የእውቀት ካዝና


Kanal geosi va tili: ko‘rsatilmagan, ko‘rsatilmagan
Toifa: ko‘rsatilmagan


ኢንሻአላህ በአላህ ፍቃድ ስለ ዲናችን እንማማርበታለን ፣ አጫጭር መልዕክቶችን እናስተላልፋለን አላማችን እናንተ ያላወቃችሁትን ማሳወቅ ነው ደግሞ እኛ ከማንም በልጠን አይደለም።

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
ko‘rsatilmagan, ko‘rsatilmagan
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


◼️ከትዳር በፊት ጥንቃቄ ለሴቶች‼️
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

✅ ብዙ ጊዜ ከትዳር በፊት ከHIVና ሌላም በሽታ ፍራቻ የደም ምርመራ ይደረጋል። ነገር ግን ከደም ምርመራ በላይ የመንሀጅ፣ የአቂዳ፣ የሱናና የአኽላቅ ምርመራ ሊደረግ ይገባል።

↪️ የመንሀጅ ምርመራ፦ ለትዳር አጋር ይሆነኛል ብለሽ የምትመርጭው አካል መንሀጁ ምን እንደሆነ ማጤን ወሳኝ ይሆናል። በሶሀቦች መንገድ በሰለፎች ጎዳና ቀጥ ያላለ ከሆነ አልፎም፦
🔻አህባሽ
🔻ኢህዋንይ
🔻ሱፍይ
🔻ሀዳድይ
🔻አሽአርይ
🔻ተክፊርይና ሌላም ከሆነ
♻️ከጠማሞችና ከጠፊዎች ስለሆነ ለትዳር አይበጅምና ጠንቀቅ በይ።

↪️ የአቂዳ ምርመራ፦ የትዳር አጋርሽ አቂዳው የተስተካከለ፣ አላህን በብቸኝነት የሚያመልክና አቂዳን ከሚያበላሹ ነገሮች የራቀ መሆኑን ማረጋገጥ ይጠበቅብሻል። ምክንያቱም የአላህን ሀቅ ያልተወጣ የኔን ሀቅ ይወጣል ብለሽ አታስቢ።
♻️ቀብር አምላኪ
♻️ሰይድና ኸድር አብዱልቃድር ጅላሌ የሚል
♻️ለቀብር ባለቤት የሚያርድና የሚሳል
♻️ከአላህ ውጪ ያሉትን ድረሱልኝ የሚል
♻️ወልይ ሷሊህና ነብያት የሚለምን
♻️ሁዝ ቢየዲ ያረሱሉላህ የሚል
♻️አብሬት ቃጥባሬ ንጉሶቹ ሸኸና ሁሴን አባድር አኒ ዳኒ ሌላም የሚል ከሆነ
♨️ሙሽሪክ ነውና ለትዳር ስለማይሆን ጠንቀቅ በይ።

↪️ የሱና ምርመራ፦ ለትዳር ያሰብሽው አካል አቅሙ በቻለ መጠን ሱናን የሚከተል፣ ከቢድአና ከቢድአ ባለቤቶች የሚርቅ መሆን አለበት።
🔸መውሊድ የሚያከብር
🔸ሀሙስ፣ እስነይን እያ ቀን ሚከፋፍል
🔸ኢስራ ወል ሚእራጅ እያለ ሚያከብር
🔸የሸእባን ግማሽን ከሌላው ቀን የሚለይ ከሆነ
♨️ሙብተዲእ ነውና ለትዳር ስለማይሆን ጠንቀቅ በይ።

↪️ የዲን ምርመራ፦ ለትዳር ያሰብሽው አካል፦
🔹ሶላት በቋሚነት ቀጥ ብሎ የማይሰግድ
🔹ሙዚቃ የሚሰማና ነሺዳ የሚያዳምጥ
🔹በፊልም በድራማና በኳስ ጊዜው ሚገል
🔹ቁርአን የማይቀራ ዲኑን የማይማር
🔹ሲጋራ የሚነፋ ጫት የሚቅም
🔹ፂሙን የሚላጭ ፀጉሩን የሚያበላልጥ
🔹ሱሪውን ሚጎትት ፋሽን የሚከተል
🔹ሴትን የሚጨብጥ ኢኽቲላጥ ሚያበዛ ከሆነ
♨️ለትዳር አይሆንሽምና ጠንቀቅ በይ።
⤵️⤵️
https://t.me/Dnel_Eslam
https://t.me/Dnel_Eslam


🇸🇦መኖር ካለብን በኢስላም🇸🇦 dan repost
🌹አሰላሙአሊኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ🌹

#ጥያቄ #መልስስስ

1⃣✍እስላማዊ አቆጣጠር የሚጀምርበት አመት ስንት ነው ?

ሀ// 622✅

ለ// 587

ሐ// 266

መ// 612

2⃣✍ በአላህ ( ሱ ወ ) የተላኩ ነብያት ሁሉ የጠሩት ምን ወደሚለው ቃል ነው ?

A/ ላ ኢለሀ ኢለላህ✅

B/ አታጋሩ

C/ ሙሐመድ ረሱልለላህ

D/ ዝሙት አትሰሩ

3⃣ ✍ ከሚከተሉት ውስጥ ቁረይሾች ነብዩ ሙሐመድን ( ሰ አ ወ ) ዳዕዋ ለማደናቀፍ የተጠቀሟቸው ዘዴወች የትኞቹ ናቸው ?
ሀ // በመሳለቅና በማሾፍ
ለ // ክርክር በመፍጠር
ሐ // ሰዎች ጥሪውን እንዳይሰሙ በመረበሸ ጥርጣሬና ውሸትን በመንዛት
መ // ሁሉም መልስ ናቸው✅

4⃣✍ ከሚከተሉት ውሰጥ የነብዩ ሙሐመድን ( ሰ አ ወ ) የሰማይ ጉዞን ምን ያህል ጊዜ ( በተቀራራቢው ) ፈጅ ?
ሀ // ሰባት ቀን
ለ // 1 ለሊት✅
ሐ // ሁለት ቀን
መ // ሶሰት ቀን

5⃣✍ ከሚከተሉ ውስጥ በቁርአን ውስጥ በመጥፎ ስራወች በስም የተወሳው ግለሰብ የትኛው ነው ?

A/ ሉቅማን

B/ ዙል ቀረይን

C/ ጃሉት✅

D/ መልስ የለም

6⃣✍በቁርአን ውስጥ ሱረቱ ነስር በመባል የምትታወቀው ሱራ ማናት

ሀ ወል አስር
ለ አልሀኩሙተካሱር
ሐ ኢዘ ሰማኡን ፈጠረት
መ ለም የኩኒለዚነ
ሠ መልሱ አልተሰጠም✅

7⃣ሰብአ መሳኒ "سبع المثاني" (ሰባት ተደጋጋሚ) በመባል የሚታወቀው የቁርአን ምእራፍ ሱረቱል በቀራ ነው።

A// ትክክል ነው

B// ትክክል አይደለም✅

8⃣✍ሱዋዕ የተባለውን ጣዖት የሚያመልኩት የትኞቹ ጎሳዎች ናቸው?

ሀ//ከልብ ለሚባል ጎሳ የነበረ ጎሳ ደውመተጀንደል የሚባል ቦታ ያለ ጣዖት

ለ// ለሁዘይል ጎሳ የነበረ ጣዖት✅✅

ሐ// ሙራድ ለሚባል ጎሳ በኒ ጉጠይፉ አከባቢ (የመን) የሚገኝ ጣዖት

መ// ሀምዳን ለሚባል ጎሳ የነበረ ጣዖት

ሠ// ሂሜር ለሚባል ጎሳ የነበረ ጣዖት

የተሳተፉችሁ 💐💐💐💐

Aziza🏆🏆🌺🛍

Helima🏆🏆🌺🛍

Alyar🏆🏆🌺🛍

ፀሀይ አካሉ🏆🏆🌺🛍

እማሁሌም በልቤ ዉስጥ ነሽ🏆🏆🌺🛍

አላህ ይጨምርላችሁ የኔ ጀግኖች
👏👏👏👏👏👏👏👏👏


🇸🇦መኖር ካለብን በኢስላም🇸🇦 dan repost
🌹አሰላሙአሊኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ🌹

#ጥያቄ

1⃣✍እስላማዊ አቆጣጠር የሚጀምርበት አመት ስንት ነው ?

ሀ// 622

ለ// 587

ሐ// 266

መ// 612

2⃣✍ በአላህ ( ሱ ወ ) የተላኩ ነብያት ሁሉ የጠሩት ምን ወደሚለው ቃል ነው ?

