( አንቺ እናት ባትሆኝኝ )
የመኖሬ ትርጉም ቅኔዉ ሲጠፋብኝ፣
የህይወቴ መፅሐፍ ገፁ ሲምታታብኝ፣
የእኔነቴ ዋጋ ባዶ ሲሆንብኝ፣
የሀጢያት ሐረግ ሲነጠላጠልብኝ፣
ሙቸ መራመዴ ለእኔ ሲታዉቀኝ፣
ምን ይዉጠኝ ነበር አንቺ ባትኖሪልኝ?
አልቅሸ ሰነገርሺ አለዉህ ባትይኝ፣
የመዳንን መድህን ልዑል ባትዉልጂልኝ፣
በምልጃሺ ፀሎትሺ ቤቴ ባይሞላልኝ፣
በይቅር ባይነት ንሮ ባይቀናልኝ፣
ማን ያሰበኝ ነበር አንች ባታሰቢኝ።
ሀጥያት ተፀይፈሺ ፊት ያላዞርሽብኝ፣
ብርሀን ዉልደሺ ፀሀይ የሆንሺልኝ፣
ለዉለታሺ ገላጭ ምንም ቃላት የለኝ፣
አማላጇ እናቴ ሁሌም ክበሪልኝ፣
ድንግል እመቤቴ ከፍ ከፍ በይልኝ።
የችግሬ ደራሽ እመ እግዚአብሔር፣
ቃል ኪዳንሽ ይርዳኝ ካንቺ ጋራ ልኑር።
የአዳም ተስፋው ነሽ የሴት ቸርነቱ፣
ኪዳነ ምህረት ነሽ የኖህ ምልክቱ።
አዳም ደጅ የጠናሽ ሲገባ ንስሃ፣
ኖህም ድኖብሻል ከጥፋቱ ውሀ።
የአብርሃም ድንኳን ነሽ የሙሴ ፅላቱ፣
ማርያም አንቺ ነሽ የፈጣሪ እናቱ።
የእስራኤል መሰላል የሴም እጣ ክፍሉ፣
እመብርሃን ስሚኝ ልመናዬን ሁሉ።
የሰለሞን አክሊል የዳዊት ዝማሬ፣
ድንግል መሆንሽን ትመስክር ከንፈሬ።
ለተጠማ ውሻ የሚራራው ልብሽ፣
ለኔም ራርቶልኝ አስታርቂኝ ከልጅሽ።
የተራበ ጠግቦ የተጠማ ረክቶ፣
በስምሽ ይኖራል ሁሉም ተደስቶ።
በህይወት ጠብቂኝ ከመሞት ሰውረሽ
መከራን እንዳላይ በክንፎችሽ ጋርደሽ።
የምህረት ቃልኪዳን አምላክ የሰጠሽ፣
የአማኑኤል እናት መጽናኛዬ ነሽ።
ምንም ተስፋ የለኝ ባንቺ ነው እምነቴ፣
አማልጅኝ ከልጅሽ ክብረት እመቤቴ።
ሕይወቴ ጎስቁሎ በነፍሴ ብዝልም፣
በምልጃሽ ታምኜ በኪዳንሽ ልቁም።
ስምሽን እየጠራሁ እጽናናለሁኝ፣
ስሞት እንዳልጠፋ ድንግል ጠቢቂኝ።
ደሃ ምስኪን ሆኜ ለሰዎች ብታይም፣
ሞልቶ የተረፈ ጥሪት ባይኖረኝም፣
ስምሽን ብጠራው ምንም አይጨንቀኝም።
አንቺ ካለሽልኝ ኑሮዬ ሙሉ ነው፣
አፍሮ አያውቅምና የተማጽነሽ ሰው።
እኔን የሚረዳኝ በአገሩ ስቸገር፣
ዘመድ ጠያቂ የለኝ ፍጽም ካንቺ በቀር።
ከውጭም ስገባ ከቤትም ብወጣ፣
