@sebhhobekhlotu
@sebhhobekhlotu
@sebhhobekhlotu
"ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ" ማቴ 3፥16
ጌታችን እንደ አይሁድ ሕግ በአደባባይ የሚያስተምርበትና አገልግሎቱን የሚጀምርበት እድሜው ሲደርስ (በ30 ዓመቱ) ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ሊጠመቅ መጣ። የጽድቅ ፀሐዩ ክርስቶስ ለጥቂት ጊዜ እያበራ እና እየነደደ ሕዝቡን ደስ ያሰኝ ወደ ነበረው የአጥቢያው ኮከብ ዮሐንስ ዘንድ ሊጠመቅ በትሕትና መጣ።(ዮሐ 5፥35) ቅዱስ ዮሐንስ ግን እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል እንጂ አንተ ወደ እኔ ለመጠመቅ ትመጣ ዘንድ አይገባም? በጎ ሥጦታዎች ሁሉ ፍጹምም በረከት የብርሃናት አባት ከሆንከው ከአንተ ወደ እኛ ይወርዳሉ እንጂ እንዴት ከምድር ወደ ሰማይ ይወጣሉ? ይህስ አይሆንም ብሎ ይከለክለው ነበር። ጌታም ዮሐንስን "አጥምቀኝ እኮ ነው የምልህ?!" ሲል አልተቆጣውም። ይልቅስ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና "አሁንስ ፍቀድልኝ" ሲል ሊነገር በማይችል ትሕትና ለመነው። ይህን ታላቅ አምላካዊ ተማጽኖ ሰምቶ እንዴት የዮሐንስ ልብ ሊጸና ይችላል?! ያን ጊዜ ሎሌው ዮሐንስ ፈቀደና ጌታውን አጠመቀ።(ማቴ 3፥15)
ጌታችን ኢየሱስም ተጠምቆ ከውኃ ሲወጣ እነሆ ሰማያት ተከፈቱ። ወንጌላዊው "ሰማያት ተከፈቱ" እንጂ "ሰማያት ተከፈቱለት" ብሎ አልጻፈም። ምክንያቱም እርሱ እኛን ለመቤዠት ሰው ቢሆንና በባሕር መካከል ቆሞ ቢታይም በሰማይ ካለው መንበሩ ስላልጎደለ በሰማያትም ለሚኖረው ለእርሱ "ሰማያት ተከፈቱለት" አይባልም። ይልቅስ "ሰማያት ተከፈቱ" የሚለው ቃል ለእኛ በጌታ ጥምቀት ያገኘናቸውን ሰማያዊ በረከቶች የሚያሳይ ነው።
ጌታችን ተጠምቆ ወዲያው ከውኃው እንደ ወጣ ሰማያት ተከፈቱ ማለቱ፣ መድኃኒታችን በሰማይ ወዳለው መንግሥቱ እንድንገባ ተዘግቶ የነበረውን በር በጥምቀቱ እንደ ከፈተልን ለማስረዳት ነው። የማዳን ሥራውን ሲጀምር ተጠምቆ የሰማዩን ደጅ እንደከፈተልን፣ ማዳኑን ሲፈጽም ደግሞ ተሰቅሎ በመሞት የሲዖልን ደጆች ሰባብሮልናል።
ሌላው ከጥምቀቱ በኋላ ሰማያት መከፈታቸው፣ ተዘግቶ የቆየ ቤት በሩ በተከፈተ ጊዜ በውስጥ ያሉ ነገሮች እንዲታዩ በዘመነ ብሉይ ተሰውሮ የነበረው በሰማያት የሚኖረው የእግዚአብሔር የሦስትነቱ ምሥጢር አሁን ግልጥ ሆኖ መታየቱን ያመለክታል። ይኸውም ወልድ እግዚአብሔር በባሕረ ዮርዳኖስ ቆሞ በመታየቱ፣ አብ በደመና "የምወደው ልጄ ይህ ነው" ብሎ በመናገሩ እና መንፈስ ቅዱስ ደግሞ በርግብ አምሳል በመውረዱ ነው።
ሁላችንም እንደምናውቀው ሰማይ ለሚያምንም ሆነ ለሚጠራጠር ሁሉ የሚታይ ነገር ነው። ይሁን እንጂ ሁሉም የሚያዩት ሰማይ ግን "ሲከፈት" ለመመልከት መጠመቅ ያስፈልጋል። ልክ እንደዚህ ሰማይ በሚያምነውም በማያምነውም እጅ የሚገኝ እና ሁሉም የሚያየው (የሚያነበው) መጽሐፍ "መጽሐፍ ቅዱስ" ነው። ሆኖም መጽሐፍ ቅዱስን ሁሉም ያንብቡት እንጂ የምሥጢር በሩ እንዲከፈትና ውሳጣዊ መልእክቱን ለመረዳት ግን መጠመቅ ያስፈልጋል።
እንኳን ለበዓለ ጥምቀቱ በሰላም አደረሰን!!!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
@sebhhobekhlotu
@sebhhobekhlotu