A/ ላ ኢለሀ ኢለላህ

B/ አታጋሩ

C/ ሙሐመድ ረሱልለላህ

D/ ዝሙት አትሰሩ

3⃣ ✍ ከሚከተሉት ውስጥ ቁረይሾች ነብዩ ሙሐመድን ( ሰ አ ወ ) ዳዕዋ ለማደናቀፍ የተጠቀሟቸው ዘዴወች የትኞቹ ናቸው ?

ሀ // በመሳለቅና በማሾፍ

ለ // ክርክር በመፍጠር

ሐ // ሰዎች ጥሪውን እንዳይሰሙ በመረበሸ ጥርጣሬና ውሸትን በመንዛት

መ // ሁሉም መልስ ናቸው

4⃣✍ ከሚከተሉት ውሰጥ የነብዩ ሙሐመድን ( ሰ አ ወ ) የሰማይ ጉዞን ምን ያህል ጊዜ ( በተቀራራቢው ) ፈጅ ?
ሀ // ሰባት ቀን
ለ // 1 ለሊት
ሐ // ሁለት ቀን
መ // ሶሰት ቀን

5⃣✍ ከሚከተሉ ውስጥ በቁርአን ውስጥ በመጥፎ ስራወች በስም የተወሳው ግለሰብ የትኛው ነው ?

A/ ሉቅማን

B/ ዙል ቀረይን

C/ ጃሉት

D/ መልስ የለም

6⃣✍በቁርአን ውስጥ ሱረቱ ነስር በመባል የምትታወቀው ሱራ ማናት

ሀ ወል አስር
ለ አልሀኩሙተካሱር
ሐ ኢዘ ሰማኡን ፈጠረት
መ ለም የኩኒለዚነ
ሠ መልሱ አልተሰጠም

7⃣ሰብአ መሳኒ "سبع المثاني" (ሰባት ተደጋጋሚ) በመባል የሚታወቀው የቁርአን ምእራፍ ሱረቱል በቀራ ነው።

A// ትክክል ነው

B// ትክክል አይደለም

8⃣✍ሱዋዕ የተባለውን ጣዖት የሚያመልኩት የትኞቹ ጎሳዎች ናቸው?

ሀ//ከልብ ለሚባል ጎሳ የነበረ ጎሳ ደውመተጀንደል የሚባል ቦታ ያለ ጣዖት

ለ// ለሁዘይል ጎሳ የነበረ ጣዖት

ሐ// ሙራድ ለሚባል ጎሳ በኒ ጉጠይፉ አከባቢ (የመን) የሚገኝ ጣዖት

መ// ሀምዳን ለሚባል ጎሳ የነበረ ጣዖት

ሠ// ሂሜር ለሚባል ጎሳ የነበረ ጣዖት

መልስ ማስቀመጫ⤵️⤵️

@Seimara12_bot
@Seimara12_bot


· ➪ጁመዓ!
--------------------

➪የጁምዓ እለት የሳምንቱ ምርጥ ቀን ነው።

➪የአላህ መልእክተኛ ﷺ
«አላህ ዘንድ ከቀናቶች ሁሉ በላጩ የጁምዓ እለት ነው።» ብለዋልና በዚህ እለት ስራዎቻችንን ይበልጥ ማሳመር ይገባናል።
#صححه الألباني في
السلسلة الصحيحة - رقم: (1502)
صحيح الجامع -  رقم: (1098)


➪የጁምዓ እለት ከሌሎች ቀናት በበለጠ በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋት የማውረጃ ቀን ነው።

🍂የአላህ መልእክተኛ ﷺ
«በጁምዓ ቀንና በጁምዓ ሌሊት በኔ ላይ ሰለዋትን አብዙ። በኔ ላይ አንዴ ሰለዋትን ላወረደ አላህ በሱ ላይ አስር ያወርዳል።» ብለዋልና ትንሽ ሰርተን ከአስር እጥፍ በላይ ለማግኘት ከወዲሁ እድሉን እንጠቀም።
#صحيح الجامع 
الألباني حسن - رقم: 1209


➪የጁምዓ እለት የሳምንቱ ከኃጢኣት መንፂያ ቀን ነው።

➪የአላህ መልእክተኛ ﷺ
«ከባባድ ኃጢኣቶች ኖረው ካልጋረዱት በስተቀር አምስቱ ሰላቶች እንዲሁም ከጁምዓ እስከ ጁምዓ በመሃከላቸው ያለውን ኃጢኣት ያብሳሉ።»¹ በሌላ ዘገባም «ከባባድ ኃጢኣቶች ኖረው ካልጋረዱ በስተቀር ከጁምዓ እስከ ጁምዓ በመሃከላቸው ላለው ማበሻ ናቸው።»² ብለዋል።
,
  ➪ስለዚህ ከከባባድ ወንጀሎች በመራቅ ወይም ተውበት በማድረግ፣ አምስቱን እለታዊ ሰላቶች ጠብቆ በመስገድና የሳምንቱን ልዩ የስብስብ ቀን የጁምዓን ሰላት በመስገድ ተጨማሪ ግድፈቶቻችንን እናፅዳ።

¹صحيح مسلم - رقم: (233)
²الألباني - صحيح الجامع رقم: (3110)

➪ጁምዓ የሳምንቱ ልዩ የመከባበርያ
ቀን ነው።

ሁሉም ሙስሊም ክቡር ነው። ሀብታም ከድሃ ታላቅ ከታናሽ፣ ገዢ ከተገዢ የሚለይበት ቦታ አየደለምና መስጂድ ሲደርስ ያገኘበት ክፍት ቦታ ሊቀመጥ ይገባዋል እንጂ ማንንም አስነስቶ ወይም እንዲነሳ አስደርጎ ሊቀመጥ አይገባውም። 

➪የአላህ መልእክተኛ ﷺ
«አንዳችሁ በጁምዓ ቀን ወንድሙ የተቀመጠበት ቦታ ሊቀመጥ ብሎ እንዳያስነሳው። ነገር ግን ሰፋ ሰፋ አድርጉ ይበል።» ብለዋልና ኢማሙ ኹጥባ ያልጀመሩ እንደሆነ ሰዎችን እንዲጠጋጉለትና እንዲሸጋሸጉለት በስርዓት ማግባትም ይችላል።
صحيح مسلم - رقم: (2178)

☞︎︎︎ጁምዓ የሳምንቱ ልዩ የፅዳት ቀን ነው።

➪የአላህ መልእክተኛ ﷺ
«አንዳችሁ ወደ ጁምዓ ሲሄድ ይታጠብ።» ማለታቸው ተዘግቧል።
#صحيح البخاري - رقم: (882)


➪ጁምዓ የሳምንቱ ልዩ የቁርኣን ቀን ነው።

የአላህ መልእክተኛ ﷺ ቀጣዩን
ብለዋል፣

☞︎︎︎በጁምዓ ቀን ሱረቱል ካህፍን ለቀራ ሰው በሁለቱ ጁምዓዎች መሃል ያለውን ያህል ከብርሃን ያበራለታል።»
#حسنه الألباني في
تخريج مشكاة المصابيح - رقم:(2116)



﷽ { የጁምዓ ቀን ሱናዎች }
1 ገላን መታጠብ
2 ሽቶ መቀባት (ለወንድ)
3 ጥርስ መፍቂያ መጠቀም
4 የክት ልብስ መልበስ ለወንድ (ነጭ ልብስ)
5 በጊዜ ወደ መስጂድ መሄድ
6 በእግር ወደ መስጂድ መሄድ
7 መስጂድ ውስጥ የሰዎችን ትከሻ አለመረማመድ
8 ኹጥባ እየተደረገም ቢሆን ተህየቱ መስጂድ መስገድ
9 ኹጥባ ወደ ሚያደርገው ኢመም መዞር እና ኢማሙን እያዩ ኹንባን ማዳመጥ
10 ኹጥባ በሚደረግበት ወቅት ፀጥታን መላበስ
11 ሰደቃ ማብዛት
12 ከሀሙስ ማታ እስከ ጁምዓ ዐስር ድረስ ሱረቱል ካፍ መቅራት
13 ድዓ ማድረግ
14 የአላህ መልክተኛ(ሠ.ዐ.ወ) ላይ ሰለዋት ማብዛት


