#ልሳነ_ግዕዝ
#ክፍል_4
#ግሥና_የግሥ_ምንነት
#ግሥ
ግሥ ገሠሠ፣ ዳሠሠ ካለው ዐቢይ አንቀጽ ይወጣል ። ትርጉሙም ልዩ ልዩ ርባታዊ ቃላትን በየፈርጃቸው መግለጽን ማብራራትን ይመለከታል ። ግስ ከካዕብና ሳልስ በስተቀር በቀሩት #በ፭ቱ የኆኄ ቤቶች ይነሳል። ለምሳሌ ከፈለ፣ባረከ፣ ሤመ ፣ ክህለ፣ቆመ።
#አዕማደ_ግሥ
አዕማድ የዐምድ ብዙ ቁጥር ሲሆን በቁሙ ዋና ፣ ቀዋሚ፣ ተሸካሚ ... የሚል ትርጉም አለው ። አዕማድ የሚባሉት #፭ ናቸው ። እነሱም ፦ አድራጊ፣ተደራጊ፣አስደራጊ፣ተደራራጊ፣አደራራጊ ናቸው ።ለምሳሌ ፦ ቀተለ/ገደለ/ #አድራጊ ፣ ተቀትለ/ተገደለ/ #ተደራጊ ፣አቅተለ/አስገደለ/ #አስደራጊ ፣ ተቃተለ/ተጋደለ/ #ተደራራጊ ፣ አስተቃተለ /አጋደለ/ #አደራራጊ
#አርእስተ_ግሥ
አርእስተ ግሥን በተመለከተ የግሥ አርእስ ቀተለ ብቻ ነው የሚሉ አሉ። ልሎች ክፍሎች ደግሞ ቀተለ፣ ባረከ፣ዴገነ፣ኖለወ፣ ደንገፀ፣ማህረከ በማለት የግሥ አርእስት #7 ናቸው የሚሉ ክፍሎች አሉ።
#ፀዋትወ_ግሥ
ፀዋትወ የቋንቋ ሰፊ ሕግ ነው ። አንድ የቋንቋ ተማሪ ፀዋትወ ግሥን ለየ ማለት ስለ ቋንቋው በቂ ግንዛቤ አለው ብሎ ማለት ይቻላል። ፀዋትወ የተባሉት #4 ናቸው ። እነሱም ፦ ሀ እና አ አንድ፣ ወ ሁለት ፣የ ሶስት ፣ ሀ፡አ፡ወ፡የ የሌሉበት ማንኛውም ግሥ ሲባል በመነሻ ፣ በመሀልና በመጨረሻ ሊሆን ይችላል። ፀዋትወ ግሥን ለማወቅ በቅድሚያ አርእስተ ግሥ ፣ ሠራዊተ ግሥ መሠረት ናቸው። ፀዋትወ ግሥ ሲጠና መጀመሪያ የመመደብ ሥራ ነው የሚካሄደው ይህም ሲባል ይህ ግሥ የማን ቤት ነው ከየት ይመደባል የመሳሰለው ሁሉ።
#ገዳፍያነ_ዘመድ
ገዳፍያነ ዘመድ የኒባሉት ቤታቸውን ለቀው የኒሄዱ ናቸው ።እነዚህም "ወ" ና "የ" ናቸው ። ወ በመነሻ በመድረሻ በመሐል ቤቱን ለቆ ወደ ሌላ ቤት ይሄዳል ። ለምሳሌ ወለደ ብሎ ይወልድ ይላል ።
#ወሳክያነ_ባዕድ
እነዚህ ደሞ ከግሥ ያልነበረ ቀለምን የሚጨምሩ ናቸው ለምሳሌ ፦ ቆመ ብሎ ይቀውም ፣ ኤለ ብሎ የአይል ይላል።
#ሠጋርያን
ሠጋርያን ማለት መሸጋገሪያ ማለት ነው ። ሰጋርያን የተባሉ ቤታቸውን ለቀው ያለቤታቸው የሚገኙ በመሆናቸው ነው ። እነዚህም ወ ና የ ናቸው ።
#ውላጤ_ግዕዝ
ውላጤ ግዕዝ የተባሉ(ሀ፡አ፡ወ፡የ) በመነሻ በመድረሻ በመሀል በደጊመ ቃል የሚገኙባቸው ግሦች ናቸው ።እነዚህም በመነሻና በመድረሻ እንዲሁም በመሀከላቸው የተገኘባቸው ግሶች ራብዑን ግዕዝ ፡ ግዕዙን ራብዕ ሳድስ ያደርጋሉ።
#አላህላህያን
አላህላህያን የተባሉ ፫ ናቸው ። እነርሱም ሀ፣ አ፣ በ ናቸው ።እነዚህ ቀለማት በመካከል የተገኙበት ግሥ አይጠብቅም ።
#ወኀጥያን
ወኀጥያን የሚባሉት ፊደላት (አ፡ቀ፡ከ፡ገ) ናቸው ። ወኀጥያን በአንስቱ ቅርብ አነ፣አንተ፡አንቲ፡አንትሙ፡አንትን በረባ ጊዜ ቀለማትን ውጠውና አጥብቀው የሚያስቀሩ ናቸው
❤️ @lesangeez128❤️
💛 @lesangeez128💛
💚 @lesangeez128💚
