#ከሙሒቦቹ_አንደበት ♥
የሀ~ያእ~ዐይን~ሷድ (كهيعص) ትርጉም!
ማሊክ ቢን ዲናር (ረዲየላሁ ዓንሁ) እንዲህ ይላሉ፦ አንድ ጊዜ ወደ አላህ ቤት ሐረም ለሐጅ አቀናሁ። መንገድ ላይ ሳለሁ አንድ ሰው ያለ ምንም ስንቅ ሲጓዝ አየሁትና ሰላምታ ሰጠሁት እርሱም መለሰልኝ። ቀጥዬ ከየት ነው የምትመጣው? ብዬ ጠየቅኩት
"ከእርሱ" ብሎ መለሰልኝ
እንዲህ አልኩት፦ ወደ የት መሄድ ፈልገህ ነው?
"ወደ ርሱ ቤት" ብሎ መለሰልኝ
እንዲህ አልኩት፦ የታለ ስንቅህና ጓዝህ?
እንዲህ አለ፦ እርሱ ዘንድ አለኝ!
ጥያቄው ቀጠለ
— ይህ መንገድ ያለ ምግብና ያለመጠጥ አይዘለቅም ምን ይዘሀል?
— አዎን ይዣለሁ። ከሀገሬ ስወጣ አምስት ፊደሎችን ተሰንቄነው የወጣሁት።
— ምንድናቸው እነርሱ?
— የአላህ ቃላት ሲኾኑ በሱረቱል መርየም መጀመሪያ ላይ የሚገኙትን ፊደላት ጠቀሰለት (كهيعص)
— ምን ማለት ነው?
– "ካፍ" ማለት ካፊ (በቂ) ነው፣ "ሀእ" ደግሞ ሀዲ (ቅናቻ መንገድ የሚመራ) ማለት ነው፣ "ያእ" ደግሞ መእዊያ ማለት ሲኾን ስንቅን፣ ምግብን የመሳሰሉ መጠቃቀሚያዎችን የሚያስተናብር ነው። "ዓይን" ደግሞ ዓሊም (ዐዋቂ) ነው ማለት ነው። "ሷድ" ሳድቅ (እውነተኛ) ማለት ነው።
አላህ ቢቂዬ ነው ብሎ በርሱ የተመራ ከእርሱም ስንቅን ከርሱ የጠበቀ እርሱ ደግሞ ዐዋቂና እውነተኛ መሆኑን የተረዳ አይጠፋም አይፈራም። ለጉዞውም ስንቅ ማጣትን አይሰጋም።
ማሊክ እንዲህ አለ፦ ይህን ቃላት ስሰማ ቀሚሴን አውልቄ ላለብሰው ስል እምቢ አለኝና እንዲህ አለ፦ ሸይኽ ሆይ! ቅዝቃዜው ካንተ ቀሚስ ለእኔ መልካም ነው። “ ይህች ዓለም (ዱንያ) ሐላሏ (የተፈቀደ ነገሯ) ሒሳብ ነው። ሐራሟ (የተከለከለ ነገሯ) ደግሞ ቅጣት ነው።”
ለሊቱ ሲጨልም ራሱን ወደ ሰማይ ቀና አድርጎ እንዲህ ይላል፦
አንተን ብንታዘዝ የማትጠቀመው ብናምጽህ የማትጎዳው ለአንተ የማትጠቀምበትን ሥጠኝ የማትጎዳበትን ምሕረታህን ለግሰኝ።
ሰዎች በሐጅ ለይ "ለበይክ" ሲሉ ይህ ሰው አይለም ነበር። ለምን "ለበይክ" አትልም?
እንዲህ አለ፦ ሸይኽ ሆይ! አላህ ጥሪህንም አልተቀበልኩም ንግግርህን አልሰማም አልመለከትህም። (ላ ለበይክ ወላ ሳዕደይክ ...) እንዳይለኝ ፈርቼ!