✅💧አላህን መፍራት ከጭንቆች ሁሉ ለመውጣት መልካም ሲሳይን ካላሰበው ስፍራ ለማግኘት ብቸኛ ስበብ ነው❗️
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
↪️ አላህን መፍራት የዒባዳዎች ሁሉ ቁንጮና ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው፡፡ የአኼራ ስንቅም ነው፡- ተሰነቁም ፣ ከስንቅም ሁሉ በላጩ አላህን መፍራት ነው…

🔹 ከልብሶች ሁሉ ያማረ ልብስ፡ አላህን የመፍራት ልብስ ነው፡- "የአደም ልጆች ሆይ! ኀፍረተ ገላችሁን የሚሸሽ ግን ልብስ ጌጥንም በእርግጥ በናንተ ላይ አወረድን፤ አላህን የመፍራትም ልብስ፣ ይህ የተሻለ ነው፤ ይህ ከአላህ ታምራቶች ነው፤ ይገሠጹ ዘንድ (አወረደላቸው)"።።።

↪️ውጫዊው ልብስ ገላችን እንዳይታይ ነውራችን እንዳይገለጽ እንደሚሸፍነው ሁሉ፡ ውስጣዊው ልብስ "ተቅዋ" ደግሞ ቀልባችንን ከምቀኝነትና መሰል በሽታዎች እንዳንለከፍና እንዳንዋረድ ይሸፍነናል፡፡

↪️ተቅዋ ማለት፡- በአንተና በአላህ ቅጣት መሀል ጣልቃ ገብቶ እንዳያገኝህ የሚከላከል ጋሻ ማለት ነው፡፡

↪️ተቅዋ ማለት፡- አላህ ባወረደው መሥራት፣ አላህን በታላቅነቱ መፍራት፣ ለመጨረሻው ዓለም መዘጋጀት፣ ባለችን ትንሽ ነገር መብቃቃት ማለት ነው፡

↪️ ተቅዋ ማለት፡- ከአላህ በሆነ ብርሀን እየተመሩና አጅሩንም ተስፋ እያደረጉ ትእዛዙን መፈጸም፣ ከአላህ በሆነ ብርሀን እየተመሩና ቅጣቱን እየፈሩ ወንጀልን ማቆም ማለት ነው፡፡

🔹 ተቅዋ ማለት፡- አላህን ሳያምጹ ሁሌም መታዘዝ፣ ሳይረሱት ሁሌም ማስታወስ፣ ሳይክዱት ሁሌም ማመሥገን ማለት ነው፡፡

🔹አላህን መፍራት ከልብ ነው‼️
👉ነብያችን ስለሏሁአለይሂ ወሰለም ወደደረታቸው በማመላከት አት :ተቅዋ ሃሁና {{አላህን መፍራት ከዚህ ነው በማለት }}ስፍራውን ነግረውናል።ሙስሊም 2564}


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


💢ድሃ ማነው⁉
➖➖➖➖➖

↪️የአላህ መልክተኛሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም ከዕለታት አንድ ቀን ለባልደረቦቻቸው ቁጭ ብለው ሳለ እንድህ በማለት ጠየቁ

“ድሃ ማን እንደሆነ ታውቃላችሁ?”  በማለት ይጠይቃሉ። 


💧ሰሐቦችም እንድህ በማለት መለሱ፣


“▪️እኛ ጋር ድሀ ማለት ምንም ንብረትና ገንዘብ የሌለው ነው።” በማለት ይመልሳሉ። 


💧የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንድህ አሉ

 ↪️ከኡመቴ ደሀ ማለት የትንሳኤ ቀን በብዙ ሰላቶች፤ ዘካዎችና፤ ፆሞች የሚመጣ ሰው ነው፣ግና ይህ ሰው ⤵️

🔹አንድ ወንድሙን ሰድቧል፣ 

🔹ሌላው ላይ ዋሽቷል፣

🔹የአንዱን ገንዘብ ያለአግባብ ወስዷል፣

🔹 የሌላውን ደም አፍስሷል፣

🔹አንዱን መትቷል፣ 

🔹 በሌላው ላይም ድንበር አልፏል፣ 

↪️ያኔም (የትንሳኤ ምርመራ ቀን ) የራሱን ጥሩ ሥራዎች ለበደላቸው በካሳ መልክ አሳልፎ ይሰጣል፣ ጥሩ ሥራው ለመካሻ አልበቃ ይለውና የበደላቸውን ሰዎች ወንጀል((ሐጢአት}} ይሸከማል። ከዚያም ወደ ጀሀነም ይወረወራል።”  በማለት መለሱላቸው። 

{{{ ሙስሊም ሐዲሥ ቁ.653}}}




አስታውስ___ማስታወስ___ለሙዕሚን___ይጠቅማልና።



አቡ ሙሳ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአሏህ መልክተኛ {ﷺ} እንዲህ ብለዋል፡• "አሏህን በሚያስታውስ ና አሏህን በማያስታውስ ሰው መካከል ያለው ምሳሌ ልክ በሕይውት እንዳለ ና እንደ ሞተ {ሰው} ነው ብለዋል
። ቡኻሪ ዘግበታል)።


አቡ ሁረይራ {ረ.ዐ} እንዳስተላለፉት" የአሏህ መልክተኛ {ﷺ} እንዲህ ብለዋል ፡• "በቀን ውስጥ አንድ መቶ ጊዜ ሱብሓነሃልላሁ ወቢ ሐምዲሂ ያለ ሰው ወንጀሎቹ ባህር ላይ እንደሚታይ አረፋ ቢሆኑም እንኳ በሙሉ ይማረለታል። { ቡኻሪ ዘግበታል)።


አቡ ሁረይራ {ረ.ዐ} እንዳስተላለፉት" የአሏህ መልክተኛ { ﷺ}እንዲህ ብለዋል ፡• " በቀን ውስጥ አንድ መቶ ጊዜ " ላ ኢላሃ ኢልለላሁ ወሕደሁ ላሸሪከለሁ ለሁልሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩልሊ ሸይኢን ቀዲይር ያለ ሰው አስር ባሪያዎችን ነፆ እንዱወጣ ተደርጎ ምንዳ ይፃፍለታል።
የአንድ መቶ መልኳም ስራዎች መከላከያ ይሆነዋል።
ማንም ሰው እንደዚህ መልኳም ነገር አይሰራም።

"ይህ ሰው ካደረገው በበለጠ ሁኔታ ከሚሰራ ሰው በስተቀር።
"ቡኻሪ ዘግበውታል"።

الَّذِينَ آمَنُوا وَتَطْمَئِنُّ قُلُوبُهُم بِذِكْرِ اللَّهِ ۗ أَلَا بِذِكْرِ اللَّهِ تَطْمَئِنُّ الْقُلُوبُ

(ሱረቱ አል- ረዕድ፥ - 28)
(እነሱም) እነዚያ ያመኑ ልቦቻቸውም አላህን በማውሳት የሚረኩ ናቸው፡፡ ንቁ! አላህን በማውሳት ልቦች ይረካሉ።

•════•••🌺🍃•••════•
ሼር 👇JoiN👇 & Share👇

@rezakuhakimu
@rezakuhakimu
@rezakuhakimu


🎤🎤🎤🎤 የእውቀት ካዝና ቻናል ተከታታዮች እና አዲስ ገቢዎች እናም ሙስሊም ወንድሞቼ እህቶቼ ለአኬራቹህ በምን እየተዘጋጃቹህ ነው ?በዚክሩ፣በዱአው፣በቂራአቱ ፣በሶላቱ፣ በዘካው እና ሌሎችም አላህ ባዘዘው ነገር እየተገበራቺሁት ያሉትን ቀጥሉበት ያልተገበራቹሁትን ተግብሩ ነገ ልትኖሩም ላትኖርም ትችላላችሁ ።የተፈጠራችሁበትን አላማ አትርሱ👈👈👈👈👈👈👈👈


1, ፊቅህ ማለት: -

☞በቋንቋ ደረጃ ማወቅ (መገንዘብ)

አላህ (ሱ,ወ) እንድህ ይላል: -አላህ ኸይር ያሻለት ሰው ድኑን (ሀይማኖቱን) ያሳውቀዋል እንድረዳ ፣ እንድገነዘብ ያደርገዋል

☞ ፊቅሁል ኢባዳ:- ኢባዳ ላይ ያተኮረ ሶላት ፣ ፆም ፣ዘካ ፣ ሀጂ ላይ ያተኮረ

የፊቁሁል ኢባዳ አይነቶች (ትምህርቶች) 7 አይነት ናቸው ሌላኛው ስለ ቤተሰብ የሚያጠና አለ ቤተሰባዊ ነክ የሆኑ ጉዳዬችን የሚያጠና አለ እንደዚሁም ፊቅሁል ሙአመላት ይህም ህዝቦች በመካከላቸው ያላቸውን ግንኙነት በስፋት የሚያጠና የትምህርት ዘርፍ ነው።ሌላው