@sebhhobekhlotu
@sebhhobekhlotu
@sebhhobekhlotu
"ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ" ማቴ 3፥16
ጌታችን እንደ አይሁድ ሕግ በአደባባይ የሚያስተምርበትና አገልግሎቱን የሚጀምርበት እድሜው ሲደርስ (በ30 ዓመቱ) ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ሊጠመቅ መጣ። የጽድቅ ፀሐዩ ክርስቶስ ለጥቂት ጊዜ እያበራ እና እየነደደ ሕዝቡን ደስ ያሰኝ ወደ ነበረው የአጥቢያው ኮከብ ዮሐንስ ዘንድ ሊጠመቅ በትሕትና መጣ።(ዮሐ 5፥35) ቅዱስ ዮሐንስ ግን እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል እንጂ አንተ ወደ እኔ ለመጠመቅ ትመጣ ዘንድ አይገባም? በጎ ሥጦታዎች ሁሉ ፍጹምም በረከት የብርሃናት አባት ከሆንከው ከአንተ ወደ እኛ ይወርዳሉ እንጂ እንዴት ከምድር ወደ ሰማይ ይወጣሉ? ይህስ አይሆንም ብሎ ይከለክለው ነበር። ጌታም ዮሐንስን "አጥምቀኝ እኮ ነው የምልህ?!" ሲል አልተቆጣውም። ይልቅስ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና "አሁንስ ፍቀድልኝ" ሲል ሊነገር በማይችል ትሕትና ለመነው። ይህን ታላቅ አምላካዊ ተማጽኖ ሰምቶ እንዴት የዮሐንስ ልብ ሊጸና ይችላል?! ያን ጊዜ ሎሌው ዮሐንስ ፈቀደና ጌታውን አጠመቀ።(ማቴ 3፥15)
ጌታችን ኢየሱስም ተጠምቆ ከውኃ ሲወጣ እነሆ ሰማያት ተከፈቱ። ወንጌላዊው "ሰማያት ተከፈቱ" እንጂ "ሰማያት ተከፈቱለት" ብሎ አልጻፈም። ምክንያቱም እርሱ እኛን ለመቤዠት ሰው ቢሆንና በባሕር መካከል ቆሞ ቢታይም በሰማይ ካለው መንበሩ ስላልጎደለ በሰማያትም ለሚኖረው ለእርሱ "ሰማያት ተከፈቱለት" አይባልም። ይልቅስ "ሰማያት ተከፈቱ" የሚለው ቃል ለእኛ በጌታ ጥምቀት ያገኘናቸውን ሰማያዊ በረከቶች የሚያሳይ ነው።
ጌታችን ተጠምቆ ወዲያው ከውኃው እንደ ወጣ ሰማያት ተከፈቱ ማለቱ፣ መድኃኒታችን በሰማይ ወዳለው መንግሥቱ እንድንገባ ተዘግቶ የነበረውን በር በጥምቀቱ እንደ ከፈተልን ለማስረዳት ነው። የማዳን ሥራውን ሲጀምር ተጠምቆ የሰማዩን ደጅ እንደከፈተልን፣ ማዳኑን ሲፈጽም ደግሞ ተሰቅሎ በመሞት የሲዖልን ደጆች ሰባብሮልናል።
ሌላው ከጥምቀቱ በኋላ ሰማያት መከፈታቸው፣ ተዘግቶ የቆየ ቤት በሩ በተከፈተ ጊዜ በውስጥ ያሉ ነገሮች እንዲታዩ በዘመነ ብሉይ ተሰውሮ የነበረው በሰማያት የሚኖረው የእግዚአብሔር የሦስትነቱ ምሥጢር አሁን ግልጥ ሆኖ መታየቱን ያመለክታል። ይኸውም ወልድ እግዚአብሔር በባሕረ ዮርዳኖስ ቆሞ በመታየቱ፣ አብ በደመና "የምወደው ልጄ ይህ ነው" ብሎ በመናገሩ እና መንፈስ ቅዱስ ደግሞ በርግብ አምሳል በመውረዱ ነው።
ሁላችንም እንደምናውቀው ሰማይ ለሚያምንም ሆነ ለሚጠራጠር ሁሉ የሚታይ ነገር ነው። ይሁን እንጂ ሁሉም የሚያዩት ሰማይ ግን "ሲከፈት" ለመመልከት መጠመቅ ያስፈልጋል። ልክ እንደዚህ ሰማይ በሚያምነውም በማያምነውም እጅ የሚገኝ እና ሁሉም የሚያየው (የሚያነበው) መጽሐፍ "መጽሐፍ ቅዱስ" ነው። ሆኖም መጽሐፍ ቅዱስን ሁሉም ያንብቡት እንጂ የምሥጢር በሩ እንዲከፈትና ውሳጣዊ መልእክቱን ለመረዳት ግን መጠመቅ ያስፈልጋል።
እንኳን ለበዓለ ጥምቀቱ በሰላም አደረሰን!!!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
@sebhhobekhlotu
@sebhhobekhlotu
@sebhhobekhlotu