#ክፍል_4
#ግሥና_የግሥ_ምንነት
#ግሥ
ግሥ ገሠሠ፣ ዳሠሠ ካለው ዐቢይ አንቀጽ ይወጣል ። ትርጉሙም ልዩ ልዩ ርባታዊ ቃላትን በየፈርጃቸው መግለጽን ማብራራትን ይመለከታል ። ግስ ከካዕብና ሳልስ በስተቀር በቀሩት #በ፭ቱ የኆኄ ቤቶች ይነሳል። ለምሳሌ ከፈለ፣ባረከ፣ ሤመ ፣ ክህለ፣ቆመ።
#አዕማደ_ግሥ
አዕማድ የዐምድ ብዙ ቁጥር ሲሆን በቁሙ ዋና ፣ ቀዋሚ፣ ተሸካሚ ... የሚል ትርጉም አለው ። አዕማድ የሚባሉት #፭ ናቸው ። እነሱም ፦ አድራጊ፣ተደራጊ፣አስደራጊ፣ተደራራጊ፣አደራራጊ ናቸው ።ለምሳሌ ፦ ቀተለ/ገደለ/ #አድራጊ ፣ ተቀትለ/ተገደለ/ #ተደራጊ ፣አቅተለ/አስገደለ/ #አስደራጊ ፣ ተቃተለ/ተጋደለ/ #ተደራራጊ ፣ አስተቃተለ /አጋደለ/ #አደራራጊ
#አርእስተ_ግሥ
አርእስተ ግሥን በተመለከተ የግሥ አርእስ ቀተለ ብቻ ነው የሚሉ አሉ። ልሎች ክፍሎች ደግሞ ቀተለ፣ ባረከ፣ዴገነ፣ኖለወ፣ ደንገፀ፣ማህረከ በማለት የግሥ አርእስት #7 ናቸው የሚሉ ክፍሎች አሉ።
#ፀዋትወ_ግሥ
ፀዋትወ የቋንቋ ሰፊ ሕግ ነው ። አንድ የቋንቋ ተማሪ ፀዋትወ ግሥን ለየ ማለት ስለ ቋንቋው በቂ ግንዛቤ አለው ብሎ ማለት ይቻላል። ፀዋትወ የተባሉት #4 ናቸው ። እነሱም ፦ ሀ እና አ አንድ፣ ወ ሁለት ፣የ ሶስት ፣ ሀ፡አ፡ወ፡የ የሌሉበት ማንኛውም ግሥ ሲባል በመነሻ ፣ በመሀልና በመጨረሻ ሊሆን ይችላል። ፀዋትወ ግሥን ለማወቅ በቅድሚያ አርእስተ ግሥ ፣ ሠራዊተ ግሥ መሠረት ናቸው። ፀዋትወ ግሥ ሲጠና መጀመሪያ የመመደብ ሥራ ነው የሚካሄደው ይህም ሲባል ይህ ግሥ የማን ቤት ነው ከየት ይመደባል የመሳሰለው ሁሉ።
#ገዳፍያነ_ዘመድ
ገዳፍያነ ዘመድ የኒባሉት ቤታቸውን ለቀው የኒሄዱ ናቸው ።እነዚህም "ወ" ና "የ" ናቸው ። ወ በመነሻ በመድረሻ በመሐል ቤቱን ለቆ ወደ ሌላ ቤት ይሄዳል ። ለምሳሌ ወለደ ብሎ ይወልድ ይላል ።
#ወሳክያነ_ባዕድ
እነዚህ ደሞ ከግሥ ያልነበረ ቀለምን የሚጨምሩ ናቸው ለምሳሌ ፦ ቆመ ብሎ ይቀውም ፣ ኤለ ብሎ የአይል ይላል።
#ሠጋርያን
ሠጋርያን ማለት መሸጋገሪያ ማለት ነው ። ሰጋርያን የተባሉ ቤታቸውን ለቀው ያለቤታቸው የሚገኙ በመሆናቸው ነው ። እነዚህም ወ ና የ ናቸው ።
#ውላጤ_ግዕዝ
ውላጤ ግዕዝ የተባሉ(ሀ፡አ፡ወ፡የ) በመነሻ በመድረሻ በመሀል በደጊመ ቃል የሚገኙባቸው ግሦች ናቸው ።እነዚህም በመነሻና በመድረሻ እንዲሁም በመሀከላቸው የተገኘባቸው ግሶች ራብዑን ግዕዝ ፡ ግዕዙን ራብዕ ሳድስ ያደርጋሉ።
#አላህላህያን
አላህላህያን የተባሉ ፫ ናቸው ። እነርሱም ሀ፣ አ፣ በ ናቸው ።እነዚህ ቀለማት በመካከል የተገኙበት ግሥ አይጠብቅም ።
#ወኀጥያን
ወኀጥያን የሚባሉት ፊደላት (አ፡ቀ፡ከ፡ገ) ናቸው ። ወኀጥያን በአንስቱ ቅርብ አነ፣አንተ፡አንቲ፡አንትሙ፡አንትን በረባ ጊዜ ቀለማትን ውጠውና አጥብቀው የሚያስቀሩ ናቸው
❤️ @lesangeez128❤️
💛 @lesangeez128💛
💚 @lesangeez128💚