አስተዳደር ነክ የሆኑ ጉዳዬችን የሚያጠና የፊቅህ ዘርፍ ነው ይህም ህጎችን (የህዝቦችና የመንግስታት (ከሚያስተዳድራቸው አካል ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያጠና የትምህርት ዘርፍ ነው።ሌላው
ፊቅሁል እቁባት የሚል ቅጣትን በተመለከተ ያጠፋን ሰው ምን አይነት ቅጣት ይጣልበታል ምን ይጠብቀዋል

አለም አቀፋዊ ግንኙነቶችን የሚያጠና የአኘፊቅህ ዘርፍ አለ
ስለ አህላቅ የሚያጠና የፊቅህ ዘርፍ አለ።
በዚህ መልኩ ኡለማዎች በመከፋፈል የፊቅህን ትምህርት ዘርዝረው ያስተምራሉ።

☞አንድ ሰው እውቀትን የሚጨብጥበት ነብዩ (ሰ,ዐ,ወ) በተከተለ መልኩ ኢባዳን ለመፈፀም ነው

ማንኛውም ኢባዳ ተቀባይነት የሚያገኘው በኢኽላስና በሙታብዓ ስለሆነ ነው

✏አንድ ሰው የድን እውቀት ካለው በማንኛውም ዘርፍ እውቀቱን ከተጠቀመበት ኢህላስን በልቡ ውስጥ እንድያመጣ ይረዳዋል

✏አንድ ሰው የድን እውቀት ካለው ☞አቂዳው የተስተካከለ ይሆናል። ☞ኢባዳውም ትክክል ይሆናል።
☞ከሰዎች ጋር ያለውም ግንኙነት የተስተካከለ ይሆናል።
☞ሁሉንም በመስመሩ ለማስኬድ ይረዳዋል።
☞በተቀመጠለት ለመፈፀምም ያግዘዋል።
☞አላህን ብቻ እንድገዛ ይረዳዋል።
☞በቀጥተኛ ጎዳና እንድጓዝም ይረዳዋል።........
☞ከጥመትና ከመሀይምነት እንድወጣ ዋስትና ይሆንለታል።

✏የድን እውቀትን ማወቅ ወደ ጀነት የሚወስድ መንገድ ነው።ይህም በሀድስ ሰፍሯል:-

አላህ ኸይር ያሻለት ሰው የድን እውቀትን ያስገነዝበዋል፣ ያሳውቀዋል።

ከባሮቹ አላህን የሚፈሩት ማናቸው አዋቂዎች ፣ኡለማዎች ናቸው።

☞የድን እውቀትን ለመማር የተጓዘ ወይንም ደግሞ የዚህን መንገድ የተከተለ አላህ (ሱ,ወ) የጀነት መንገድን ያገራለታል።

✏ ፈርድ (ግደታ) ማለት:

አንድን ነገር ከሰራነው የምንሸለምበትና ምንዳ የምናገኝበት ካልሰራነው የምንቀጣበት (የምንጠየቅበት) ስራን የሚያመለክት ማለት ነው። ግደታ የሆነ ነገር እንድንፈፅመው ወይም እንዳንፈፅመው ግደታ የተደረገብን ነገር ማለት ነው።
ፈርድ መከወኑ (መተግበሩ) ግደታ ነው። በመተግበራችን አላህ (ሱ,ወ) ምንዳን ይሰጠናል። ካለተገበርነው ደግሞ እንቀጣበታለን ማለት ነው።

✏ፈርደል አይን ማለት:-
በእያንዳንዱ (በሁሉም) ሰው ላይ ግደታ የሚሆን ማለት ነው
☞ፈርድ ግደታ ማለት ነው
☞አይን በእያንዳንዱ ሰው ላይ ማለት ነው

ምሳሌ:- መታወቅ ያለበት እውቀት ከሆነ ፈርደል አይን ነው ከተባለ ምሳሌ ፋቲሀን አያንዳንዱ ሰው በሰለት ወቅት መቅራት ግደታ ነው

✏ፈርደል ኪፋያ ማለት:-

በሁሉም ሰው ላይ ግደታ የማይሆን ወይም የተወሰኑ የማህበረሰብ ግለሰቦች ካወቁት (ከተገበሩት) ሚወርድ ሌሎቹ የማይጠየቁበት
የተወሰኑ ሰዎች ከፈፀሙት ሀላፊነቱ የሚበቃ ነገር ማለት ነው

ለምሳሌ:- ሶላቱል ጀናዛ መስገድ በሁሉም ሰው ላይ ግደታ አይሆንም

✏ሱና ማለት:-

መሰራት ያለበት ነገር ሆኖ ( እንድሰራ የሚበረታታ) ተግባር ኢባዳ ማለት ነው። ይህም ሽልማት የሚያስገኝ ከተውት ደግሞ የማያስቀጣ
ሱና ሁሉም ሰው እንድሰራ የሚበረታታ ጉዳይ ሆኖ ከተሰራ አጂር (ምንዳ) የሚያስገኝ ካልተሰራ ደግሞ የማያስቀጣ

✏ሱነቱል ሙዓከዳ ማለት:-

ነብዩ (ሰ,ዐ,ወ) ሁል ጊዜ የሚያከናውኑት፣ የማይተውት ፣ ሁሌ የሚተገብሩት ተግባር ነገር ማለት ነው። ጠንካራ ሱና ይባላል።

✏ሱነቱል ሙስተሃብ (የተወደደ ሱና) ማለት:-

የተወደደ ሱና ጠንካራ ያልሆነ ማለት ነው። ይህም ነብዩ (ሰ,ዐ,ወ) ሁል ጊዜ የማያከናውነው ፣ የማይተገብረው አንዳንድ ጊዜ የሚሰሩት ነገር ማለት ነው መስራቱ ግን የተወደደ ይሆናል ።

✏ሙባህ ማለት:-

የተፈቀደ ማለት ነው። ሽልማት የማያስገኝ ቅጣትንም የማያስቀጣ
ብትጠቀመውም ከአላህ ዘንድ ምንዳ የማያስገኝ ከተውት ደግሞ ያያስቀጣ ማለት ነው።

✏ መክሩህ ማለት:-

የተጠላ ማለት ነው። ይህ ደግሞ ሸሪዓው እንዳይተገበር የሚያበረታታ (የሚገፋፋ) ነገር ማለት ነው ። ሸሪአው እንዳንሰራው የሚከለክለን ነገር ነው መክሩህ ይባላል።
☞መክሩህ የሆነን ነገር መተው ያሸልማል (ምንዳ) ያስገኛል ።የተጠላን ነገር ደግሞ የተጠቀመ አይቀጣበትም።

✏ሀራም ማለት:-

የተከለከለ (የተጠላ) ማለት ነው። አንድ ሰው ሀራም የተባለውን ነገር ከተላለፈ የሚያስቀጣ ሀራም የተባለውን ነገር የሚተወውም ከሆነ ይሸለምበታል ምንዳ ያገኝበታል
አንድ ሀራም ነው የተባለን ነገር የተገበረ ፣ የተጠቀመ ፣ የፈፀመ ሰው ይቀጣበታል ። ካልተገበረው ደግሞ ምንዳ ያገኝበታል።

✏ኢጂማዕ ማለት:-

የሙስሊሙ ኡማ ተመራማሪዎች ፣ ታላላቅ አሊሞች ፣ ኡለማዎች የተስማሙበት ጉዳዮች በነርሱ ስምምነት መከተል ግደታ የሆነ ነገር ማለት ነው።

✏ቅያስ ማለት:-

አንድ ነገር ቀጥታ ማስረጃ ያልተገኘለት አንድን ጉዳይ ምሳሌ አስመልክቶ ቀጥተኛ የሆነ የፁሁፍ ማስረጃ ካልተገኘለት ከሀዲስ ፣ በቁርዓን ማለት ነው ለሱ ዋስትና ሊሰጥ የሚችል መፍትሄ ከሌላኛው መውሰድ
አንድ መልእክትን የሚያስተላልፍ ሌላ አያ አለ እንበልና ያ ጉዳይ ከዛ ላይ የነብዮችን ምላሽ እንድሰጥ ሆኖ ይገኛል ይህ አይነቱ ቂያስ ይባላል።
☞ አንድን ነገር ለሌሎች ሀሳቡን ከተረዱ በኃላ ከዙያ ላይ ለሌሎቹ ጉዳዮች የመፍትሄ ሀሳብ ማመንጨት (አቅጣጫ መጠቆም) ቂያስ ይባላል።

