መቅረዝ


Kanal geosi va tili: ko‘rsatilmagan, ko‘rsatilmagan
Toifa: ko‘rsatilmagan


የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ መቅረዝ የኪነ-ጥበብ አፍቃሪያን ህብረት
ቴያትር፣ግጥም፣ወግ፣ደብዳቤ፣ወርቃማ ገፆች፣ፎቶ ግራፍን እንዲሁም ፊልምን አጠቃሎ ይይዛል

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
ko‘rsatilmagan, ko‘rsatilmagan
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ብርጋና ምስጢራዊው እረዥም ልብ ወለድ መጽሀፍ እሁድ ነሀሴ 9 ከቀኑ 7:30 ጀምሮ በህጻናት ማሳደጊያ ይመረቃል፡፡ ተገባዥ
እንግዶች
ደራሲ ይስመሀከ ወርቁ (ዴርቶጋዳ) እና ሌሎችም ባሉበት ይመረቃል በነጻ ትራንስፖርት መጥተው ይመርቁ ህጻናትን ይጠይቁ አድራሻዉን የጠፋበዎ ኮንቦኒ ኳስ ሜዳ ፋርማ ኮሌጅ ፊት ለፊት

ለበለጠ መረጃ 0963336337/0937485266
መቅረዝ የኪነጥበብ አፍቃሪያን ህብረት
@mekereze


📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖
የመፃህፍት ጥቆማ
📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖
ሠላም እንደምን ናችሁ ውድ የአምዳችን ቤተሰቦች፤እንደምን ናችሁ? የዛሬው የመፃህፍት ዳሰሳችን የሚዳስሰው መፃሃፍ፦
አርዕስት ፦ የህሊና ደወል
ደራሲ፦ በዓሉ ግርማ (ልብ ወለድ)
በማንኩሳ አሳታሚ
ሦስተኛ ዕትም 2005 ዓ.ም
የመሸጫ ዋጋ 150(አንድ መቶ ሃምሳ ብር)
የገፅ ብዛት 248
ይህ መፃሃፍ የመጀመርያ ዕትሙ በ1966 ዓ.ም ነው።የእውነት ሀዲስ ሳህሌ የኛ ዘመን ወጣት ክፍተትን የሚያነሳ፤ከብዙ ተቃውሞ፣ከብዙ ሁካት ጥቂት ሥራ ብዙ ትርጉም እንዳለው ልባችን ውስጥ በሥራው ሥራ በዝምተኝነት ያነቃናል።
ፊታውራሪ ተካ በእምነታቸው ጥንካሬ ልጃቸውን ሊወስድ የመጣን ሙሽራ መልሰው እኛስ? በእምነታችን እስከየት ድረስ ነን ያስብሉናል።
አይናለም የፊትአውራሪ ተካ ልጅ በአባቷ እምነት መታመን አድጋ፣ባለቤቷን ሀዲስ አግብታ ያመነችበትን ለመፈፀም በምትሄደው ጉዛ ውስጥ እኔስ ምንም አላዋቂ ብሆን እንዴት እንደ ቶሎሳ ላመንኩበት ህልሜ በኔው መንገድ አልሞትም...በራሴ መንገድ መኖር አልቻልኩም!፣እሺ ቢያንስ ለተስፋዬ፣ለቃሌ በኔ መንገድ አልሞትም?
የበዓሉ አተራረክ፣በዚህ ውብ የልቦለድ አለም ውስጥ ተሸምኖ እነሆ በረከት ይላችኃል፣እነሆ በረከት፦
"ህይወት ራሱ ህልም - ቅዠት መስሎ ታየው።ምናልባት ከዚህ ቅዠት አምልጠን ወደውነተኛው ህይወት ዘለአለማዊ ህይወት የምንገባውና ከፍጥረት ጋር የምንዋሀደው በሞት ብቻ ይሆናል፤ሞት ብቻ ነው የፍጥረት ሁሉ የመጨረሻ ግብ - "
ገፅ-170
ደሞ አንድ ቀን ኢትዮጵያ ሀገራችን
"እጅህን በተስፋ ስጠባበቅ ኖርኩ ልጄ አሁንስ ታከተኝ.."
እንዳትለን በፍቅር የተሞላ ልባችንን፣በእምነት የተሞላ ኑሯችንን እና በሥራ የተሞላ እጃችንን አንንፈጋት።
መልካም ንባብ
@mekereze
አግኙን
@zeki23Etete
@aduyes
@test17
ዘካርያስ ምህረቱ ወ.በ
5/12/2013ዓ.ም
ፈጣሪ በምህረት ዐይኑ ምድራችንን ይመልከትልን ።
አሜን !!!


