ዶናልድ ትራምፕ የ2020 ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እንዲዘገይ ጥሪ አቀረቡ
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በህዳር 2020 የሚካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እንዲዘገይ በትዊተር ገጻቸው ጥሪ ማቅረባቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ይህንን ያሉት በኢሜልና በፖስታ ሊደረግ የታሰበው የሕዳሩ ምርጫ እንዳይጭበረበር ነው ብለዋል፡፡
በቀጣይ ሕዳር የሚካሄደው ምርጫ የማይዘገይ ከሆነ በታሪክ ከፍተኛ የሆነ የድምጽ ማጭበርበር ሊከሰት እንደሚችል ግምት አስቀምጠዋል፡፡ የተሳሳተ ውጤት ከሚመጣ ምርጫው ቢዘገይ የሚል ሃሳብ ያቀረቡት ትራምፕ የሰው ልጆች የጤና ስጋት ውስጥ በማይገቡበትና አስተማማኝ በሆነ መልኩ ድምጽ መስጠት እስከሚችሉ ድረስ ምርጫው እንዲዘገይ ሀሳብ አቅርበዋል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በህዳር 2020 የሚካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እንዲዘገይ በትዊተር ገጻቸው ጥሪ ማቅረባቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ይህንን ያሉት በኢሜልና በፖስታ ሊደረግ የታሰበው የሕዳሩ ምርጫ እንዳይጭበረበር ነው ብለዋል፡፡
በቀጣይ ሕዳር የሚካሄደው ምርጫ የማይዘገይ ከሆነ በታሪክ ከፍተኛ የሆነ የድምጽ ማጭበርበር ሊከሰት እንደሚችል ግምት አስቀምጠዋል፡፡ የተሳሳተ ውጤት ከሚመጣ ምርጫው ቢዘገይ የሚል ሃሳብ ያቀረቡት ትራምፕ የሰው ልጆች የጤና ስጋት ውስጥ በማይገቡበትና አስተማማኝ በሆነ መልኩ ድምጽ መስጠት እስከሚችሉ ድረስ ምርጫው እንዲዘገይ ሀሳብ አቅርበዋል።