✏ጠሃራ ማለት: -

በቋንቋ ደረጃ (ነዛፋ) ንፅህና ማለት ነው ።
አወንታዊ ፍቹ: ሁለት ትርጉሞች አሉት

☞ አል ጠሃራቱል ማዕነውያ:- የማይታየው የማይዳሰሰውን አካል ልብን የሚመለከት ጠሃራ ማለት ነው

☞ አል ጠሃራቱል ኪስያ: - አካላችንን ማፅዳት ፣ ልብሳችንን ውጫዊ የሆነን ነገር የሚታየውን ፣ የሚዳሰሰውን ነገር የሱን ጠሃራ መጠበቅ

✏ኡለማዎች በቀላሉ እንድንገነዘብ አስቀምጠውልናል
ለምሳሌ:- አል ጠሃታቱል ማዕነውያ ይህን በሁለት ከፍለውታል
☞ትልቁ :-ቀልባችንን ከሽርክ ፣ ከቢድዓ ማፅዳት ከዛ በተውሂድ መሙላት ፣ በተውሂድ አመለካከት መተካት ይህ አል ጠሃራቱል ኩብራ ይባላል።
ቀልብን ከኩራት ፣ ከኒፋቅ ፣ ከፊህድ ከተንኮል ባጠቃላይ ከክፉ አመለካከቶች ማፅዳት አለብን ። ከዚያም በጥሩ አስተሳሰብ በተውሂድ ፣ በአላህ ውደታ ፣ በነብዩ (ሰ,ዐ,ወ) ውደታ ልንሞላት ይገባል።

☞ትንሹ: - ከተለያዩ ወንጀሎች ቀልብን ማፅዳት ነው። ከዚያ በኃላ በመልካም ነገሮች መሙላትና መጠበቅ (አል ጠሃራቱል ሹብራ)


•════•••🌺🍃•••════•
ሼር 👇JoiN👇 & Share👇
https://t.me/AAASELEFYA
https://t.me/AAASELEFYA


روائع التلاوات | وما من دابة في الأرض إلا على الله رزقها .. - إبراهيم العسيري

ቁርአን የጥበቦች ሁሉ መፍለቂያ ድንቅ እና ታላቅ መለኮታዊ መጽሐፍ ሲሆን ዘላለማዊ ተአምር የሆነ ሙሉ የህይወት መመሪያ ነው።
🍃 ┈┈•✿❁✿•┈┈•🍃
🌸ውብ ቲላዋ 🌸

https://t.me/Quran_Nur_Hayati


‹‹የነብዩን ሙሀመድ ﷺ ሱና መከተል»

« الإتباع سنة رسول الله ﷺ »

🎙 በኡስታዝ አብራር አቡ አብዱረህማን (ሀፊዘሁላህ)


📌 ትምህርቱን ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ

https://t.me/ustazabrar/172


✥--- ስድስቱ የተውበት መስፈርቶች---✥

በህይወታችን ብዙ ጊዜ ወንጀሎችን እንፈፅማለን። አላህ ያደለው በወንጀሉ አላህ ፊት እንዳይጠየቅ ተውበት ማድረግን ያስባል። ግን ስንቱ ነው ተውበቱ መስፈርቶችን የሚያሟላ እንዲሆን የሚጨነቀው? እራሳችንን በሚገባ ጠይቀን እናውቃለን?! ለመሆኑ መስፈርቶቹን ምን ያህሎቻችን በሚገባ እንለያቸዋለን? ለማያውቁ ጥቆማ፣ ለሚያውቁ ማስታወሻ ይሆን ዘንድ እጠቅሳለሁ። የተውበት መስፈርቶች ስድስት ናቸው። እነሱም:–

① ኢኽላስ: – አላህን ብቻ በማሰብ ሊፈፀም ነው። አንድ ሰው ወንጀልን የሚቶወው ዱንያዊ ጥቅሞችን አስቦ ከሆነ የመጀመሪያውን የተውበት መስፈርት ዘንግቷል።

② ወንጀሉን ማቆም:– አንድ ሰው የሚፈፅመውን ወንጀል ባላቋረጠበት ሁኔታ "ቶብቻለሁ" ቢል ቀልድ ነው የሚሆነው። ስለዚህ ተውበት ያሰበ ሰው ጥፋቱን በቀጠሮ ሳይሆን ቀጥታ ሊያቆም ይገባል።

③ ወደ ጥፋቱ ዳግም ላይመለሱ ቁርጠኛ ውሳኔ ላይ መድረስ። አንድ ሰው ከወር ቡሀላ እንደሚመለስ እያሰበ ረመዳን ሊገባ ሲል አንድን ወንጀል ቢተው መስፈርት ስላላሟላ ተውበት አድርጓል ማለት አይቻልም።

④ በወንጀሉ መፀፀት። ሰውየው ሲፈፅመው በቆየው ወንጀል ላይ ደንታ ቢስ ከሆነ ተውበቱ የሐቂቃ አይደለም። ፀፀቱ "ሰው ምን ይለኛል" ወይም "ክብሬ ጎደፈ" በሚል ሳይሆን የጌታውን ህግ በመጣሱ ሊሆን ይገባል። ለምሳሌ ብዙ ሰዎች ዝሙት ፈፅመው ጌታቸው ዘንድ ካለው ሂሳብ ይልቅ ዱንያ ላይ ያለው የሰው ወሬ ሲያስጨንቃቸው ይፀፀታሉ። እንዲህ አይነት ፀፀት የተውበትን መስፈርት አያሟላም። ይልቅ ከዛሬው የበዛ ህዝብ ፊት ነገ በአኺራ መዋረድ ከመምጣቱ በፊት ትክክለኛውን ፀፀት እዚሁ ልናስገኝ ይገባል።

⑤ ተውበቱ ወቅቱን የጠበቀ መሆን። ይህም ሞት አፋፍ ላይ ከመድረሱ በፊት እና ፀሀይ በመጥለቂያዋ ከመውጣቷ በፊት መሆኑ ነው።

⑥ ወንጀሉ የሰው ሐቅ መግፋት ከሆነ ሐቁን ሊመልስ ወይም ይቅርታውን ሊያገኝ ይገባል። ወይም ኢስቲግፋርና ኸይር ስራ ሊያበዛ ይገባል።

┄┅┄┅┄┅┄┅┄┅┄┅┄┅┄┅┄
ሼር 〰〰〰 ይደረግ
•┈┈┈•┈┈•⊰✿••||✿⊱•┈┈•┈┈•

@FeruVsAb


⭕️ ወንድ ሴትን መጨበጥ ሴትም ወንድን መጨበጥ
በእስልምናችን እንዴት ይታያል?

ነብያችን (ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ) በዚህ ዙሪያ ምን እንደተናገሩ እንመልከት:-
" ﻷﻥ ﻳﻄﻌﻦ ﻓﻲ ﺭﺃﺱ ﺃﺣﺪﻛﻢ ﺑﻤﺨﻴﻂ ﻣﻦ ﺣﺪﻳﺪ ﺧﻴﺮ
ﻟﻪ ﻣﻦ ﺃﻥ ﻳﻤﺲ ﺍﻣﺮﺃﺓ ﻻ ﺗﺤﻞ ﻟﻪ "

"የማትፈቀድለትን ሴት ከሚነካ የአንደኛችሁ ጭንቅላት
በብረት መርፌ ቢወጋ ይሻለዋል።" (ጦበራኒ ዘግበውታል)

ነገር ግን በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ቡዙ መስሊም ወንዶችና
ሴቶች የማይፈቀድላቸውን ሰዎች በመጨበጥ እራሳቸውን
እየበደሉ ይገኛሉ። አልፎ ተርፎም ከወንጀሉ የበለጠ የሚያስጠሉ ምክንያቶችን ይደረድራሉ ለናሙና ያህል:-

* "ልባችን ንፁህ ናት" ይላሉ! የነዚህ ሰዎች ልብ ከነብዩ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ልብ የበለጠ ንፁህ ናትን? ለመሆኑ በዚህ ዓለም ላይ ከነቢዩ(ﷺ) የበለጠ ልቡ ንፁህ የሆነ ሰው አለ? ከርሳቸው በላይ ልቡ መልካም ነገር የሚያስብ ሰው አለን?

