ሰበብ ባይኖርስ?
➡️➡️➡️🗣️
አዎ! በሔድንበት ሁሉ ድክመታችን እንዳይታወቅ፣ ስንፍናችንን ላለማመን፣ መጥፎ ስሜታችንን አለባብሶ ለማለፍ የማናቀርበው ምክንያት፣ የማንደረድረው ሰበብ የለም። ሃላፊነት መውሰድ፣ ለእራስ ጥፋት ተጠያቂ መሆን የሚባለውን ነገር አብዝተን እንሸሸዋለን። ተጠያቂነትን ፍራቻ ሁሌም ምክንያት የምትደረድር ከሆነ የትም እንደማትደርስ እወቅ፤ ሰበብ እያበዛህ አንድ እርምጃ እደማትጓዝ ተገንዘብ። የስሜቱ ባሪያና በሰበብ አስባቡ የተገዛ ሰው አንድም የእራሴ የሚለው ታማኝ ማንነት የለውም፣ ሌላም በሰው ፊት ድፍረትና በእራስ መተማመን አይኖረውም። በሚያሳዝን ሁኔታ የሚያቀርበው ምክንያት እንኳን ሌሎችን ይቅርና እራሱንም የሚያሳምን አይደለም። ለገዛ እራሱ የሰጠው ግምትና የበታችነት ወደ ውድቀትና ተስፋ ቢስነት ያንደረድረዋል። እላይ ታች ብለህ እራስህን ማዳን በሚገባህ ጊዜ ምክንያት በመደርደር የተጠመድክ እንደሆነ ከእራስህ በላይ ለእራስህ ጠላት አይኖርህም።
አዎ! ጀግናዬ..! ሰበብ ባይኖርስ? ምክንያት መደርደር ባይቻልስ? ለጥፋቱም ሆነ ለልማቱ ሃላፊነት አለመውሰድ ባይቻልስ? የት በደረስክ ነበር? የህይወትህ መልክ፣ ገፅታው፣ ማንነቱ ምን ይመስል ነበር? አንተስ ምን አይነት ሰው ትሆን ነበር? ሰበብ በእርግጥም አለ ነገር ግን በመኖሩ የሚጨምርልን ነገር ከሌለ፣ ወደፊት ለመጓዝ ካላገዘን፣ እንድንጠነክር ካላደረገን፣ ካላበረታን ምንድነው ነጥቡ? ቆዳን ማልፋት ቢያደክምም በመጨረሻ ውጤት ያመጣል፤ ሰበብ ማብዛቱ፣ ምክንያት መደርደሩ፣ ሁኔታዎችን ማገለባበጡ ግን እራስን ከማታለል፣ የእራስን ዋጋ ከማሳነስ፣ ክብርን ዝቅ ከማድረግ ውጪ የሚያመጣልን ነገር የለም።
አዎ! ያሰብከውን ላለማድረግህ ቆጥረህ የማትጨርሳቸው በቂ ምክንያቶች ይኖሩሃል፤ ብታደርገውም ለማድረግህ እጅግ ብዙ በቂና ከዛ በላይ ምክንያቶች ይኖሩሃል። ለሁለቱም ሚዛን የሚደፉ ምክንያት ቢኖርህም ሚዛኑ ግን አንተ ነህ፤ እራስህ ላይ የምትወስነው፣ አዋጩን የምትመርጠው፣ ጠቃሚውን የምታደርገው አንተ ነህ። የምክንያት ለውጥ አድርግ፤ ላለማድረግ የምትደረድረውን ምክንያት ማድረግ በሚያስችሉህ ጠንካራ ምክንያቶች ተካቸው፤ በእነርሱ ለውጣቸው። ላለህበት ሁኔታ ያደረሱህ ነገሮች በተናጥል ሳይሆን በጋራ ለዚህ አብቅተውሃል። አዎንታዊ ምክንያቶችህም ብቻቸውን ሳይሆን ከቆራጥነትህ ጋር፣ ውሳኔህን በማካተት፣ በህይወት አላማህ በመደገፍ ተዓምራዊውን ህይወት ወዳንተ ያመጣሉ። ሰበቦችህን አሸጋሽግ፤ ምክንያቶችህን አቀያይር። አሉታዊዎቹን አስቀር፣ በአዎንታዊዎቹ ተመራ፤ ብርታቶችህን ምረጥ ጥንካሬህን አስቀድም፤ ያሰብከውን ትልቅ ነገር አድርገህ ተገኝ።
ውብ ምሽት ይሁንልን! 🌘🌒✨⭐️
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋
#SHARE እንዳይረሳ ቤተሰቦች! 🙏😍
በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
🔺🔻 SUBSCRIBE NOW
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @mikre_aimro 😊 💪