ማስተካከያ
ዛሬ የነበረው የበጎ አድራጎት ስራ ወደ ፊታችን ቅዳሜ ማለትም ነሀሴ 8 2013 ዓ.ም የተዛወረ መሆኑን ከታላቅ ይቅርታ ጋር እንገልፃለን።

መቅረዝ የኪነጥበብ አፍቃሪያን ህብረት
@mekereze


===========================
ከመቅረዝ ማህደር
===========================
📚 1) " መለያየት !" 📚
ደሞ...
ሸምነን ለነበር፣ነበር ልናለብሰው
መልካሙን ለወራሽ ልናወርሰው
ለታሪክ ላይዳ፣መንሽ ይዘን
እህሉን ከገለባው ለይተን
ከዛሬ ፊት ለፊት
በታሪክ መማሪያ ነት
በነግ አለን እምነት ፍታት
በታሪክ መዐድ ፍልቅልቅ
በጎደለ ሞልተን ልንሰብቅ
ትናንት ባለቀስን ልንስቅ፤
ተገናኘን ለጭንቅ፣ለምጥ
ነበር ወልደን ልናመልጥ።
ከቻልን ከእኛችን ልንበልጥ
ከልብ ያለ ቋጥኝ ልናቀልጥ
በይቅርታ ውብ ፈረስ
ሰግረን የፈረሰ ልናድስ
ተገናኘን ለመለየት
ወይ መለየት...
ዘካርያስ ምህረቱ ወ.በ
ሐምሌ 30/ 2013 ዓ.ም

📚 2) " ዝም፣ለመኝታ..."📚
ዝም ካለው ቦታ፣በልኬ በተበጀ ጎታ
ሳታበዙ ለአፈር፣የአፈር ጋጋታ
ዝም ብላችሁ፣በዝምታ
ተሸክሜው ከነበረው
ለመኖሬ ላለው፣
በእንቅፋቴ ለምገባው
መሬት እንዳይከብደው
እምባችሁን ይቅርታችሁ ይቅደመው
ይቅር በሉኝ፣ይቅር ብያለው ።
የዝምታን ለመምቴ፣ተከትላችሁ በዕምነቴ
ሄቤሎ እንዳልሆን፣ዘር ይሁን ገለባነቴ
ሕልም ምን ይሳነዋል መቼም
ልማድ ሆኖ በሌለው አጎልም
እምባ ባያሻውም የግዴታ
አበባው ይረግፋል አበባው ቦታ፤
ዝም፣ዝምታ፣ዝም፣ዝምታ
ልተኛ በፎይታ፣ዝምታ!፣ዝምታ
ዘካርያስ ምህረቱ ወ.በ
ሐምሌ 30/ 2013 ዓ.ም


@mekereze
@mekereze
@mekereze
ፈጣሪ በምህረት ዐይኑ ምድራችንን ይመልከትልን ።
አሜን !!!
መልካም ቀን።


...ከእለታት አንድ ቀን አሚር አውዘል ቀርነይኒ ቀንድ አበቀለ።በጥምጣሙ ደበቀው።አንድ ቀን ግን ፀጉር ቆራጩ ቀንዱን አየበት።
"ስለዚህ ነገር ከእኔና ከአንተ በቀር የሚያውቅ የለም ትናገርና ወዮልህ!"
"ኧረ እኔ አልናገርም" ይላል ሰውየው ግን መናገር አስፈለገው።ለሰው እንዳይናገር መጥፊያው ይሆናል፤ግን ወሬው ሆዱን ነፋው።አልቻለም።በመጨረሻም ከከተማ ወጥቶ ርቆ ሄዶ መሬት ቆፍሮ ለመሬት ነገራት "አውዘል ቀርነይኒ ቀንድ አብቅሏል!" ይህን ተንፍሶ ወደ ጉዳዩ ሄደ።እዚያች ስፍራ ዋንዛ ዛፍ በቀለ።ጊዜው ሲደርስ ተቆረጠና ከበሮ ሆነ።ሰዎች ከበሮውን ሲመቱት"አውዘል ቀርነይኒ ቀንድ አብቅሏል!" ይላል።