* "ይህንን መተው ለኛ ሀገር ይከብዳል" ይላሉ እስልምና የመጣው ነብያችንም (ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ) የተላኩት ለዓለም እንጂ ለሳውዲ፣ ለኢትዮጲያ፣ ለዓረብ፣ ለፈረንጅ፣ ለጥቁር ለሀብታም፣ ለድሀ ብለው በመለየት አይደለም አላህ እንዲህ ይላል:-

ﻭﻣﺎ ﺃﺭﺳﻠﻨﺎﻙ ﺇﻻ ﺭﺣﻤﺔ ﻟﻠﻌﺎﻟﻤﻴﻦ
"ለዓለማት እዝነት ቢሆን እንጂ አላክንህም"

ስለዚህ ሸሪዓችን ማንንም ሳይለይ ሁሉንም ይመለከታል! እስቲ ሁላችንም አንዴ ቆም ብለን እናስተውል በሚስማር ጭንቅላታችን ተወግቶ በአንድ ጎን ገብቶ በሌላ ጎን ቀዶ
መውጣቱ የማትፈቀድን ሴት ከመጨበጥ ይሻላል መባሉ
አያሰደነግጥምን? አላህ እርሱን የሚፈራ ልብ ይስጠን!!!

በመጀመርያ ደረጃ መጨበጥ የተፈቀዱ ዘመዶች እንመልከት

🌹ውድ ወንድሜ

እናትህ፣ እህትህ፣ የወንድምህ ልጅ፣ የእህትህ ልጅ፣ ሚስትህ፣ ልጅህ፣ አክስትህ፣ የሚስትህ እናት ለአንተ እንድትጨብጥ የተፈቀዱ ናቸው።

🌹ውዷ እህቴ

አባትሽ፣ ወንድምሽ፣ አጎትሽ፣ ባልሽ፣ ልጅሽ፣ የወንድምሽ ልጅ፣ የእህትሽ ልጅ፣ የባልሽ አባት እነዚህ መጨበጥ የተፈቀዱልሽ የቤተሰብ አባላት ናቸው።

ውድ ወንድሜ መጨበጥ የተከለከሉ ዘመዶችህ እወቃቸው

❌የአጎትህ ልጅ (በእናትም በአባትም)
❌የአክስትህ ልጅ (በእናትም በአባትም)
❌የወንድምህ ሚስት
❌የሚስትህ እህት
👉እነዚህ ሴቶችና ሌሎችም ልትጨብጣቸው አልተፈቀደልህም! እነዚህ ካልተፈቀዱልህ ከነዚህ የራቁት ደግሞ የባሰ ነው።

እህቴ ሆይ! መጨበጥ የተከለከሉ ዘመዶችሽ እወቂያቸው

❌የአጎትሽ ልጅ (በእናትም በአባትም)
❌የአክስትሽ ልጅ (በእናትም በአባትም)
❌የባልሽ ወንድም
❌የእህትሽ ባል
👉እነዚህና ሌሎችም ወንዶች ልትጨብጫቸው
አልተፈቀደልሽም! እነዚህ ካልተፈቀዱልሽ ከነዚህ የራቁት ደግሞ የባሰ ነው።

ወንድምና እህቶቼ ሆይ! ይህ በወንጀል ላይ ችክ ማለታችን
እስከመቼ ነው? ቀብር እስክንገባ? የሰዎችን ወሬ እየፈራን! ከሰዎች እናፍራለን ከአለማቱ ጌታ ያለን ፍራቻ የታል? ከሰዎች እያፈርን ከሰዎች ጌታ አናፍርምን ?

አላህ እርሱንና መልክተኛውን ከሚታዘዙት መልካም ባሮቹ ይጨምረን !!! አሚን
ــــــــــــــــــــــــــــــــ


💎 ተውራት የወረደው ለነብዩላህ ሙሳ ነበር።
💎 ኢንጂል የወረደው በነብዩላህ ኢሳ ዐ.ሰ ላይ ነበር።
💎 ዛቡር የወረደው በነብዩላህ ዳውድ ዐ.ሰ ላየ ነበር።
💎 አላህ ሱ.ወ ለሶዶማውያን የላከው ነብይ ነብዩላህ ሉጥ ዐ.ሰ ነበር።
💎 ነብዩላህ ሉጥ ዐ.ሰ የአናጢነት ሙያ ባለቤት ነበሩ።
💎 ነብዩላህ ሙሳ ዐ.ሰ እረኛ ነበሩ።
💎 ነብዩላህ ኢብራሂም ዐ.ሰ ለመጀመሪያ ጊዜ በሰይፍ የተዋጉ ነብይ ነበሩ
💎 ነብዩላህ ሱለይማን ዐ.ሰ ለመጀመሪያ ጊዜ بسْـــــــــــــــــــمِ اللّهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِيْم ብለው የፃፉ ነብይ ናቸው።
💎ነብዩላህ ኢብራሂም ዐ.ሰ ለመጀመሪያ ጊዜ ለኢስላም ብለው የተሰደዱ ነብይ ናቸው።

💎ነብዩላህ ሱለይማን ዐ.ሰ ለመጀመሪያ ጊዜ ሳሙናን የተጠቀሙ ነብይ ናቸው።
💎ነብዩላህ ኢሳ ዐ.ሰ ለመጨረሻው ወደ እስራኤል ልጆች የተላኩ ነብይ ናቸው።
💎ነብዩላህ አደም ዐ.ሰ ወደ መሬት ከመውረዳቸው በፊት በጀነት ይኖሩ ነበር።
💎ነብዩላህ አዩብ ዐ.ሰ ለረጅም ጊዜያት በህመም ሲሰቃዩ ኖረዋል።
💎የነብዩላህ ዩሱፍ ዐ.ሰ ልብስ ታሪክ በቅዱስ ቁርአን ተገልፃል።
💎የብዩላህ አደም ዐ.ሰ የተፈጠሩት በጁመዓ ቀን ነበር።
💎ነብዩላህ ኢብራሂም ዐ.ሰ የተቀበሩት በፊልሰጤም አል ኻለል በተባለች ቦታ ነው።
💎አላህ በድምፅ ብቻ ከሁለት ነብያቶች ጋር አውርቷል። እነሱም ነብዩላህ ሙሳ ዐ.ሰ እና ነብዩ ሙሀመድ ﷺ ናቸው።
💎124,000 ነብያቶች ወደ ሰው ልጆች ተልከዋል።
💎ሚና ከተማ በምስራቅ አቅጣጫ ከመካ በ3 ማይል ርቀት ላይ የምትገኝ በረሃማ ቦታ ስትሆን ከሐጅ ስርዓቶች አብዛኛው የሚከናወነው በዝችው በረሃማ ከተማ ሚና ላይ ነው።
💎ቁርአን በአለም ለይ በ103 ቋንቋዎች ገደማ ተተርጉሟል።
💎የኮሙኒዝም ስርዓት በተፈጥሮ ሃይማኖትን ይቃወማል በተለይም እስልምናን
💎የመጀመሪያው ኃጢያት (ወንጀል) ኩራት ነው። እሱም በሰይጣን (ኢልቢስ) ነው የተፈፀመው።
💎በፍርድ ቀንየሚጠየቀው የመጀመሪያ ጥያቄ "ሰላት" ነው።
💎አንዲት ሴት ባለቤቷ ከሞተ በኃላ ትዳር ለመመስረት 4 ወራት ከ10 ቀናት መቀመጥ ይኖርባታል። ከዚያ በኃላ አዲስ ትዳር መመስረት ትችላለች
💎አብደላህ እና አብዱረህማን ተመራጭ የኢስላም ስሞች ናቸው። ሙሀመድ የሚለው ስም በአለም አንደኛው ስም ነው።
💎ጀነት በጣም ጥልቅና እጅግ በጣም ሰፊ ከመሆኗ የተነሳ ስፋቱ በሰዎች ሊደረስበት አይችልም።
💎ሰዎች በጀነት ውስጥ ምን እንደሚመስሉና ምን እንዳለ ቢያውቁ ኖሮ በዚህ ዱንያዊ ኑሮ አይደሰቱም ነበር
💎የፈርዖን ሚስት የሆነችው አስያ በተትረፈረፈ ጀነት ውስጥ ትሮራለች፤ ባለቤቷ ፈርዖን ደግሞ በጀሃነም ለዘላለም ይኖራል።
💎 አልይ ረ.ዐ በኢስላም የመጀመሪያው እስር ቤት የገነቡ ሰው ናቸው።
💎ዑመር ረ.ዐ በኢስላም የመጀመሪያውን ደብዳቤ ስርዓትን የተጠቀሙ ሰው ናቸው።
💎ዑመር ረ.ዐ በኢስላም የመጀመሪያውን የሂጅራ ካላንደር የፃፉ ሰው ናቸው።
💎አጅማዕ ማለት ኡለሞች የተስማሙበት ማጣቀሻ ነው።
💎የእስልምና ህግ (ህገ-መንግስት) ሸሪዓ ይባላል።
💎የኢደል ፊጥረ በአል የሚከበረው በሸዋል ወር ውስጥ ነው።
💎የኢደል አድሃ (አረፋ) በአል የሚከበረው በዙለሂጃ ወር ውስጥ ነው
💎የኢድ ሰላት ሁለት ረካዓ አሉት። የመጀመሪያው ረከዓ 7 ተክቢራ፤ ሁለተኛው ደግሞ 5 ተክቢራ አለው።
💎ረመዳን በሂጅራ አቆጣጠረ 9ኛው ወር ነው።
💎ሙሃረም በሂጅራ አቆጣጠር የመጀመሪያው ወር ነው።
💎ለይለቱል ቀድር በረመዳን ወር እንደምትገኘ ገልፆዋል።
💎ሽርክ አላሀ ሱ.ወ ይቅር የማይለው ወንጀል ነው።
💎የደጃል መምጣት ከየውመል ቂያማ ምልክቶች ትልቁ ነው።
💎አቂቃ ማለት አዲስ ልጅ ሲወለድ በመሰዋትነት መልኩ የሚቀርብ እንስሳ ነው።
💎ዚክር (አላህ ሱ.ወ ማውሳት) ማለት ሲሆን በልብም በምላስም የሚተገበር ነው።
💎ዱዓ ማለት አላህ ሱ.ወ አላህ ሱ.ወን የሚፈልጉትነ ነገር መለመን ማለት ነው።
💎ታማኝ ምንጭነታቸው ከተረጋገጡት ውስጥ ሰሂህ አል ቡኻሪ እና ሙስሊም ዋናዎቹ ናቸው።
💎ኢህራም ማለት አንድ ሰው ሀጅ ወይም ኡምራ ለማድረግ መነየት ነው።
💎ኢስቲንጃ ማለት ራስን ከቆሻሻ (ነጃሳ) ነገር በንፁህ ውሃ ወይም አፈር መፀዳዳት ነው።
💎ተቅዋ ማለት የአላህን ሱ.ወ መፍራት ሲሆን እሱ ያዘዘውን መስራት፤ እሱ የከለከለውን መራቅ ማለት ነው
💎ጠዋፈ ማለት የአላህን ሱ.ወ ቤት (ካባን) 7 ጊዜ መዞር ነው።
💎በመስጂደ ሀረም(መካ) መስገድ የ100,000 ደረጃ ያህል ከሌሎች መስጂዶች በለጨ ነው።
💎በመስጂደል ነበዊ (መዲና) መሰገድ የ1000 ደረጃ ያህል ከሌሎች መስጂዶች ይበልጣል።
💎የውሙል ቂያማ ቀን የሚውለው በአርብ (ጁመዓ) ቀን ላይ ነው።
💎የጀነት በር የሚከፈተው በነብዩ ሙሀመድ ﷺ ነው።
💎ህፃናት፣ ባሪያዎች፣ በሽተኞች፣ ሴቶች እና መንገደኞች የጁመዓን ሰላት መስገድ አይገደዱም።
💎አንድ ሙስሊም ትዳር ለመመስረት 2 ምስክሮች ያስፈልጉታል።
💎ሎተሪ በኢስላም አይፈቀድም።
💎በወርቅ፣ በብር ላይ መብላት (መጠጣት) ሃራም ነው።
💎በኢስላም ብድር ይፈቀዳል። ነገር ግን ወለድ ካለው ሃራም ነው።
💎አንዲት ሴት ባሏ ከሞተባት የሚፈቀድላት 1/8ኛውን(አንደ ስምንተኛውን) ብቻ ነው።
💎ተይሙም ካደረጉ በኃለ ውሃ ሲገኝ ተይሙም ይበላሻል።