ከዚያም ከእኔ ዕይታ ተሰወረብኝ። ሚና ላይ እንዲህ ብሎ በግጥም ስንኝ ሲያለቅስ ግን አየሁት።
إﻥ ﺍﻟﺤﺒﻴﺐ ﺍﻟﺬﻱ ﻳﺮﺿﻴﻪ ﺳﻔﻚ ﺩﻣﻲ -- ﺩﻣﻲ ﺣﻼﻝ ﻟﻪ ﻓﻲ ﺍﻟﺤﻞ ﻭﺍﻟﺤﺮﻡ""
ﻭﺍلله ﻟﻮ ﻋﻠﻤﺖ ﺭﻭﺣﻲ ﺑﻤﻦ ﻋﺸﻘﺖ -- ﻗﺎﻣﺖ ﻋﻠﻰ ﺭأﺳﻬﺎ ﻓﻀﻼ ﻋﻠﻰ ﺍﻟﻘﺪﻡ""
ﻳﺎ ﻻﺋﻤﻲ ﻻ ﺗﻠﻤﻨﻲ ﻓﻲ ﻫﻮﺍﻩ ﻓﻠﻮ -- ﻋﺎﻳﻨﺖ ﻣﻨﻪ ﺍﻟﺬﻱ ﻋﺎﻳﻨﺖ ﻟﻢ ﺗﻠﻢ""
ﻳﻄﻮﻑ باﻟﺒﻴﺖ ﻗﻮﻡ ﺑﺠﺎﺭﺣﺔ --ولو بالله ﻃﺎﻓﻮﺍ ﻷﻏﻨﺎﻫﻢ ﻋﻦ ﺍﻟﺤﺮﻡ""
ﻟﻠﻨﺎﺱ ﺣﺞ ﻭﻟﻲ ﺣﺞ ﺇﻟﻰ ﺳﻜﻨﻲ -- ﺗﻬﺪى الأﺿﺎﺣﻲ ﻭأﻫﺪﻱ ﻣﻬﺠﺘﻲ ﻭﺩﻣﻲ
ከዚያም እንዲህ አለ
ጌታዬ ሆይ! ሰዎች በዕርድና በሰጠሀቸው ነገር ወደአንተ ለመሄድና ተቃረቡህ። እኔ በነፍሴ እንጂ ወደ አንተ የምቃረብበት ነገር የለኝምና ተቀበለኝ። ከዚያም ወደ ሰማይ እየተመለከተና በብርቱ ሆኔታ እያለቀሰ ወደ አላህ ዘንድ በሞት ተሻገረ። አላህ ይዘንለት።
ይህን ለሊት ይህን ጉዳይ እያሰብኩ በሕልሜ አገኘሁትና ጠየቅኩት ይላሉ ታሪኩን የሚዘግቡልን ታላቅ ሰው።
አላህ በአንተ ላይ ምን አድርጎ ነው?
እንዲህ አለኝ፦ በበድር ዕለት የተሰዉት ላይ እንዳደረገው። ለእኔ ግን ከዚያም በላይ ጨመረልኝ።
ምንድነው ጭማሬው? ሰል ጠየቅኩት
እንዲህ አለ፦ እነርሱ የተገደሉት በከሐዲያን ሰይፍ ሲኾን እኔ ግን የተገደልኩት በጀባር መሐባ ነው።
(ከ ረውድ አል ሪያሒይን መጽሐፍ)
ኢማሙ ሻፍዒይ (ራዐ)
አላህ ሙሒቦች ከቀመሱት ያቅምሰና ♥
✍best kerim
የሀ~ያእ~ዐይን~ሷድ (كهيعص) ትርጉም!
ማሊክ ቢን ዲናር (ረዲየላሁ ዓንሁ) እንዲህ ይላሉ፦ አንድ ጊዜ ወደ አላህ ቤት ሐረም ለሐጅ አቀናሁ። መንገድ ላይ ሳለሁ አንድ ሰው ያለ ምንም ስንቅ ሲጓዝ አየሁትና ሰላምታ ሰጠሁት እርሱም መለሰልኝ። ቀጥዬ ከየት ነው የምትመጣው? ብዬ ጠየቅኩት
"ከእርሱ" ብሎ መለሰልኝ
እንዲህ አልኩት፦ ወደ የት መሄድ ፈልገህ ነው?
"ወደ ርሱ ቤት" ብሎ መለሰልኝ
እንዲህ አልኩት፦ የታለ ስንቅህና ጓዝህ?
እንዲህ አለ፦ እርሱ ዘንድ አለኝ!
ጥያቄው ቀጠለ
— ይህ መንገድ ያለ ምግብና ያለመጠጥ አይዘለቅም ምን ይዘሀል?
— አዎን ይዣለሁ። ከሀገሬ ስወጣ አምስት ፊደሎችን ተሰንቄነው የወጣሁት።
— ምንድናቸው እነርሱ?
— የአላህ ቃላት ሲኾኑ በሱረቱል መርየም መጀመሪያ ላይ የሚገኙትን ፊደላት ጠቀሰለት (كهيعص)
— ምን ማለት ነው?