ነፍሴ እንድትቀደስ ከርኩስነት አምልጣ፣
ጠብቂኝ እመቤቴ ከዘመኑ ቁጣ።
ከአፌ አለይሽም አንቺን እጠራለሁ፣
ከአፌ አለይሽም ማርያም እልሻለሁ፣
አንቺ የወለድሽው ኢየሱስ አምላክ ነው፣
አንቺ የወለድሽው ክርስቶስ ንጉስ ነው።
የዳዊት ዘር ድንግል ንጉሱ ወዶሻል፣
ገነትን ስናጣ ተስፋችን ሆነሻል።
ክብርሽን የሚረሳ ልብ የለንም ከቶ፣
ልጅሽ አድኖናል ሞታችንን ሞቶ፣።
አሳረፈው ልቤን የእጆችሽ በረከት፣
የአማኑኤል እናት የታተምሽው ገነት።
በሰማይ በምድር ያንቺ ክብር ልዩ ነው፣
ለሰው ዘር መዳኛ ምክንያት የሆንሽው።
ክብርሽን ያወቀው ከመቅደስሽ ገብቶ፣
ተፈሲህ ይልሻል ለክብርሽ ተቀኝቶ።
ከሴቶች ለይቶ ማደሪያው ሲያረገሽ፣
የአዳም ዘር በሙሉ ቆሙ ለምስጋናሽ።
እናቱ ነሽና ዘመሩ ለስምሽ።
ፀጋን የተሞላሽ ደስተኛይቱ ሆይ ደስ ይበልሽ !
አዛኝቷ እመቤት አደለም ለሰው ልጆች ለውሻ የራራችው ኪዳነ ምህረት እናታችን የመረረውን ሕይወታችሁን ጣፋጭ ታድርግላችሁ ሲጨንቃቹ ሲጠባቹ ከልጇ ከወዳጇ ታማልዳችሁ!!!
@kinexebebe
የመኖሬ ትርጉም ቅኔዉ ሲጠፋብኝ፣
የህይወቴ መፅሐፍ ገፁ ሲምታታብኝ፣
የእኔነቴ ዋጋ ባዶ ሲሆንብኝ፣
የሀጢያት ሐረግ ሲነጠላጠልብኝ፣
ሙቸ መራመዴ ለእኔ ሲታዉቀኝ፣
ምን ይዉጠኝ ነበር አንቺ ባትኖሪልኝ?
አልቅሸ ሰነገርሺ አለዉህ ባትይኝ፣
የመዳንን መድህን ልዑል ባትዉልጂልኝ፣
በምልጃሺ ፀሎትሺ ቤቴ ባይሞላልኝ፣
በይቅር ባይነት ንሮ ባይቀናልኝ፣
ማን ያሰበኝ ነበር አንች ባታሰቢኝ።
ሀጥያት ተፀይፈሺ ፊት ያላዞርሽብኝ፣
ብርሀን ዉልደሺ ፀሀይ የሆንሺልኝ፣
ለዉለታሺ ገላጭ ምንም ቃላት የለኝ፣
አማላጇ እናቴ ሁሌም ክበሪልኝ፣
ድንግል እመቤቴ ከፍ ከፍ በይልኝ።
የችግሬ ደራሽ እመ እግዚአብሔር፣
ቃል ኪዳንሽ ይርዳኝ ካንቺ ጋራ ልኑር።
የአዳም ተስፋው ነሽ የሴት ቸርነቱ፣
ኪዳነ ምህረት ነሽ የኖህ ምልክቱ።
አዳም ደጅ የጠናሽ ሲገባ ንስሃ፣
ኖህም ድኖብሻል ከጥፋቱ ውሀ።
የአብርሃም ድንኳን ነሽ የሙሴ ፅላቱ፣
ማርያም አንቺ ነሽ የፈጣሪ እናቱ።
የእስራኤል መሰላል የሴም እጣ ክፍሉ፣