ወይ አውዘል ቀርነይኒ!
(ከሰብሀት ገብረእግዚአብሔር እግረመንገድ ገፅ 98
አርትኦት ደምሴ ፅጌ )
@mekereze


ለመልካሞች፡፡
እሁድ ማለትም በቀን 02/12 2013 ዓ.ም የመልካም ሰዎች መዋያ ተዘጋጅቷል፡፡ በ ቀኑ ለት ማንኛውም ተማሪ መሳተፍ የሚችል ሲሆን፡፡ የበጎ ስራው የሚያካትተው
1,ተሳትፎ እና min ከ30 ብር ጨምሮ ለቡና ፕሮግራም የሚውል፡፡
2, ማንኛውም ልብስ
3,መፀሐፍ: ደብተር: ብዕር/እስኪብርቶ (ከአንድ ጀምሮ )
4,መገኘት እና ማስተባበር ሌሎችም እናንተ ጋር ያለመልካም ስራ ሁሉ፡፡

ቦታ 05 አቤኔዘር suporting and development volunter assocation

#መቅረዝ የኪነ- ጥበብ አፍቃሪያን ህብረት
ጋር በመተባበር
በጎ ስራ ለመስራት አንቦዝንም፡፡

@mekereze

Tell 0963336337


ቅዳሜ ጉድ ፈላ

ሰማይ መልቲ ሚዲያ ፕሮዳክሽን ከሀዋሳ ዩኒቨርስቲ መቅረዝ የኪነጥበብ አፍቃሪያን ህብረት ጋር በመተባበር የኮከቡ ሰው የተሰኘውን ቴአትር በሀዋሳ ሚሊኒየም አዳራሽ ለተመልካች ያቀርባል።በመሆኑም መላው የግቢያችን ተማሪዎች የተጋበዛችሁ መሆኑን ከወዲሁ ለመግለፅ እንወዳለን።

