የዛሬው ሪፖርት ማንቂያ ደውል ይሁነን!
በዛሬው ዕለት የሰማናቸው 2 የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ኬዞች ሁላችንንም ሊያነቁ ፣ ካለንበትም የመዘናጋት እና የቸልተኝነት እንቅስቃሴ ሊያወጡን ይገባል።
ሁለቱም በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ግለሰቦች የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የሌላቸው ፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት የሌላቸው መሆኑ ሁላችንንም በእጅጉ ሊያሳስበን ይገባል ፤ አካሄዳችንንም ቆም ብለን እንድንገመግም ያስገድደናል።
የታማሚዎች ማገገም እጅግ በጣም ደስ የሚያሰኝና ተስፋ የሚሰጥ ቢሆንም ሰዎች እያገገሙ ነው ማለት ቫይረሱ አይሰራጭም ወይም ቫይረሱ እየጠፋነው ማለት አይደለምና ትልቅ ዋጋ ከመክፈላችን በፊት መዘንጋቱ፣ ትዕግስት ማጣቱ፣ ቸልተኝነቱ ሊያበቃ ይገባል ለማለት እንወዳለን።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia