በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ ና አዛኝ በኾነው
ኢስላማዊ ሕክምና(ሩቃ)
الرقية
بسم الله الرحمن الرحيم
الحمد لله رب العالمين والصلاة والسلام على نبينا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين أما بعد:
በዚህ ነጥብ ዙሪያ ለመፃፍ ያነሳሳኝ ነገር
አንደኛ: በሩቃ ስም የሚከፈቱ በውስጡ ሽርክ፣ዝሙት፣ የሚፈፀምባቸው ቤቶች በመብዛታቸው።
ሁለተኛ: አብዛኞቻችን ሩቃ እናረጋለን ነገር ግን ውጤቱ እምብዛም መሆኑ
ሶስተኛው: ሙስሊሞች በተለይ ሴቶች ና ወደ ገጠር አካባቢ ያለው ማህበረሰብ በሩቃ ስም ገንዘቡን ፣ ንብረቱን ለሼኽ ተብዬዎች እየገበረ መሆኑ ነው።
አሏህ ሱብሀነሁ ወተዐላ ሰዎችንም ጂኖችንም ሲፈጥር እርሱን ብቻ እንዲገዙ ና ከእርሱ ውጭ ያሉትን ጣኦት የተባለን ነገር በሙሉ እንዲርቁ ነው። ይህ የተፈጠርንለት ዐላማ ሲሆን ይህን የተፈጠርንለትን ዐላማ ለመፈፀም ስንጥር መንገዱ ሁሉ ወርቅ በወርቅ አይሆንም፣እውነተኞች መሆናችንን ለማረጋገጥ ሲባል በሂይወታችን ውስጥ ብዙ መከራዎች ና ፈተናዎች ይገጥሙናል።ፈተናውን በትዕግስት ያለፈ ሰው ቀሪውን የሂይወት ዘመኑን ደስተኛ ሆኖ የሚቀጥል ሲሆን በፈተናው የወደቀ ሰው ቀሪውን የሂይወት ዘመኑን በቁጭት ያሳልፋል።
ከሚገጥሙን ፈተናዎች አንዱ የተለያዩ በሽታዎች ናቸው።እነዚህ ፈተናዎች ወንጀሎቻችንን ለማበስ፣ደረጃዎቻችንን ከፍ ለማድረግ፣ወደ አሏህ እንድንመለስ ሲባል ነው።
ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንደነገሩን ማነኛውንም በሽታ አሏህ አያመጣም ለዚህ በሽታ መድሀኒት ያወረደለት ቢሆን እንጂ፣ያወቀው አውቆታል፣ያላወቀው አላወቀውም ብለዋል
ለዛሬ ላስቃኛችሁ የፈለኩት (ሩቃ) በመባል የሚታወቀውን ኢስላማዊ ሕክምና ነው።
ሩቃ ምንድ ነው?
ما هي الرقية؟
ሩቃ ማለት:ህመምተኛ እንዲፈወስ፣በሽታዎች እንዲወገዱ አሏህን መለመን ነው።
ሩቃ አሏህ ላይ ማጋራት (ሽርክ) የሌለበት እስከሆነ ድረስ ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ፈቅደዋሉ።
{اعرضوا علي رقاكم. لا بأس بالرقى ما لم يكن فيه شرك} مسلم
ነቢዩ ለሰሀቦቻቸው እንዲህ ይላሉ:{ የምታደርጉትን ሩቃ እኔ ዘንድ አቅርቡ፣በውስጡ አሏህ ላይ ማጋራት(ሽርክ) የሌለበት ሩቃ (በመደረጉ)ችግር የለውም} ሙስሊም 2200
ነቢዩም ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ራሳቸው በሩቃ ይታከሙ እንደነበረ ከሰሀቦች ተዘግቧል።
ሩቃ ለፈውስ ሰበብ ይሆን ዘንድ መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች ምንድ ናቸው?