መግቢያ፡ 100 ብር


መቅረዝ የኪነጥበብ አፍቃሪያን ህብረት

@mekereze


ተጎንጓኝ ስንኞች !!!
ሠላም ቤተሰቦቻችን ! እስቲ ዛሬ እነሆ እንበላችሁ በዝምታ...
1. የሐበሻ ልጆች
========

ፕሊስ እባካችሁ
ጥንት አባቶቻችሁ
አለቱን ፈልፍለው ፊደል የቀረፁ
አክሱምን ያቆሙ ‘ሮሀን ያነፁ
በባህል በልማት በወግ የከበሩ
በአገራቸው ስርዓት ኮርተው የሚኖሩ
……ነበሩ እያላችሁ
ነገር አትጀምሩ
ሙድ አታበላሹ አቦ ምን ነካችሁ?
……እንዴ ምን ነካችሁ !
እኛ የዛሬዎች እንደ አባቶቻችን
ቅኔ የምንዘርፍ
ጥበብ የምንነድፍ
ጠቢብ ብቻ ሳንሆን
የአዲሱ አለም ስርዓት በእውቀት ያጠመቀን
ዘመን የሚዘፍነን አለም የሚዘርፈን
እኛው እራሳችን ቅኔዎች እኮ ነን
……………ስለዚህ እባካችሁ!
#ጥንት #አባቶቻችን
መርከብ አበጅተው ባህር ያቋረጡ
በእውቀት የበለጡ በጥበብ ያጌጡ
እንዲህ ያደረጉ እንደዛ የሠጡ
እትት…ብትት… አትበሉን ጠዋት ማታ
አቦ ሰላም ስጡን ኳስ እንይበታ ! ! !
……እንዴ ምን ነካችሁ?
……እስኪ ይታያችሁ
እንደ አፄ ቴወድሮስ ሽጉጥ ከመጨለጥ
ለእንግሊዝ እግር ኳስ ምናለ እጅ ብንሠጥ
ምናለበት እስኪ እዚህ ከመቀመጥ
ቪዛ ሳናስመታ ትኬት ሳናስቆርጥ
በአየር ሳንሳፈፍ ባህር ሳናቋርጥ
በዲ ኤስ ቲቪ ሾልከን ብናመልጥ
በአዲሱ አለም ስርዓት በእውቀት የተጠመቅን
ግሎባላይዜሽን ጠልቆ የዘለቀን
የነቃን የበቃን የገባን እኮ ነን
ምናለበት ታዲያ ሀርድ ባትሰጡን
ሀገር ልማት ታሪክ ምናምን ባትሉን
ምናል ብትተዉን !
ምናል ብትረሱን !
እውነት ምን ነካችሁ?
ግሎባላይዜሽን ምናል ቢገባችሁ
ምናለበት እስኪ
በኢትዮጵያ በሬ አሜሪካ ቢያርሱ
እስኪ ምናለበት
ለጋሀር ተኝቶ ለንደን ላይ ቢነሱ
እኛኮ ልዩ ነን ቅኔ ስደተኞች
በመንፈስ ኮብልለን
ሀገር ነቅለን ወጥተን
አንድም የማንጎድል ምዕታተኛ ቁጥሮች
ኖረንም ሄደንም " መቶ" ሚልዮኖች
እፁብ ድንቅ እኮነን ጉድ ነንኮ ሀበሾች
የአዲሱ አለም ስርዓት በእውቀት ያጠመቀን
በስታዲየም ታጥረን አለምን የናቅን
ሁሉን ነገር ትተን
ሁሉንም ‘ረስተን
ስለኳስ አስበን ስለኳስ አውርተን
ከኳስ ጋር ተኝተን ከኳስ ጋራ ነቅተን
ቀን የቼልሲ ነገር ሀሳብ የሚሆነን
ሌት የአርሰናል ጉዳይ እንቅልፍ የሚነሳን
የማንቼ ድል መንሳት የሚያስፈነጥዘን
የሮኒ ወለምታ የሚጠዘጥዘን
የአንጄሊና ትዳር የሚወዘውዘን
እንጨነቅበት ሀሳብ የጨነቀን
እንቸገርበት ችግር የቸገረን
ድፍን የሀበሻ ዘር እኛኮ ቅኔ ነን
ምናለበት ታዲያ አቦ ባትወግሙን
ሐገር ልማት ታሪክ ምናምን ባትሉን
~~~~~||~~~~~~

ጌትነት እንየው

2. ዘመንኛ ስንኞች ።
ትናንትን የሀሳብ ምግብ፤
ዛሬ እንደ እንስሳ ስገርብ፤
በቋንቋዬ ሳመነዥግ፣
ሳደቅ ጥጋቤን ሰፈልግ፤
የሚያዝ አለመያዜ፣
አሳቅፎኝ ትካዜ፤
ያለፈን ዛሬ ላይ፣
አድርጌ ለነገ አዋይ፤
ከእድሜ ቁጥር ሰጣ ገባ፤
አበጅቼ ባዶ አምባ፤
ሳፍተለትል ቅረት ፀጉር፣
ብጫቂ ወረቀት ስመረምር፤
መካን አዕምሮዬን በተስፋ ካብ፤
በጉም ውጥን ድርብርብ፤
ክቤ፣ክቤ ልጠግብ፤
እቀነጥሳለው፣
እገርባለው፣
በትናንቴ፣የነግ ተስፋ፣
ዛሬዬን ዘመቼ ላሰፋ፤
ያባት ውርሴን አውድሜ፤
ባዶዬን ያለ ትጥቅ ቁሜ፤
የልጅ ብድሬን በዚ አቅሜ፤
ልከፍል ምዬ በቃሌ፣
አመልጣለው ብዬ ከአመሌ፤
ወደ ትፋቴ ላልመለስ፣
ስንቅ አንግቤ የለት ውርስ፤
እነታረካለው፣በቃ እላለው፣
ዛሬ ለነግ አለው፤
ትናንትን ረግማለው፤
እቀነጥሳለው፣
እገርባለው፣
ኑሮዬ ነው፣
አመልጣለው፣
እላለው፤
መዳረሻ እንዳለው።

ዘካርያስ ምህረቱ ወ.በ
2013 ዓ.ም


@mekereze
@mekereze
@mekereze
አግኙን
@zeki23Etete
@aduyes
@test17
ፈጣሪ በምህረት ዐይኑ ምድራችንን ይመልከትልን ።
አሜን !!!

ሰናይ አዳር ።


"ጨለማን መተቸት ብርሃን አያመጣም
ክፋትን መኮነንም ደግነት አይሆንም
ኋላቀርነትን ማጥላላት ሥልጣኔ አያመጣም
ጦርነትን መፍራትም ሠላም አይሆንም
እንዲሁም ረሃብን አለመፈለግ ጥጋብ አያመጣም ።
ዕውቀትና በጎ አመለካክት
ግን ማህበረሰብን መቀየር ይችላሉ ፡፡"
.
(ዶ/ር ምህረት ደበበ)


መረጃ
የቶክዮ ኦሎምፒክ ሰዓቱ በግልፅ አናቀውም እያላችሁ ለምትገኙ ውድ ኢትዮጵያዊያን ይሄ መረጃ አስፈላጊ ሆኖ ስላገኘን ልናጋራችሁ ተገደናል።በመሆኑም ሁሉም ውድድሮች በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የመዝናኛ ቻናል መከታተል ትችላላችሁ።


ድል ለኢትዮጵያውያን 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

መቅረዝ የኪነጥበብ አፍቃሪያን ህብረት
@mekereze


/ተጎንጓኝ ስንኞች/
እስቲ ዛሬያችንን እውነትን መደርደሪያ እንድትሆነን እና የልብ የልባችንን እንድንወያይባት እንፍቀድ፤እንጠያየቅ፤እንመካከር ! ማን በገጻችን ላይ የእለታትን ምስል እያሳረፈ ነው ? ምን በየትኛው ቀን አትርፈናል ? ዛሬን ለማን በስጦታ መልክ ሰጠን ? ከአላማችን የሚያደርስ ከምን ምን አተረፍን ? እነሆ እንደመግቢያ እንዲ ካልን፣መሀሉ አይነገርም ብለን ወደ ሌላኛው ጠርዝ እንዝመት...

1. የጠፉት፣በጎች

ለአንዷ በግ ብሎ ~ ከሰማይ ወረደ
አንዷን በግ ሊታደግ ~ እንደበግ ታረደ
አንዷን በግ አድኖ ~ ወደ አባቱ ሄደ
° ° °
የምፅአት ቀን ደርሶ ~ መለከት ሲነፋ
ዘጠና ዘጠኙ ~ የገቡበት ጠፋ
° ° °
የገቡበት ጠፍቶ ~ ዘጠና ዘጠኙ
ታስሰው ታስሰው ~ ከሲኦል ተገኙ
===||===
ከሙሉቀን ሰ•
2. ይሁዳ

እኚያ ጓደኞችህ ጴጥሮስ ወይ ዮሀንስ
ናትናኤል ፊሊጶስ
ቀራጩ ማቲዎስ
ሌሎቹም በሙሉ
ጌታ ሆይ እኔ እሆን? እኔ እሆን? ሲሉ
አይደለም ሲባሉ
የእነሱ እናቶች በደስታ ሲዘሉ
ምናለች እናትህ አንተን ሲጠቁምህ
