሻይ በዳቦ ፤ ስልስ ይቀርባል ፤ ምሳ እና እራት በሳምንት 2-3 ቀን ስጋ ምሳ እና እራት ይኖራል ፤ ሽሮ ፤ ምስር ፤ አታክልት የመሳሰሉት ምግቦች ይቀርባሉ ።  (በፎቶ የምግቡን ጥራት ማየት ይቻላል)


ከካፌ ውጪ ስለሚገኙ ምግቦች እና ዋጋቸው ❓

📚 ከሌሎች ግቢዎች የተለየ አይደለም ነገር ግን 4 ኪሎ ግቢ ምግብ ከሚታሰበው በላይ ቅናሽ ነው ። ዋጋቸው ከታች ተቀምጧል ...!

ቀላል ምግቦች ፓስታ ፍርፍር... etc 20 -30 ብር
ከባድ ምግቦች እንቁላል ፤ ስጋ ..etc 30-50 ብር
ሻይ እና ቡና ...etc 2-4 ብር ይሆናል ።

የሎከር ነገር ❓

📚 ሎከር በጣም አስቸጋሪ ነው ፤ በዶርም ውስጥ አንድም የሚሰራ ሎከር ማግኘተ ይከብዳል ። አብዛኛው ተበላሽቷል አይሰራም ።

  ውሃ ❓

📚ውሃ በተደጋጋሚ ይጠፋል ፤ በተለይ ደሞ የዕረፍት ቀናት ለአንድ ሰዓት ብቻ ተለቆ ይቆማል ፤ ከተማዋ ላይ የውሃ እጥረት ስላለ ግቢ ውስጥም የተለየ ነገር የለም ..!

...ሽንት ቤት ...❓

📚 እንደ ካንፓሶቹ ቢለያይም አብዛኛው ግን በጣም አሪፍ የሚባል ነው ፤ በተለይ 4 ኪሎ በየቦታው ይገኛል ፤  የሚያስከፋ ነገር የለውም ሻል ያለ ነው ።

  በግቢው ስላለ የዕቃ ስርቆት፦! ❓

📚 እንደካንፓሶቹ ቢለያይም ግርግር ፤ ረብሽ የሚባል ነገር ስለሌለ የስርቆት ነገር በጣም rare ነው ፤ ቸልተኛ ካልሆነ ስርቆቶ ብዙ የሚያሳስብ ነገር አይደለም ።


የሃይማኖታዊ ተቋማት ፦  ❓

📚 በብዙዎቹ ካንፓሶች በአቅራቢያቸው መስኪድ እና ቤተስኪያን ስላለ ሀይማኖታዊ ጉዳዮችን ለመከውን አያዳግትም ።


📚ተጨማሪ መረጃዎች በፎቶ እና ድምፅ የተቀመጡ ለማግኘት የድምፅ መረጃ ወይም የፎቶ መረጃ የሚለውን በተን ይጫኑ ።

📚 በተጨማሪም ሌሎች መረጃዎች ማወቅ እና መጠየቅ ከፈለጋችሁ ተጨማሪ የሚለውን በመጫን  የዮኒቨርሲቲው ዌብሳይት እና ሬጅስትራል ስልክ የተማሪ ተወካዮች ሰልክ እንዲሁም የነባር ተማሪዎች መወያያ ግሩፖችን አቅርበንላቹሃል።

➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

@Ethio_entrance


1. Which organelle is responsible for protein synthesis?
(a) Ribosomes
(b) Mitochondria
(c) Golgi apparatus
(d) Nucleus

2. What is the semi-permeable barrier that surrounds the cell?
(a) Cell membrane
(b) Cell wall
(c) Cytoplasm
(d) Nucleus

3. Which type of cell does not have a nucleus?
(a) Prokaryotic cell
(b) Eukaryotic cell
(c) Plant cell
(d) Animal cell

4. What is the function of the cytoskeleton?
(a) To store genetic material
(b) To transport materials
(c) To provide structural support
(d) To synthesize proteins

5. Which organelle is responsible for cellular respiration?
(a) Mitochondria
(b) Chloroplasts
(c) Ribosomes
(d) Golgi apparatus


6. Which type of cell is found in plants but not in animals?
(a) Prokaryotic cell
(b) Eukaryotic cell
(c) Plant cell
(d) Animal cell

7. Which type of cell has a cell wall made of cellulose?
(a) Prokaryotic cell
(b) Eukaryotic cell
(c) Plant cell
(d) Animal cell