➡️➡️➡️🗣️
አዎ! በሔድንበት ሁሉ ድክመታችን እንዳይታወቅ፣ ስንፍናችንን ላለማመን፣ መጥፎ ስሜታችንን አለባብሶ ለማለፍ የማናቀርበው ምክንያት፣ የማንደረድረው ሰበብ የለም። ሃላፊነት መውሰድ፣ ለእራስ ጥፋት ተጠያቂ መሆን የሚባለውን ነገር አብዝተን እንሸሸዋለን። ተጠያቂነትን ፍራቻ ሁሌም ምክንያት የምትደረድር ከሆነ የትም እንደማትደርስ እወቅ፤ ሰበብ እያበዛህ አንድ እርምጃ እደማትጓዝ ተገንዘብ። የስሜቱ ባሪያና በሰበብ አስባቡ የተገዛ ሰው አንድም የእራሴ የሚለው ታማኝ ማንነት የለውም፣ ሌላም በሰው ፊት ድፍረትና በእራስ መተማመን አይኖረውም። በሚያሳዝን ሁኔታ የሚያቀርበው ምክንያት እንኳን ሌሎችን ይቅርና እራሱንም የሚያሳምን አይደለም። ለገዛ እራሱ የሰጠው ግምትና የበታችነት ወደ ውድቀትና ተስፋ ቢስነት ያንደረድረዋል። እላይ ታች ብለህ እራስህን ማዳን በሚገባህ ጊዜ ምክንያት በመደርደር የተጠመድክ እንደሆነ ከእራስህ በላይ ለእራስህ ጠላት አይኖርህም።
አዎ! ጀግናዬ..! ሰበብ ባይኖርስ? ምክንያት መደርደር ባይቻልስ? ለጥፋቱም ሆነ ለልማቱ ሃላፊነት አለመውሰድ ባይቻልስ? የት በደረስክ ነበር? የህይወትህ መልክ፣ ገፅታው፣ ማንነቱ ምን ይመስል ነበር? አንተስ ምን አይነት ሰው ትሆን ነበር? ሰበብ በእርግጥም አለ ነገር ግን በመኖሩ የሚጨምርልን ነገር ከሌለ፣ ወደፊት ለመጓዝ ካላገዘን፣ እንድንጠነክር ካላደረገን፣ ካላበረታን ምንድነው ነጥቡ? ቆዳን ማልፋት ቢያደክምም በመጨረሻ ውጤት ያመጣል፤ ሰበብ ማብዛቱ፣ ምክንያት መደርደሩ፣ ሁኔታዎችን ማገለባበጡ ግን እራስን ከማታለል፣ የእራስን ዋጋ ከማሳነስ፣ ክብርን ዝቅ ከማድረግ ውጪ የሚያመጣልን ነገር የለም።
አዎ! ያሰብከውን ላለማድረግህ ቆጥረህ የማትጨርሳቸው በቂ ምክንያቶች ይኖሩሃል፤ ብታደርገውም ለማድረግህ እጅግ ብዙ በቂና ከዛ በላይ ምክንያቶች ይኖሩሃል። ለሁለቱም ሚዛን የሚደፉ ምክንያት ቢኖርህም ሚዛኑ ግን አንተ ነህ፤ እራስህ ላይ የምትወስነው፣ አዋጩን የምትመርጠው፣ ጠቃሚውን የምታደርገው አንተ ነህ። የምክንያት ለውጥ አድርግ፤ ላለማድረግ የምትደረድረውን ምክንያት ማድረግ በሚያስችሉህ ጠንካራ ምክንያቶች ተካቸው፤ በእነርሱ ለውጣቸው። ላለህበት ሁኔታ ያደረሱህ ነገሮች በተናጥል ሳይሆን በጋራ ለዚህ አብቅተውሃል። አዎንታዊ ምክንያቶችህም ብቻቸውን ሳይሆን ከቆራጥነትህ ጋር፣ ውሳኔህን በማካተት፣ በህይወት አላማህ በመደገፍ ተዓምራዊውን ህይወት ወዳንተ ያመጣሉ። ሰበቦችህን አሸጋሽግ፤ ምክንያቶችህን አቀያይር። አሉታዊዎቹን አስቀር፣ በአዎንታዊዎቹ ተመራ፤ ብርታቶችህን ምረጥ ጥንካሬህን አስቀድም፤ ያሰብከውን ትልቅ ነገር አድርገህ ተገኝ።
ውብ ምሽት ይሁንልን! 🌘🌒✨⭐️
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋
#SHARE እንዳይረሳ ቤተሰቦች! 🙏😍
በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
🔺🔻 SUBSCRIBE NOW
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @mikre_aimro 😊 💪