بسم الله الرحمن الرحيم
الحمد لله والصلاة والسلام على من لا نبي بعده، وبعد :
حكم التوسل بالاولياء والصالحين
በወሊዮች እና በሷሊሆች(በደጋግ) ሰዎች ተወሱል የማድረግ ፍርዱ
ይህን ርዕስ ለመንሳት ያስገደደኝ ነገር ሰሞኑን አህባሾች ና ሱፍዮች ዘንድ ከየመን ሐቢብ ዑመር የሚባል ግለሰብ መምጣቱን አስከትሎ በዚህ ግለሰብ ላይ ድንበር ሲያልፉበት በመመልከቴ ሲሆን እነርሱ እንግዲህ ይህን ግለሰብ ወልይ ነው ብለው ስለሚገምቱ ነው።በዚህ ግለሰብ ላይ ድንበር ካለፉበት ነገሮች መሀከል ተወሱል የሚባለውን ታላቅ ዒባዳ አሳልፈው ሲሰጡና ሌሎችንም ሙስሊሞች ወደዚህ ተግባር ጥሪ ሲያረጉ ነበር።
ይህን አስመልክቶ አንዳንድ የሙስሊሙን ማህበረሰብ እያታለሉ ይገኛሉ። እስኪ ይህን ርዕስ በሸሪዐ ሚዛን ጠለቅ ብለን እንመልከተው።
በመጀመሪያ ተወሱል(التوسل) ማለት ምን ማለት ነው?
التوسل: هو التقرب إلى الشيئ والتوصل إليه
ተወሱል ማለት: ወደ ማነኛውም ነገር መቃረብ ና መዳረስ ነው።
التوسل قسمان
ተወሱል በሁለት ይካፈላል
القسم الأول: توسل مشروع.وهو أنواع
የመጀመሪያው የተወሱል ዐይነት: የተፈቀደ ተወሱል ሲሆን እርሱም ብዙ ዐይነት ነው።
النوع الأول: التوسل إلى الله تعلى بأسمائه وصفاته
አንደኛው: በአሏህ ስሞች ና ባህሪያቶች ተወሱል ማድረግ ነው።
አሏህ እንዲህ ይላል: { ለአሏህም መልካም ስሞች አሉት፣በእርሷም ጥሩት} አል አዕራፍ 180
በዚህ የቁርዐን አንቀፅ መሠረት የአሏህን ስሞች ና ባህሪዎችን በመጥቀስ ወደ አሏህ ማድረግ እንደሚቻል ይጦቅመናል።
النوع الثاني: التوسل إلى الله تعلى بالإيمان والأعمال الصالحة التى قام بها المتوسل
ሁለተኛው: ተወሱል የሚያረገው ግለሰብ በኢማኑ እና በሰራቸው መልካም ስራዎች ወደ አሏህ መቃረብ ነው።
አሏህ እንዲህ ይላል: { ጌታችን ሆይ: እኛ በጌታችሁ እመኑ በማለት ወደ እምነት የሚጠራን ጠሪ ሰማን:አመንም፣ጌታችን ሆን ሀጢያቶቻችንን ለኛ ማር፣ክፉ ስራዎቻችንንም ከኛ አብስ፣ከመልካሞችም ሰዎች ጋር ግደለን} አል ዒምራን 193
ቡኻሪ ና ሙስሊም ከኢብኑ ዑመር ከዘገቡት ሀዲስም እነዚያ ሶስት ሰዎች በጉዞ ላይ ሳሉ መሽቶባቸው ለማረፍ ወደ ዋሻ ገብተው ቋጥኝ ተንከባሎ መውጫ መንገድ ዘግቶባቸው ሶስቱም ለአሏህ ብለው የሰሯቸውን መልካም ስራ በመጥቀስ ወደ አሏህ ተወሱል በማድረግ ከነበሩበት ጭንቀት ወጥተው ጉዟቸውን ቀጥለዋል
ይህ የሚያመለክተን በመልካም ስራዎች ተወሱል ማድረግ እንደሚቻል ነው።
النوع الثالث:التوسل إلى الله تعلى بتوحيده
ሶስተኛው: በተውሂድ (ከአሏህ በስተቀር በእውነት የሚገዙት አምላክ)የሌለ መሆኑን በመመስከር ወደ አሏህ ተወሱል ማድረግ ነው።
አሏህ የነቢዩሏሂ ዩኑስን ዐሳ ነባሪ ሆድ ውስጥ ሆነው ተወሱል ሲያረጉ እንዲህ ይላል:{ በጨለማዎችም ውስጥ ኾኖ ከአንተ በስተቀር በእውነት የሚገዙት አምላክ የለም፣ጥራት ይገባህ፣እኔ በእርግጥ ከበዳዮች ነበርኩ በማለት ተጣራ) አል አንቢያ 87
ከዚህ ምንረዳው አንድ ሰው አሏህን በተውሂድ ነጥሎ መገዛቱን እየነገረ ችግሮቹ እንዲቀረፉለት ወደ አሏህ ተወሱል ማድረግ ይችላል።
النوع الرابع:التوسل إلى الله تعلى بإظهار الضعف والحاجة والإفتقار إلى الله
አራተኛው: ድክመትህን፣ወደ አሏህ ፈላጊነትህን፣እንደዚሁም ወደ አሏህ ከጃይ መሆንህን እየገለፅክ ወደ አሏህ ተወሱል ማድረግ ነው።
አሏህ የነቢዩሏሂ አዩብ ዐለይሂ ሰላም ታሪክ ሲያወሳ እንዲህ ይለናል:{ አዩብንም ጌታውን ሲል በተጣራ ጊዜ አስታውስ} አንቢያ 83
ነቢዩሏሂ አዩብ ዐለይሂሰላም ችግራቸውን በመጥቀስ ወደ አሏህ ተወሱል አርገዋል።
النوع الخامس: التوسل إلى الله تعلى بدعاء الصالحين الأحياء
አምስተኛው: በሂይወት ባሉ ደጋግ የአሏህ ባሮች በዱዐቸው ተወሱል ማድረግ ነው።
ልክ ሰሀቦች ነቢዩ ዘንድ እየመጡ ችግራቸው እየነገሯቸው ነቢዩም ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ችግራቸውን አሏህ እንዲያስወግድላቸው ዱዐ ያረጉ ነበር።ከነቢዩም ህልፈት ቡሀላ ሰሀቦች ወደ ነቢዩ ቀብር ሳይሆን የሄዱት ወደ ታላቁ ሰሀባ ዐባስ ረዲየሏሁዐንሁ ጋር በመምጣት አሏህን እንዲለምኑላቸው ይጠይቋቸው ነበር።
እነዚህ እንግዲህ ከሚፈቀደው የተወሱል ዐይነት የሚመደቡ ሲሆን በቀጣይ የሚከለከለውን የተወሱል ዐይነት በዝርዝር እናያለን
ወሏሁ አዕለም
الحمد لله والصلاة والسلام على من لا نبي بعده، وبعد :
حكم التوسل بالاولياء والصالحين
በወሊዮች እና በሷሊሆች(በደጋግ) ሰዎች ተወሱል የማድረግ ፍርዱ
ይህን ርዕስ ለመንሳት ያስገደደኝ ነገር ሰሞኑን አህባሾች ና ሱፍዮች ዘንድ ከየመን ሐቢብ ዑመር የሚባል ግለሰብ መምጣቱን አስከትሎ በዚህ ግለሰብ ላይ ድንበር ሲያልፉበት በመመልከቴ ሲሆን እነርሱ እንግዲህ ይህን ግለሰብ ወልይ ነው ብለው ስለሚገምቱ ነው።በዚህ ግለሰብ ላይ ድንበር ካለፉበት ነገሮች መሀከል ተወሱል የሚባለውን ታላቅ ዒባዳ አሳልፈው ሲሰጡና ሌሎችንም ሙስሊሞች ወደዚህ ተግባር ጥሪ ሲያረጉ ነበር።
ይህን አስመልክቶ አንዳንድ የሙስሊሙን ማህበረሰብ እያታለሉ ይገኛሉ። እስኪ ይህን ርዕስ በሸሪዐ ሚዛን ጠለቅ ብለን እንመልከተው።
በመጀመሪያ ተወሱል(التوسل) ማለት ምን ማለት ነው?
التوسل: هو التقرب إلى الشيئ والتوصل إليه
ተወሱል ማለት: ወደ ማነኛውም ነገር መቃረብ ና መዳረስ ነው።
التوسل قسمان
ተወሱል በሁለት ይካፈላል
القسم الأول: توسل مشروع.وهو أنواع
የመጀመሪያው የተወሱል ዐይነት: የተፈቀደ ተወሱል ሲሆን እርሱም ብዙ ዐይነት ነው።
النوع الأول: التوسل إلى الله تعلى بأسمائه وصفاته
አንደኛው: በአሏህ ስሞች ና ባህሪያቶች ተወሱል ማድረግ ነው።
አሏህ እንዲህ ይላል: { ለአሏህም መልካም ስሞች አሉት፣በእርሷም ጥሩት} አል አዕራፍ 180
በዚህ የቁርዐን አንቀፅ መሠረት የአሏህን ስሞች ና ባህሪዎችን በመጥቀስ ወደ አሏህ ማድረግ እንደሚቻል ይጦቅመናል።
النوع الثاني: التوسل إلى الله تعلى بالإيمان والأعمال الصالحة التى قام بها المتوسل
ሁለተኛው: ተወሱል የሚያረገው ግለሰብ በኢማኑ እና በሰራቸው መልካም ስራዎች ወደ አሏህ መቃረብ ነው።
አሏህ እንዲህ ይላል: { ጌታችን ሆይ: እኛ በጌታችሁ እመኑ በማለት ወደ እምነት የሚጠራን ጠሪ ሰማን:አመንም፣ጌታችን ሆን ሀጢያቶቻችንን ለኛ ማር፣ክፉ ስራዎቻችንንም ከኛ አብስ፣ከመልካሞችም ሰዎች ጋር ግደለን} አል ዒምራን 193
ቡኻሪ ና ሙስሊም ከኢብኑ ዑመር ከዘገቡት ሀዲስም እነዚያ ሶስት ሰዎች በጉዞ ላይ ሳሉ መሽቶባቸው ለማረፍ ወደ ዋሻ ገብተው ቋጥኝ ተንከባሎ መውጫ መንገድ ዘግቶባቸው ሶስቱም ለአሏህ ብለው የሰሯቸውን መልካም ስራ በመጥቀስ ወደ አሏህ ተወሱል በማድረግ ከነበሩበት ጭንቀት ወጥተው ጉዟቸውን ቀጥለዋል
ይህ የሚያመለክተን በመልካም ስራዎች ተወሱል ማድረግ እንደሚቻል ነው።
النوع الثالث:التوسل إلى الله تعلى بتوحيده
ሶስተኛው: በተውሂድ (ከአሏህ በስተቀር በእውነት የሚገዙት አምላክ)የሌለ መሆኑን በመመስከር ወደ አሏህ ተወሱል ማድረግ ነው።
አሏህ የነቢዩሏሂ ዩኑስን ዐሳ ነባሪ ሆድ ውስጥ ሆነው ተወሱል ሲያረጉ እንዲህ ይላል:{ በጨለማዎችም ውስጥ ኾኖ ከአንተ በስተቀር በእውነት የሚገዙት አምላክ የለም፣ጥራት ይገባህ፣እኔ በእርግጥ ከበዳዮች ነበርኩ በማለት ተጣራ) አል አንቢያ 87
ከዚህ ምንረዳው አንድ ሰው አሏህን በተውሂድ ነጥሎ መገዛቱን እየነገረ ችግሮቹ እንዲቀረፉለት ወደ አሏህ ተወሱል ማድረግ ይችላል።
النوع الرابع:التوسل إلى الله تعلى بإظهار الضعف والحاجة والإفتقار إلى الله
አራተኛው: ድክመትህን፣ወደ አሏህ ፈላጊነትህን፣እንደዚሁም ወደ አሏህ ከጃይ መሆንህን እየገለፅክ ወደ አሏህ ተወሱል ማድረግ ነው።
አሏህ የነቢዩሏሂ አዩብ ዐለይሂ ሰላም ታሪክ ሲያወሳ እንዲህ ይለናል:{ አዩብንም ጌታውን ሲል በተጣራ ጊዜ አስታውስ} አንቢያ 83
ነቢዩሏሂ አዩብ ዐለይሂሰላም ችግራቸውን በመጥቀስ ወደ አሏህ ተወሱል አርገዋል።
النوع الخامس: التوسل إلى الله تعلى بدعاء الصالحين الأحياء
አምስተኛው: በሂይወት ባሉ ደጋግ የአሏህ ባሮች በዱዐቸው ተወሱል ማድረግ ነው።
ልክ ሰሀቦች ነቢዩ ዘንድ እየመጡ ችግራቸው እየነገሯቸው ነቢዩም ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ችግራቸውን አሏህ እንዲያስወግድላቸው ዱዐ ያረጉ ነበር።ከነቢዩም ህልፈት ቡሀላ ሰሀቦች ወደ ነቢዩ ቀብር ሳይሆን የሄዱት ወደ ታላቁ ሰሀባ ዐባስ ረዲየሏሁዐንሁ ጋር በመምጣት አሏህን እንዲለምኑላቸው ይጠይቋቸው ነበር።
እነዚህ እንግዲህ ከሚፈቀደው የተወሱል ዐይነት የሚመደቡ ሲሆን በቀጣይ የሚከለከለውን የተወሱል ዐይነት በዝርዝር እናያለን
ወሏሁ አዕለም