8. Which type of cell has a large central vacuole?
(a) Prokaryotic cell
(b) Eukaryotic cell
(c) Plant cell
(d) Animal cell

9. Which type of cell is specialized for muscle contraction?
(a) Muscle cell
(b) Nerve cell
(c) Red blood cell
(d) White blood cell

10. Which type of cell is responsible for fighting infection?
(a) Muscle cell
(b) Nerve cell
(c) Red blood cell
(d) White blood cell


11. Which type of microscope uses visible light to magnify objects?
(a) Light microscope
(b) Electron microscope
(c) Scanning probe microscope
(d) Fluorescence microscope

12. What is the function of the objective lens?
(a) To magnify the image
(b) To focus the light
(c) To collect light
(d) To project the image

13. Which type of microscope has the highest magnification?
(a) Light microscope
(b) Electron microscope
(c) Scanning probe microscope
(d) Fluorescence microscope

14. What is the function of the diaphragm?
(a) To control the amount of light entering the microscope
(b) To focus the light
(c) To magnify the image
(d) To project the image

15. What is the difference between brightfield and darkfield microscopy?
(a) Brightfield microscopy uses transmitted light, while darkfield microscopy uses reflected light.
(b) Darkfield microscopy uses transmitted light, while brightfield microscopy uses reflected light.
(c) Brightfield microscopy has a higher resolution than darkfield microscopy.
(d) Darkfield microscopy has a higher resolution than brightfield microscopy.

📘Answer Key:

1. a
2. a
3. a
4. c
5. a
6. c
7. c
8. c
9. a
10. d
11. a
12. a
13. b
14. a
15. a

📌Join and share 👇👇👇
           @ethio_entrance


የ12ኛ ክፍል ውጤት መቼ ይፋ ይደረጋል?

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት መቼ ይፋ እንደሚደረግ የሚጠይቁ በርካታ መልዕክቶች ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ደርሰዋል፡፡

የመልቀቂያ ፈተናው ውጤት መቼ ይፋ ይደረጋል ስንል አንድ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከፍተኛ አመራርን ጠይቀናል፡፡

"የፈተናው እርማት በጥንቃቄ እየተከናወነ እንደሆነ" የገለፁት ኃላፊው፤ እርማቱ እንደተጠናቀቀ በመገናኛ ብዙሃን አማካኝነት መግለጫ እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡

"እርማቱ በጥንቃቄ እና በፍጥነት እየተሠራ መሆኑንና በቅርቡም ውጤቱ ይፋ እንደሚደረግ" ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

@ethio_entrance


Репост из: Telebirr Gift 🎁
🛄 BAGA NAGAAN GARA TELEBIRR GIFT NAGAAN DHUFTAN

Bootii Telebirr gift fayyadamuudhan yemmuu miseensa taatan qarshii 1000 badhaafamtu.

🎁 Dabalataan nama tokko yemmuu affeertan kafaltii qarshii 100 argattu!

Namoonni affeertaan 25 yeroo gahan, qarshii 3500 baasii gochuu dandeessu.

Kabajamoo maamila keenyaa Liinkin affeerraa keessanii ⬇️
https://t.me/Telebirrgift_bot?start=r07272423965


EUEE ENGLISH Exam Focus Areas: Based on 1995-2015EC Exams (Ethiopia)

🟢Grammar Focus Areas

1. Tenses
2. Passive and Active Voices
3. Subject Verb Agreement
4. Adverbial Clauses and Related
A. Common Clauses
   ☞  Reason clauses
   ☞  Result clauses
   ☞  Contrast clauses
   ☞  Purpose clauses
   ☞  Relative clauses
   ☞  Time clauses
B. Other Transitional Words to:
   ☞  give emphasis
   ☞  focus attention on what follows
   ☞  give additional ideas
   ☞  give examples
   ☞  show sequence/order of events:
   ☞  show different ideas
5. Comparisons
6. As, like, as if, as though.. .
7.Conditional Clauses:
8.Regret/wish/unreal...
9.Quantifiers
   ☞  Each and Every
   ☞  No
   ☞  None
   ☞  Any and Some
   ☞  No one, Someone… 
   ☞  Little and A little
   ☞  A few, Few and others
10. Uses of Modal Verbs
   ☞  Obligation
   ☞  Absence of Obligation
   ☞  Possibility
   ☞  Deduction
   ☞  Ability
   ☞  Permission and Request
   ☞  Suggestion and Advice
11. Gerund, Infinitive & Participle
12. Parts of Speeches and Others
  ☞ Nouns, Pronouns, Verbs
  ☞ Adverbs, Adjectives, Articles
  ☞ Conjunctions, prepositions
  ☞ Word formations
  ☞ Use of had better, no sooner...
13. Questions and Related Areas
  ☞ Wh-word questions
  ☞ Tag questions
  ☞ Yes or No questions
  ☞ Indirect questions.. .
14. Verbs and their Types
A. Main Verbs:
   ☞  Action Verbs
   ☞  State Verbs
   ☞  Transitive Verbs
   ☞  Intransitive Verbs
B. Auxiliary Verbs:
   ☞  Verb to be
   ☞  Verb to have
   ☞  Verb to do
   ☞  Modal Verbs