– "ካፍ" ማለት ካፊ (በቂ) ነው፣ "ሀእ" ደግሞ ሀዲ (ቅናቻ መንገድ የሚመራ) ማለት ነው፣ "ያእ" ደግሞ መእዊያ ማለት ሲኾን ስንቅን፣ ምግብን የመሳሰሉ መጠቃቀሚያዎችን የሚያስተናብር ነው። "ዓይን" ደግሞ ዓሊም (ዐዋቂ) ነው ማለት ነው። "ሷድ" ሳድቅ (እውነተኛ) ማለት ነው።
አላህ ቢቂዬ ነው ብሎ በርሱ የተመራ ከእርሱም ስንቅን ከርሱ የጠበቀ እርሱ ደግሞ ዐዋቂና እውነተኛ መሆኑን የተረዳ አይጠፋም አይፈራም። ለጉዞውም ስንቅ ማጣትን አይሰጋም።
ማሊክ እንዲህ አለ፦ ይህን ቃላት ስሰማ ቀሚሴን አውልቄ ላለብሰው ስል እምቢ አለኝና እንዲህ አለ፦ ሸይኽ ሆይ! ቅዝቃዜው ካንተ ቀሚስ ለእኔ መልካም ነው። “ ይህች ዓለም (ዱንያ) ሐላሏ (የተፈቀደ ነገሯ) ሒሳብ ነው። ሐራሟ (የተከለከለ ነገሯ) ደግሞ ቅጣት ነው።”
ለሊቱ ሲጨልም ራሱን ወደ ሰማይ ቀና አድርጎ እንዲህ ይላል፦
አንተን ብንታዘዝ የማትጠቀመው ብናምጽህ የማትጎዳው ለአንተ የማትጠቀምበትን ሥጠኝ የማትጎዳበትን ምሕረታህን ለግሰኝ።
ሰዎች በሐጅ ለይ "ለበይክ" ሲሉ ይህ ሰው አይለም ነበር። ለምን "ለበይክ" አትልም?
እንዲህ አለ፦ ሸይኽ ሆይ! አላህ ጥሪህንም አልተቀበልኩም ንግግርህን አልሰማም አልመለከትህም። (ላ ለበይክ ወላ ሳዕደይክ ...) እንዳይለኝ ፈርቼ!
ከዚያም ከእኔ ዕይታ ተሰወረብኝ። ሚና ላይ እንዲህ ብሎ በግጥም ስንኝ ሲያለቅስ ግን አየሁት።
إﻥ ﺍﻟﺤﺒﻴﺐ ﺍﻟﺬﻱ ﻳﺮﺿﻴﻪ ﺳﻔﻚ ﺩﻣﻲ -- ﺩﻣﻲ ﺣﻼﻝ ﻟﻪ ﻓﻲ ﺍﻟﺤﻞ ﻭﺍﻟﺤﺮﻡ""
ﻭﺍلله ﻟﻮ ﻋﻠﻤﺖ ﺭﻭﺣﻲ ﺑﻤﻦ ﻋﺸﻘﺖ -- ﻗﺎﻣﺖ ﻋﻠﻰ ﺭأﺳﻬﺎ ﻓﻀﻼ ﻋﻠﻰ ﺍﻟﻘﺪﻡ""
ﻳﺎ ﻻﺋﻤﻲ ﻻ ﺗﻠﻤﻨﻲ ﻓﻲ ﻫﻮﺍﻩ ﻓﻠﻮ -- ﻋﺎﻳﻨﺖ ﻣﻨﻪ ﺍﻟﺬﻱ ﻋﺎﻳﻨﺖ ﻟﻢ ﺗﻠﻢ""
ﻳﻄﻮﻑ باﻟﺒﻴﺖ ﻗﻮﻡ ﺑﺠﺎﺭﺣﺔ --ولو بالله ﻃﺎﻓﻮﺍ ﻷﻏﻨﺎﻫﻢ ﻋﻦ ﺍﻟﺤﺮﻡ""
ﻟﻠﻨﺎﺱ ﺣﺞ ﻭﻟﻲ ﺣﺞ ﺇﻟﻰ ﺳﻜﻨﻲ -- ﺗﻬﺪى الأﺿﺎﺣﻲ ﻭأﻫﺪﻱ ﻣﻬﺠﺘﻲ ﻭﺩﻣﻲ
ከዚያም እንዲህ አለ
ጌታዬ ሆይ! ሰዎች በዕርድና በሰጠሀቸው ነገር ወደአንተ ለመሄድና ተቃረቡህ። እኔ በነፍሴ እንጂ ወደ አንተ የምቃረብበት ነገር የለኝምና ተቀበለኝ። ከዚያም ወደ ሰማይ እየተመለከተና በብርቱ ሆኔታ እያለቀሰ ወደ አላህ ዘንድ በሞት ተሻገረ። አላህ ይዘንለት።
ይህን ለሊት ይህን ጉዳይ እያሰብኩ በሕልሜ አገኘሁትና ጠየቅኩት ይላሉ ታሪኩን የሚዘግቡልን ታላቅ ሰው።
አላህ በአንተ ላይ ምን አድርጎ ነው?
እንዲህ አለኝ፦ በበድር ዕለት የተሰዉት ላይ እንዳደረገው። ለእኔ ግን ከዚያም በላይ ጨመረልኝ።
ምንድነው ጭማሬው? ሰል ጠየቅኩት
እንዲህ አለ፦ እነርሱ የተገደሉት በከሐዲያን ሰይፍ ሲኾን እኔ ግን የተገደልኩት በጀባር መሐባ ነው።
(ከ ረውድ አል ሪያሒይን መጽሐፍ)
ኢማሙ ሻፍዒይ (ራዐ)
አላህ ሙሒቦች ከቀመሱት ያቅምሰና ♥
✍best kerim