እመብርሃን ስሚኝ ልመናዬን ሁሉ።
የሰለሞን አክሊል የዳዊት ዝማሬ፣
ድንግል መሆንሽን ትመስክር ከንፈሬ።
ለተጠማ ውሻ የሚራራው ልብሽ፣
ለኔም ራርቶልኝ አስታርቂኝ ከልጅሽ።
የተራበ ጠግቦ የተጠማ ረክቶ፣
በስምሽ ይኖራል ሁሉም ተደስቶ።
በህይወት ጠብቂኝ ከመሞት ሰውረሽ
መከራን እንዳላይ በክንፎችሽ ጋርደሽ።
የምህረት ቃልኪዳን አምላክ የሰጠሽ፣
የአማኑኤል እናት መጽናኛዬ ነሽ።
ምንም ተስፋ የለኝ ባንቺ ነው እምነቴ፣
አማልጅኝ ከልጅሽ ክብረት እመቤቴ።
ሕይወቴ ጎስቁሎ በነፍሴ ብዝልም፣
በምልጃሽ ታምኜ በኪዳንሽ ልቁም።
ስምሽን እየጠራሁ እጽናናለሁኝ፣
ስሞት እንዳልጠፋ ድንግል ጠቢቂኝ።
ደሃ ምስኪን ሆኜ ለሰዎች ብታይም፣
ሞልቶ የተረፈ ጥሪት ባይኖረኝም፣
ስምሽን ብጠራው ምንም አይጨንቀኝም።
አንቺ ካለሽልኝ ኑሮዬ ሙሉ ነው፣
አፍሮ አያውቅምና የተማጽነሽ ሰው።
እኔን የሚረዳኝ በአገሩ ስቸገር፣
ዘመድ ጠያቂ የለኝ ፍጽም ካንቺ በቀር።
ከውጭም ስገባ ከቤትም ብወጣ፣
ነፍሴ እንድትቀደስ ከርኩስነት አምልጣ፣
ጠብቂኝ እመቤቴ ከዘመኑ ቁጣ።
ከአፌ አለይሽም አንቺን እጠራለሁ፣
ከአፌ አለይሽም ማርያም እልሻለሁ፣
አንቺ የወለድሽው ኢየሱስ አምላክ ነው፣
አንቺ የወለድሽው ክርስቶስ ንጉስ ነው።
የዳዊት ዘር ድንግል ንጉሱ ወዶሻል፣
ገነትን ስናጣ ተስፋችን ሆነሻል።
ክብርሽን የሚረሳ ልብ የለንም ከቶ፣
ልጅሽ አድኖናል ሞታችንን ሞቶ፣።
አሳረፈው ልቤን የእጆችሽ በረከት፣
የአማኑኤል እናት የታተምሽው ገነት።
በሰማይ በምድር ያንቺ ክብር ልዩ ነው፣
ለሰው ዘር መዳኛ ምክንያት የሆንሽው።
ክብርሽን ያወቀው ከመቅደስሽ ገብቶ፣
ተፈሲህ ይልሻል ለክብርሽ ተቀኝቶ።
ከሴቶች ለይቶ ማደሪያው ሲያረገሽ፣
የአዳም ዘር በሙሉ ቆሙ ለምስጋናሽ።
እናቱ ነሽና ዘመሩ ለስምሽ።
ፀጋን የተሞላሽ ደስተኛይቱ ሆይ ደስ ይበልሽ !
አዛኝቷ እመቤት አደለም ለሰው ልጆች ለውሻ የራራችው ኪዳነ ምህረት እናታችን የመረረውን ሕይወታችሁን ጣፋጭ ታድርግላችሁ ሲጨንቃቹ ሲጠባቹ ከልጇ ከወዳጇ ታማልዳችሁ!!!
@kinexebebe