ከደሙ ላይ ነክሮ ምልክት ሲያደርግህ
ዐይኗ ምን አነባ ልቧ ምን ታዘበ
ከናንተ አንደኛው ዲያቢሎስ ነው ሲልህ እግር እያጠበ
ከየት ነው ትዕግስቷ
የእናትህ አንጀቷ
የመቻል ፅናቷ
ምናለች ? ይሁዳ ምናለች እናትህ? አንተን ሲጠቁምህ?
ምልክት ሲያደርግህ
እንደ ማሪያም አለቀሰች?
ለኔ ስትል ብላ ወድቃ ተማፀነች?
ወይንስ ለልጇ ያንተ እናት ጨካኝ ነች?
ምናለች እናትህ ታማኝ ነው ስትል ይሁዳ ያለችህ
የሰው ልጅ ይሰቅሉታል
ሰቅለው ይገድሉታል
ቢገድሉት ይነሳል
ግና ላሰቀለው
ግና ላስገደለው
ወዮለት ለዛ ሰው
ብሎ ሲናገርህ
ምናለች እናትህ አንተን ሲጠቁምህ
ከደሙ ላይ ነክሮ ምልክት ሲያደርግህ
እናትህ መለሰች
እንዲህ ተናገረች?
እውነት ነው ጌታ ሆይ ባይወለድ በተሻለው
ግና እንድወልደው እናቱ እንድሰኝ ማሕፀኔን ብትፈታው
በአርኣያ በአምሳልህ ሰው አርገህ ብትሰራው
የወለድኩስ እኔ የፈጠረው ማነው
ብላለት መለሰች
ወይንስ ምን አለች
ምን አለች እናትህ?
አንተን ሲጠቁምህ
ምልክት ሲያረግህ!!
ኤፍሬም ስዩም

አግኙን
@zeki23Etete
@aduyes
@test17
መርጣችሁ ለምርጦቻችሁ ለማጋራት
👇👇👇
@mekereze
@mekereze
@mekereze
ፈጣሪ በምህረት ዐይኑ ምድራችንን ይመልከትልን ።
አሜን !!!


የሮማን ዘውዴ ልጅ dan repost
አስቸኳይ የስብሰባ ጥሪ
መቅረዝ የኪነ-ጥበብ አፍቃሪያን ህብረት ባለፉት ወራት ያከናወናቸውን ተግባራት ግምገማና አዳዲስ ስራ አስፈፃሚዎችን የመሾም ተግባራት ሲያከናውን መቆየቱ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ያለውን ርክክብ ለማካሔድና በጠቅላላ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ለመስጠት እንዲሁም የአዳዲስ ስራ አስፈፃሚዎችን ሹመት ለማፅደቅ መላ አባላቱን በቀን 24/11/2013 ዓ.ም ለመሰብሰብ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም መላው የህብረቱ አባላት በእለቱ በ ህ.ቁ 129 ከ ቀኑ 8፡00 ላይ እንድትገኙ ስንል ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ይህ ስብሰባ በስልጠና ላይ የሚገኙ ሰልጣኝ ተማሪዎችን የማያካትት መሆኑን ከወዲሁ እንገልፃለን፡፡




መቅረዝ የኪነ-ጥበብ አፍቃሪያን ህብረት
ሐምሌ፣2013 ዓ.ም


ሠላም እንደምን ናችሁ ውድ የጥበብ ወንድም፣ እህቶቼ ? እኔ እግዚአብሔር ይመስገን ደና ነኝ።እናንተን የእውነት አስባችኃለው፣እውነት ! ተለይቼ አልተለየኃችሁም።እኔ የእውቀት ቤቴን ብዙ ያስተማራችሁኝን ጓደኞቼን በቻልኩት ሁሉ አሁን ካላችሁበት የሞቀ የመቅረዝ ቤት ስትወጡ ተሰናብታችሁ ወደዚ ስትቀላቀሉ ይህኛው ብቸኝነት እንዳይነካችሁ እና አቅማችሁን የምታሳዩበት መድረክ እንዳታጡ በቻልኩት ሁሉ እንደ ድልድይ ሆኜ እናንተን ለመጠበቅ እሞክራለው።እናንተስ አዲሶቹን ቤተሰቦቻችሁን በምን ያህል ወኔ እና ቆራጥነት ለመቀበል፤ያወቃችሁትን ለማሳወቅ እየጣራችሁ ነው ? ይህን ያህል ካልኩ ወደ ዝርዝሩ በስልክ ልግባ፦