💎በአጋጣሚ አንድ ሰው ካስመለሰው ፆሙ አይበላሽም።

💎ለመንገደኛ ፆም ለመፆም አይገደድም።

💎ሴቶች የውበት ጌጣ ጌጦችን መጠቀም ይችላሉ።

💎ኮከብ ማስቆጠርም ሆነ መቁጠር በኢስላም ሃራም ነው።


ማንኛው ሙስሊም ሊያውቃቸው የሚገቡ 55 አጫጭር
መረጃዎች

1, ኡመር ኢብኑል ኽጧብ(ረ.ዐ) እስልምናን ለመቀበል ምክንያት
የሆነው ሱራ
♦ ሱራቱል አል-ጣሃ
2, ነብያችንን(ሰ.ዐ.ወ) ለመመረዝ የሞከረች አይሁዳዊ ሴት
♦ ዘይነብ ቢንት አልሃሪዳ
3, ለመጀመሪያ ጊዜ መካ ላይ መኖር የጀመሩት ሰዎች
♦ ሂጅርና
ኢስማኤል
4, ስለ ጋብቻ ህጎች የሚናገረው የቁርኣን ምእራፍ
♦ሱራቱል አል-ኒሳ
5, የአንድ ነብይ ህዝቦች ግመል ከተራራው ውስጥ ይውጣልን
ብለው ነበር ህዝቦቹም
♦የነብዩ ሳልህ(ዐ.ሰ) ህዝቦች
6, ከነብዩላህ ሱለይማን(ዐ.ሰ) ወደ ቢልቄስ መልክት ያደረሰው
♦ሁድሁድ የሚባል ወፍ
7, ብረት የተገራለት እንደፈለገው የሚያጣጥፍ ነብይ
♦ነብዩላህ ዳውድ(ዐ.ሰ)
8, ይህን ሱራ አንድ ጊዜ ያነበበ(የቀራ) 1000 አያዎችን
እንዳነበበ ይቆጠርለልታ
♦ሱራቱል አት-ተካሱር
9, የነብያችን(ሰ.ዐ.ወ) እናት ሙሉ ስም
♦አሚና ቢንት ወሀብ
10, ነብያችንን(ሰ.ዐ.ወ) ጡት ለማጥባት ወደ ገጠር
የወሰደቻቸው ሴት
♦ የበኒ ሰዐዷ ሐሊማ
11, እናታችን አኢሻ(ረ.ዐንሀ) ያስተላለፉት ሀዲስ
♦2210 ሀዲስ
12, መካ ውስጥ ሙሽሪኮችን ተደብቆ ቁርኣን ሲያቀራ የነበረ
ሱሀብይ
♦ከባብ ኢብን አቡጧሊብ ይባላል
13, የነብዩ ሀሩን ዝርያዎች
♦ በኒ ነዲሮች ናቸው
14, ነብያችን(ሰ.ዐ.ወ) ከሞቱ ቡሀላ እስልምናን የካዱ ሰዎችን
ለመዋጋት ታጥቆ የተነሳው ሱሀባ
♦አቡሶፍያን ቢን ሀርብ
15, በእስልምና መሰረት በምላሳችን ልንዋጋቸው የሚገባን
♦ሙናፊቆችን ነው
16, ቁርአን ውስጥ የተጠቀሱ መከራን ቻይና ታጋሽ የሆኑ ነብያት
5 ናቸው
♥ረሱል (ሰ.ዐ.ወ)
♥ሙሳ (ዐ.ሰ)
♥ኢሳ (ዐ.ሰ)
♥ ኑህ (ዐ.ሰ)
♥ኢብራሂም (ዐ.ሰ)
17, ከሰማይ ከአላህ ዘንድ መፀሀፍ የወረደላቸው
~ ሙሳ (ተውራት)
~ ዳውድ (ዘቡር)
~ ኢሳ (ኢንጅን)
ሙሀመድ (ፈርቃን)
18, መካ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ጣኦትን ያመጣው ሰው
= ኢብን ሉሂይ
19, በቁርኣን ውስጥ አንዲት ምእራፍ አለች አንድ ሰው ምህረት
እስኪያገኝ ድረስ አማላጅ ሆሄንለታለች
= ተባረከለዚ ቢየዲሂል ሙልኩ
20, ይቺ አንቀፅ የወረደችው ጁሙአ ቀን የአረፋ እለት ነው ""
ዛሬ ሀይማኖታችሁን ለእናንተ ሞላሁላችሁ።ፀጋየንም በእናንተ
ላይ ፈፀምኩ።ለናንተም ኢስላምን ከሀይማኖት በኩል ወደድኩ።"""
ሱራቱል አል-ማኢዳህ
21, አቡል ሚስኪን ወይም ዙል ጅናኔን በመባል የሚታወቀው
ሱሀባ
= ጃእፋር ኢብን አቡጧሊብ
22, ነብያችን(ሰ.ዐ.ወ) ከኔ ቡሃላ ነብይ ቢኖር ኖሮ እሱ ይሆን
ነበር ያሉት
=አቡበከር ሲዲቅ
23, ኡስማን ኢብኑ አፋን ሲገደል ደሙ የፈሰሰበት አንቀፅ
የሚገኝበት ሱራ
= ሱራቱል አል-በቀራህ
24, ለዲኑ ብሎ አባቱን የገደለው ሱሀባ
= አቡ ኡበይዳህ ወይም አማር ይባላል
25, ዛቱል ኑጧቂን በመባል የምትታወቀው ሱሀቢይት
= አስማ ቢንቱ አብበከር
26, ዛቱል ሂጅረቴን በመባል የምናውቃት ሱሀብይት
= ሩቅያ ቢንቱ ሙሀመድ(ሰ.አ.ወ)
27, አብበከር ሲዲቅ(ረ.ዐ) በገንዘብ ገዝተው ነፃ ያወጡት ሱሀባ
= ቢላል ኢብኑ ረባህ
28, የእሙ አይመን የቀድሞ ስሟ
= በረካ
29, በቁርኣን ውስጥ የተጠቀሰች ትንሿ እንሰሳ
= ትንኝ
30, ነብያችን(ሰ.ዐ.ወ) ሁሉም ነብይ ሀዋርያ አለው የኔ ሀዋርያ
ነው ያሉት
= ዙበይር ኢብኑ አዋም
31, ያ አዩሀን ነብዩ የሚለው ቃል ቁርአን ውስጥ
= 11 ጊዜ ተጠቅሷል
32, የነብያችንን(ሰ.አ.ወ) የጫማዎትን ኮቴ ጀነት ውስጥ
ሰማሁት ያለው ሱሀባ
= ቢላል ኢብኑ ረባህ
33, በበድር ጦርነት ላይ የተካፈሉ ሙስሊሞች ብዛት
= 315----317
34, በኡሁድ ጦርነት ላይ የተካፈሉ ሙስሊሞች ብዛት
= 700
35, ለነብያችን(ሰ.ዐ.ወ) ሙሀመድ የሚለውን ስም ያወጣላቸው
= አብዱል ሙጦሊብ
36, የመጀመሪያው በኢስላም የተወለደ ሱሀባ
= አብዱላህ ኢብን ዙበይር
37, የመጨረሻው ኽሊፋ የነበረው
= አሊይ ኢብን አቡጧሊብ
38, የአባታችን አደም(ዐ.ሰ) ስም በቁርኣን ውስጥ የተጠቀሰው
= 25 ጊዜ
39, አባታችን አደም(ዐ.ሰ) የተፈጠሩት
= ጁሙአ ቀን
40, አላህ(ሱ.ተ) ሽይጧንን ከምን ፈጠረ
= ከእሳት ነበልባል ጫፍ
41, ጅሀምነ ለስንት አመት ተቀጣጠለች
= ለ3000 አመት
42, የውመል ቅያማ አላህ ፊት መጀመሪያ የምጠየቅይበት
ስራችን
= ሰላት
43, አንድም ቀን ሰላት ሳይሰግድ ጀነት የገባው ሱሀባ
= አማር ኢብን ሳቢት
44, የኻሊድ ኢብኑ ወሊድ ቀብር የሚገኘው
= ሀምስ ሶሪያ
45, የአላህ መልክተኛ(ሰ.ዐ.ወ) ዘረኝነትን ምን ብለው ጠሯት
= ጥምብ
46, የነብያችን(ሰ.ዐ.ወ) እናት ለነብያችን(ሰ.ዐ.ወ) ያወጡላቸው
ስም
= አህመድ
47, ነብያችን(ሰ.ዐ.ወ) መቼ ሞቱ
= 12ተኛ ረቢኡል አወል 11 አመት ሂጅራ
48, የነብያችን(ሰ.ዐ.ወ) ልጆች
~ ቃሲም
~ አብደላህ
~ ኢብራሂም
~ ዘይነብ
~ ሩቅያ
~ ፋጢማ
~ እሙከልሱም
49, አህለል ቤቶች እነንማ ናቸው
= የነብያችን(ሰ.ዐ.ወ) ቤተሰቦች
50, ነብያችን(ሰ.አ.ወ) ወደ መዲና ሲመጡ በእንግድነት ያረፉት
= አቡ እዩብ አል አንሳሪ ቤት
51, የኽባስ ኢብን አል አንሳሪን በቁሬይሾች መገደል አይቶ
የሰለመው
= ሰዓድ ኢብን አሚር
52, የካእባን ቁልፍ የሚይዝ የነበረው ሱሀባ
= ኡስማን ኢብን ጦልሀ
53, ይችን ሱራ 4 ጊዜ የቀራ ቁርኣን እንዳከተመ ይቆጠርለታል
= ሱራልቱ አል--ኢኽላስ
54, በመልክ ከነብያችን(ሰ.አ.ወ) ጋር የሚመሳሰለው ሱሀባ
= ጃእፈር ኢብን አቡጧሊብ
55, በጀነት ውስጥ የሴቶች አለቃ
= ፋጢማ ቢንቱ ሙሀመድ(ሰ.አ.ወ)


⭐️ በዱንያ ላይ የሚያምር ጓደኛ ብሎ ማለት ☞ ተስቢህ (ሱብሀነሏህ አዚም ) እና ሌሎችም ዚክሮች ﺗﺴﺒﻴﺢ

🔰 በዱኒያ ላይ ትልቁ ጓደኛ ብሎ ማለት እሱ ☞ ቁርአን ነው። ﺍﻟﻘﺮﺁﻥ

⭐️ በዱኒያ የሚያምር ውደታ ብሎ ማለት እሱ ☞ ለአላህ ብሎ መውደድ ማለት ነው። ﺍﻟﺤﺐ ﻓﻲ ﺍﻟﻠﻪ

🔰በዱኒያ ላይ ትልቁ ልብ ( ቀልብ) ብሎ ማለት ☞ የሙእሚን ልብ ( ቀልብ) ነው

⭐️በዱኒያ ላይ እውነተኛ ውደታ ማለት☞ አላህን መውደድ ነው

🔰 በዱኒያ ላይ ምርጡ ግደታ ( ፈርድ) ብሎ ማለት እሱ ☞ ሶላት ነው።

⭐️ በዱኒያ ላይ ምርጡ እንባ ማለት ☞ በአላህ ፍራቻ የምትወጣ እንባ ናት።

🔰 በዱኒያ ላይ ትልቁ ጀግንነት ማለት ☞ አላህን መፍራት ነው።

⭐️ከመልክ ሁሉ መልክ ከሚያምረው ሁሉ የሚያምረው እሱ☞ ላኢላሀ ኢለሏህ ሙሀመድ ረሱለሏህ ነው። ﻻﺇﻟﻪ ﺇﻟﻠﻪ ﻣﺤﻤﺪ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ


#ሰደቃ

#ሰደቃ ለሰጪው ሰላም ይሰጣል

↔️ #ሰደቃ ከሚቀበለው ይልቅ ለሰጪው ደስታ ይሰጣል

ከሚቀበል እጅ የሚሰጥ እጅ በላጭና የተሻለ ነው

አንተ የአም ልጅ ሆይ ስጥ ይሰጥሃል

በየቀኑ ሁለት መላይኮች ይላካሉ

✅ አንድኛው ሰደቃ ለሚሰጥ ሰሰው የተሻለ ነገር ተካለት ጨምርለት በማለት ዱዓ ያደርጉለታል
✅ ሁለኛው ለእነዛ ለሚቋጥሩ ስስታሞች ብሩን በሌላ በኩል በተለያየ ነገር እንዲያወጣው ጥፋት ላክባቸው በማለት ዱዋ ያደርጉበታል
አላሁ ሙስታዕን

ደስታን ከሚያመጡ ነገሮች ውስጥ ለሌሎች ማዘንና ሰደቃ መስጠት በዋነኛነት ይጠቀሳሉ።

ﺃَﻧﻔِﻘُﻮا ﻣِﻤَّﺎ ﺭَﺯَﻗْﻨَﺎﻛُﻢ

ከሰጠናችሁ ነገር ለግሱ፡፡
( አል_በቀራህ 254).

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

157

obunachilar
Kanal statistikasi