ما هي شروط الرقية ؟
الأول: أن لا تتضمن شركا. كدعاء الأولياء وغيرها
አንደኛ መስፈርት: በውስጧ በአሏህ ላይ ማጋራትን(ሽርክ) አቅፋ የያዘች መሆን የለባትም።ከአሏህ ውጪ ወሊዮችን መጣራት ይመስል።
الثاني:أن تكون بكلام الله سبحانه وتعلى. أو بأسمائه وصفاته.أو بما ورد في الأحاديث النبي صلى الله عليه وسلم
ሁለተኛው መስፈርት:በአሏህ ንግግር(በቁርዐን)፣በአሏህ ስሞች ና ባህሪያቶች መሆኑ ና ከነቢዩ ንግግር(ሀዲስ) በመጣበት መሆን አለበት።
الثالث:أن تكون مفهومة المعنى. بأن لا تكون عبارة عن كلمات غير مفهومة كالتميمة وغيرها.
ሶስተኛው መስፈርት: የሚነበበው ነገር ትርጉሙ የሚታወቅ መሆን አለበት።ሂርዝ ና ሌሎችም ትርጉም አልባ የሆኑ ቃላቶች መሆን የለባቸውም።
الرابع: أن لا يعتقد أنها مؤثرة بذاتها.فالقى هي من باب فعل الأسباب. فالأسباب لا تؤثر بذاتها.
አራተኛው መስፈርት:ሩቃዋ በራሷ ተፅዕኖ ማድረግ ትችላለች ብሎ ላያምን ነው።ሩቃ ሰበብ እንደማድረስ ሲሆን ሰበብ ደግሞ በራሷ ተፅዕኖ ማድረግ አትችልም።
ሰበቡን ያደርጋል መፈወስ ግን በአሏህ እጅ ነው።ልክ ነቢዩሏሂ ኢብራሒም ዐለይሂሰላም እንዳሉት
قال الله تعلى (وإذا مرضت فهو يشفين) الشعراء ٨٠
{በታመምኩም ጊዜ እርሱ(አሏህ) ያሽረኛል) አሽ ሹዐራዕ 80
በአሏህ ፍቃድ እነዚህ መስፈርቶች የተሟሉ ከሆነ ሩቃ ለፈውስ ሰበብ ይሆናል።
ለዛሬ በዚህ እናቁም፣በቀጣይ ክፍል በዚህ ርዕስ ዙሪያ የተለያዩ ነጥቦችን የምናይ ይሆናል። ኢንሻ አሏህ
ኢስላማዊ ሕክምና(ሩቃ)
الرقية
بسم الله الرحمن الرحيم
الحمد لله رب العالمين والصلاة والسلام على نبينا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين أما بعد:
በዚህ ነጥብ ዙሪያ ለመፃፍ ያነሳሳኝ ነገር
አንደኛ: በሩቃ ስም የሚከፈቱ በውስጡ ሽርክ፣ዝሙት፣ የሚፈፀምባቸው ቤቶች በመብዛታቸው።
ሁለተኛ: አብዛኞቻችን ሩቃ እናረጋለን ነገር ግን ውጤቱ እምብዛም መሆኑ
ሶስተኛው: ሙስሊሞች በተለይ ሴቶች ና ወደ ገጠር አካባቢ ያለው ማህበረሰብ በሩቃ ስም ገንዘቡን ፣ ንብረቱን ለሼኽ ተብዬዎች እየገበረ መሆኑ ነው።
አሏህ ሱብሀነሁ ወተዐላ ሰዎችንም ጂኖችንም ሲፈጥር እርሱን ብቻ እንዲገዙ ና ከእርሱ ውጭ ያሉትን ጣኦት የተባለን ነገር በሙሉ እንዲርቁ ነው። ይህ የተፈጠርንለት ዐላማ ሲሆን ይህን የተፈጠርንለትን ዐላማ ለመፈፀም ስንጥር መንገዱ ሁሉ ወርቅ በወርቅ አይሆንም፣እውነተኞች መሆናችንን ለማረጋገጥ ሲባል በሂይወታችን ውስጥ ብዙ መከራዎች ና ፈተናዎች ይገጥሙናል።ፈተናውን በትዕግስት ያለፈ ሰው ቀሪውን የሂይወት ዘመኑን ደስተኛ ሆኖ የሚቀጥል ሲሆን በፈተናው የወደቀ ሰው ቀሪውን የሂይወት ዘመኑን በቁጭት ያሳልፋል።
ከሚገጥሙን ፈተናዎች አንዱ የተለያዩ በሽታዎች ናቸው።እነዚህ ፈተናዎች ወንጀሎቻችንን ለማበስ፣ደረጃዎቻችንን ከፍ ለማድረግ፣ወደ አሏህ እንድንመለስ ሲባል ነው።
ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንደነገሩን ማነኛውንም በሽታ አሏህ አያመጣም ለዚህ በሽታ መድሀኒት ያወረደለት ቢሆን እንጂ፣ያወቀው አውቆታል፣ያላወቀው አላወቀውም ብለዋል
ለዛሬ ላስቃኛችሁ የፈለኩት (ሩቃ) በመባል የሚታወቀውን ኢስላማዊ ሕክምና ነው።
ሩቃ ምንድ ነው?
ما هي الرقية؟
ሩቃ ማለት:ህመምተኛ እንዲፈወስ፣በሽታዎች እንዲወገዱ አሏህን መለመን ነው።
ሩቃ አሏህ ላይ ማጋራት (ሽርክ) የሌለበት እስከሆነ ድረስ ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ፈቅደዋሉ።
{اعرضوا علي رقاكم. لا بأس بالرقى ما لم يكن فيه شرك} مسلم
ነቢዩ ለሰሀቦቻቸው እንዲህ ይላሉ:{ የምታደርጉትን ሩቃ እኔ ዘንድ አቅርቡ፣በውስጡ አሏህ ላይ ማጋራት(ሽርክ) የሌለበት ሩቃ (በመደረጉ)ችግር የለውም} ሙስሊም 2200
ነቢዩም ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ራሳቸው በሩቃ ይታከሙ እንደነበረ ከሰሀቦች ተዘግቧል።
ሩቃ ለፈውስ ሰበብ ይሆን ዘንድ መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች ምንድ ናቸው?
ما هي شروط الرقية ؟
الأول: أن لا تتضمن شركا. كدعاء الأولياء وغيرها
አንደኛ መስፈርት: በውስጧ በአሏህ ላይ ማጋራትን(ሽርክ) አቅፋ የያዘች መሆን የለባትም።ከአሏህ ውጪ ወሊዮችን መጣራት ይመስል።
الثاني:أن تكون بكلام الله سبحانه وتعلى. أو بأسمائه وصفاته.أو بما ورد في الأحاديث النبي صلى الله عليه وسلم
ሁለተኛው መስፈርት:በአሏህ ንግግር(በቁርዐን)፣በአሏህ ስሞች ና ባህሪያቶች መሆኑ ና ከነቢዩ ንግግር(ሀዲስ) በመጣበት መሆን አለበት።
الثالث:أن تكون مفهومة المعنى. بأن لا تكون عبارة عن كلمات غير مفهومة كالتميمة وغيرها.
ሶስተኛው መስፈርት: የሚነበበው ነገር ትርጉሙ የሚታወቅ መሆን አለበት።ሂርዝ ና ሌሎችም ትርጉም አልባ የሆኑ ቃላቶች መሆን የለባቸውም።
الرابع: أن لا يعتقد أنها مؤثرة بذاتها.فالقى هي من باب فعل الأسباب. فالأسباب لا تؤثر بذاتها.
አራተኛው መስፈርት:ሩቃዋ በራሷ ተፅዕኖ ማድረግ ትችላለች ብሎ ላያምን ነው።ሩቃ ሰበብ እንደማድረስ ሲሆን ሰበብ ደግሞ በራሷ ተፅዕኖ ማድረግ አትችልም።
ሰበቡን ያደርጋል መፈወስ ግን በአሏህ እጅ ነው።ልክ ነቢዩሏሂ ኢብራሒም ዐለይሂሰላም እንዳሉት
قال الله تعلى (وإذا مرضت فهو يشفين) الشعراء ٨٠
{በታመምኩም ጊዜ እርሱ(አሏህ) ያሽረኛል) አሽ ሹዐራዕ 80
በአሏህ ፍቃድ እነዚህ መስፈርቶች የተሟሉ ከሆነ ሩቃ ለፈውስ ሰበብ ይሆናል።
ለዛሬ በዚህ እናቁም፣በቀጣይ ክፍል በዚህ ርዕስ ዙሪያ የተለያዩ ነጥቦችን የምናይ ይሆናል። ኢንሻ አሏህ