".....ልቡ ግን ከእኔ ርቋል..."
አንድ ባሕታዊ ብዙ ሰዎች ሰብስበው እየሰበኩ ሳለ ጭራቅ ከጫካ ወደ ጉባኤው ይመጣል። ወደ ባሕታዊው ቀረብ ይልና "አባቴ እንግዲህ እንደምታውቁት የእኔ ሕልውና በሰው ሥጋና ደም ላይ የተመረኮዘ ስለሆነ እነኝህን ሰዎች ልበላቸው ነው" አላቸው።
ባሕታዊውም የሰው ሥጋ መብላትህን አውቃለሁ ግና እነዚህ ልጆቼን አትበላሸቸውም የክርስቶስ ናቸውና አትችልም ብለው ገዘቱት።
አቶዬም ግድ የሎትም አባቴ እኔ የክርስቶስ የሆኑትን አልበላም ንክችም አላረግም ሲል ቃል ገባላቸውና ተለያዩ።
ከሄዱበትም ሲመለሱ ጭራቁ ባሕታዊው ያስተማሩትን ሰው ሁሉ በልቶ ከንፈሮቻቸውንና ምላሳቸውን አስቀርቶ ጠበቃቸው ። በጉዳዩም በጣም የተቆጡት ባሕታዊ ምነው የክርስቶስ ናቸው እንዳትበላ አላልኩህም አሉት።
ጭራቁም በሰው ደም የለሰለሰውን ከንፈሮቹን በምላሱ እያበሰ "የክርስቶስ የሆኑትን አሁንም አልበላሁም" ብሎ በኩራት መለስላቸው።
ምን ማለትህ ነው ያስቀረኸው የለም እኮ ቢሉት "አባቴአባቴ የክርስቶስ የሆነው ምላሳቸው ነው። ክርስቶስ ያለው ከንፈሮቻቸውና ምላሳቸው ላይ ብቻ ስለሆነ ሌላውን አካላቸውን በላሁት" አላቸው።
ዛሬም በክስርቶስ ስም ተጠርተን አካላቱ ሆነን ልንመላለስ በሚያስፈልግበት ጊዜ እኛ በእርግጥ ሆነናል ወይስ እንደሰዎቹ ከወገብ በላይ ታቦት ከወገብ በታች ጣኦት ነን።
ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል ልቡ ግን ከእኔ ርቋል ማቴ ፲፭፣፯ ቃሉን ሰምቶ የማያድርገው ፊቱን በመስታወት እንደሚያይ ሰው ይመስላል። ፊቱን ካየው በኋላ ዞር ሲል ፊቱን ይረሳዋልና።
@kinexebebe
አንድ ባሕታዊ ብዙ ሰዎች ሰብስበው እየሰበኩ ሳለ ጭራቅ ከጫካ ወደ ጉባኤው ይመጣል። ወደ ባሕታዊው ቀረብ ይልና "አባቴ እንግዲህ እንደምታውቁት የእኔ ሕልውና በሰው ሥጋና ደም ላይ የተመረኮዘ ስለሆነ እነኝህን ሰዎች ልበላቸው ነው" አላቸው።
ባሕታዊውም የሰው ሥጋ መብላትህን አውቃለሁ ግና እነዚህ ልጆቼን አትበላሸቸውም የክርስቶስ ናቸውና አትችልም ብለው ገዘቱት።
አቶዬም ግድ የሎትም አባቴ እኔ የክርስቶስ የሆኑትን አልበላም ንክችም አላረግም ሲል ቃል ገባላቸውና ተለያዩ።
ከሄዱበትም ሲመለሱ ጭራቁ ባሕታዊው ያስተማሩትን ሰው ሁሉ በልቶ ከንፈሮቻቸውንና ምላሳቸውን አስቀርቶ ጠበቃቸው ። በጉዳዩም በጣም የተቆጡት ባሕታዊ ምነው የክርስቶስ ናቸው እንዳትበላ አላልኩህም አሉት።
ጭራቁም በሰው ደም የለሰለሰውን ከንፈሮቹን በምላሱ እያበሰ "የክርስቶስ የሆኑትን አሁንም አልበላሁም" ብሎ በኩራት መለስላቸው።
ምን ማለትህ ነው ያስቀረኸው የለም እኮ ቢሉት "አባቴአባቴ የክርስቶስ የሆነው ምላሳቸው ነው። ክርስቶስ ያለው ከንፈሮቻቸውና ምላሳቸው ላይ ብቻ ስለሆነ ሌላውን አካላቸውን በላሁት" አላቸው።
ዛሬም በክስርቶስ ስም ተጠርተን አካላቱ ሆነን ልንመላለስ በሚያስፈልግበት ጊዜ እኛ በእርግጥ ሆነናል ወይስ እንደሰዎቹ ከወገብ በላይ ታቦት ከወገብ በታች ጣኦት ነን።
ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል ልቡ ግን ከእኔ ርቋል ማቴ ፲፭፣፯ ቃሉን ሰምቶ የማያድርገው ፊቱን በመስታወት እንደሚያይ ሰው ይመስላል። ፊቱን ካየው በኋላ ዞር ሲል ፊቱን ይረሳዋልና።
@kinexebebe