15.Communicative Activities Focus Areas

  ☞  Advice
  ☞  Permission
  ☞  Request
  ☞  Opinion
  ☞  Agreement
  ☞  Telephoning
  ☞  Direction
  ☞  Shopping
  ☞  Help
  ☞  Greeting/Introduction
  ☞  Other contextual areas
====≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈

📌Join and share 👇👇👇
             ✳️  @Ethio_entrance




#GERD🇪🇹

ይህ የኢትዮጵያ ህዝብ የላብና ደም አሻራ ያረፈበት የኢትዮጵያ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ነው።

የኢትዮጵያ ህዝብ የአይን ብሌኑም ጭምር ነው።

ተማሪው ፣ ሰራተኛው ፣ ወጣቱ ፣ አዛውንቱ ለዚህ ግድብ ካለው ላይ ፤ ከሚበለው ቀንሶ ሰጥቶ ያሰራው ለትውልድ የሚያወርሰው ሀብቱና ቅርሱ ነው።

ይህ ግድብ ሀገር ውስጥ በየጊዜው በሚፈጠረው አለመረጋጋት ምክንያት ሀዘን፣ መከፋት፣ መበደል ሲመጣ እንኳን ሁሉም የውስጡን በውስጡ ይዞ " ሀገሬ ትቅደም " ብሎ ተጠናቆ በአይኑ ለማየት ሲል ብዙ ዋጋ የከፈለለት ነው።

በፖለቲካ አቋም፣ በሃሳብ፣ በአመለካከት እየተለያየ እንኳ የሀገሩን ጥቅምና ግንድቡን የሚነካበት ነገር ሲመጣ ሁሉን ጥሎ ሽንጡን ገትሮ የተራከረለት ፣ እስከመጨረሻው ድረስም ዋጋ የሚከፍልለት ነው።

ይህ ግድብ ገና ከመሰረቱ እንዳይገነባ ፤ ድጋፍም እንዳይመጣ ሲሯሯጡ የነበሩ ብዙ ናቸው።

እንዳይሳካ ያልፈነቀሉት ድንጋይ ፤ ያልሄዱበት ቦታ የለም። ግን አልሆነም ፤ ወደፊትም አይሆንም።

ዛሬም እነዚህ አካላት ለኢትዮጵያ እንደማይተኙ ግን ግልጽ ነው።

ኢትዮጵያ " የሰው ድርሻ አንድም አልነካም፤ የራሴን ግን እጠቀማለሁ " ማለቷ የሚያንጨረጭራቸው ሀገራት በግንባታው ወቅት ዛቻ ሲያዘንቡ ፣ እንዲቆም ለማስፈራራት ሲሞክሩ ፣ በአንድም በሌላ በዓለም አቀፍ መድረክ በውስጥ እና በይፋ ጫና ለማድረግ ሲሰሩ እንደከረሙ የአደባባይ ሚስጥር ነው።

ብዙ ብዙ ቢሞክሩም መክነው ቀርተዋል። አሁንም ግን ጩኸታቸው እንደቀጠለ ነው።

ለማደናቀፍ የሚደረገው ጥረትም እንደዛው እንደቀጠለ ነው።

አንዴ " የመሬት መንቀጥቀጥ ቢመጣ አይፈርሳል " ፤ አንዴ " ጥራቱ አስተማማኝ አይደለም ይደረመሳል " ፤ አልሆን ሲላቸው " በአየር እንመታዋለን ፣በቦንብ እናጋየዋለን " በማለት ብዙ ሲያወሩ ከርመዋል።

ከወሬ የዘለል ግን ምንም ማድረግ አይችሉም።

እዛው ያሉበት ሆነው የፈለጉትን ማሰብ ይችላሉ ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ እያለ ግን ማድረግ መንካት ግን ፈጽሞ አይቻልም።

@ethio_entrance

Показано 20 последних публикаций.

212

подписчиков
Статистика канала