መቅረዝ
መቅረዝ፣የእውቅ ሰው ጓዝ
አንድ ሰበዝ ማሳያ ለመምዘዝ
ማለፍያ መንገድ መያዝ
መንገድ አለ ከመንገድ
የሚመረጥ ካላማ እንዲወስድ
ከሰውም ሰውነት፤ከቅንም ቅንነት
ከሁሉ ማሳያ፣ለአብነት
መቅረዝ ቤት አለበት ።
ሙሽራ እስካለ ሐዋርያ አያውቅ ጾም
ሰተናል እንግዲ ይሁን የዐለም
ለተከልነው መልካም ውሃ አትጡለት
ለሠራነው ሕፀፅ መቀስ አበጁለት
አደራ፣አደራ፣አደራ በሀቅ እንደ መቅረዝ
ሻማ አሻሙበት፣ሻማችሁ ክብረት አይታረዝ
ደርቡት ብርሃን፣ብርሃን ይሁን ሁሉ
ሰውን እስከቻለ ቻሉት እንዳመሉ።
ዘካርያስ ምህረቱ ወ.በ
የሥነጽሁፍ ክፍል ሀላፊ


📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚
ከመቅረዝ ማህደር
📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚

1) ጠይቃለው !!!
ለምንድን ነው የምትኖረው ?
እኔው ?
እሺ ለምንድን ነው የማትሞተው ?
ካለው ?
ማን እየጠየቀኝ፤ጥያቄስ ምንድን ነው ?
እያልኩኝ፣እላለው
ማለትስ ምንድን ነው ?
ዘርፋፋ ሕይወትን፤በሎጋ ጣቶቼ
መንካት፣መዳሰስን ትቼ ላልተው ትቼ
ምን ደረሰ ዘመን፤የማን ?
ምን ተገኘ፤ከምን ?
ማን እየጠየቀኝ፤ጥያቄስ ምንድን ነው ?
እያልኩኝ፣እላለው
ማለትስ ምንድን ነው ?

ዘካርያስ ምህረቱ ወ.በ
2013 ዓ.ም
2 ) ነይ...፤
ነይ አንቺ አሳ፣
ብርድ እኮ ነው አበሳ ፤
ግቢ ከኔ መረብ፤
ምን ደሃ ሆኜ ብራብ፣
እሳት አይጠፋኝም የሚደረብ፤
ከጥዑም ቅቤም ባለኝ፣
ብነፍግ ሆዴ አይቀበለኝ !፤
ነይ አንቺ አሳ፣
ብርድ እኮ ነው አበሳ፤

ዘካርያስ ምህረቱ ወ.በ
2013 ዓ.ም
(መነሻ ሀሳብ ከመጽሐፈ ጨዋታ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ
ከዘነብ ኢትዮጵያዊ)

መልካም ሰንበት !




መቅረዝ ቤት ከነበሩ ልምዶች እነሆ አንዱ
አፈቀርኳት ። ደብዳቤ ልፅፍላት ብሞክርም አልተሳካልኝም ። ለብዙ ቀናት ሀሳብ ትካዜ አበዛው ። እንዳቅሜ ግጥም ጻፍኩላት ። ደጋግሜ ጥያቄዬን ጻፍኩላት ። እሽ ብላ መግባባት ቻልን ። ብዙ ጊዜ አብረን ቆየን ። በመሀል ተነስታ እምቢኝ አለች ። ሌላም ደጅ ሀድራ ሞልቶላት መሰል ሄደች ።እሷን ለማግኘት ስል ባገኘዋት ግጥም ፍቅር ወድቄ እሄው ዛሬ ግጥም በውብ ግጥምነቷ ታጽናናኛለች ።ዳብሳ ታሳርፈኛለች ።ስቃ ታስቀኛለች፤አልቅሳ ታስለቅሰኛለች።እኔም ከሷ ቁንዲ ለመድረስ እታገላለው፤ሩቅነቷን ለማቅረብ እጥራለው።ታሪኬ በአንድ ትንፋሽ ይጨለጥ ቢባል ይህ ነው።
ዘካርያስ ምህረቱ ወ.በ
2013 ዓ.ም
(እናንተም አጋሩን!!! በደብዳቤ፣በግጥም፣በሌላም።ብቻ አጋሩን !!)


ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለዛሬዋ ቀን አደረሳችሁ።ኢትዮጵያ በተሳካ ሁኔታ ሁለተኛውን የውሃ ሙሌት አጠናቃለች።እኛም የተሰማንን ደስታ ለመግለፅ እንወዳለን።



መቅረዝ የኪነጥበብ አፍቃሪያን ህብረት

@mekereze


መቅረዝ የኪነጥበብ አፍቃሪያን ህብረት

@mekereze


/ተጎንጓኝ ስንኞች/

በዘመን መዘመን ውስጥ ከብዙ ዓመታት ልቦናችን ማስተዋልን ከተካነች አንድ ዓመተ ምህረት በብዙ ዘመናትውስጥ አለች።በአንዲት ዓመተ ምህረት ውስጥ አንዲት ምህረት፤በፍፁም ቀናነት የምንሰጣት፤ምንም ባለ መጠበቅ..ሎሬት እሳት ወይ አበባ ውስጥ "እሳት አንሆን ወይ አበባ
በሕቅ -እንቅ ስንባባ
ባከነች ልጅነታችን ፥ እየቃተትን ስናነባ፡፡......" ይለናል እስቲ ይህን ለምድር የከበደ ቅኔ በታገል ሴፉ "
ያላንዳች ፍርሃት-ያለምንም ችግር
ባህሩን ከፍዬ- ህዝቤን እንዳሻግር፡፡" ሌላ ግጥም አጅበን ከልባችን አስተውለን አንዲት ምህረት በመስጠት !!! ሌላ የምህረት ዓመት እንቀበል።መልካሙን ሁሉ ተመኘን !
1. እሳት ወይ አበባ
..........
ይቅር ብቻ አንናገርም፥
እኔና አንቺ አንወያይም፥
ለውይይት አልታደልንም
እንዲያው ዝም እንጂ ዝም.....ዝም፡፡
አበባ አንሆን ወይም እሳት
ተጠምደን በምኞት ቅጣት
ሰመመን ባጫረው መአት
እድሜአችንን እንዳማጥናት....
እሳት አንሆን ወይ አበባ
በሕቅ -እንቅ ስንባባ
ባከነች ልጅነታችን ፥ እየቃተትን ስናነባ፡፡......
ፈራን፤ አዎን ፍቅር ፈራን፥
የነፍስን አንደበት ዘጋን፥
የእድሜ ጠብታችንን ምጥ፥ የጣር ፅንሳችንን ልሣን፥
ልጅነት የለገሠንን
በመለኮት የቀባንን
በእሳቱ ያጠመቀንን
የፍቅር አምላክ በጥበቡ፥ በሥልጣን ያላበሰንን
ፈራን፥ አዎን እውነት ፈራን
የስሜት እስትንፋስ ነሳን፡፡ ....

©ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን

2. የቀበሮ ፀሎት

------
እባክህ አምላኬ- ብትሬን ቀባና
እኔም ልወዝወዘው-የሙሴን ጎዳና
ያላንዳች ፍርሃት-ያለምንም ችግር
ባህሩን ከፍዬ- ህዝቤን እንዳሻግር፡፡
*
አቤት የኔ ጌታ ይህም አያረካም
በቃልህ ታምኜ -ከሆንኩልህ መልካም
ለእኔም ፍቀድልኝ-ያብራምን ምልክት
ከምድር አሸዋ-ዘሬ እንዲበረክት፡፡
*
አቤቱ ምን ልሁን-ይህም አልጠቀመኝ
እስቲ እንደ ዮናስ-ህዝብ ፊት አቁመኝ
*
ትንቢቴን ሰምቶልኝ-ሀገር ይተራመስ
ሰው እህል ይጡም-ከብቱም ሳር አይቅመስ፡፡
ይህም አያረካም-ይልቅ እንደዳዊት
አንተን በሚፈራ-ብዙ ሺህ ሠራዊት
ዙፋኔ ተከቦ-በደስታ እንዳመልክህ
የዚህን ሰው ኮከብ -አውጣልኝ እባክህ
*
አደራህን ታዲያ- ጭንቅ አትወድም ነፍሴ
ልመናዬን ሰምተህ-ካደረግከኝ ሙሴ
መከራውን ማረኝ-ያርባ ዓመት ስደቱን
በሲና በረሃ-መራብ መጠማቱን፡፡
*
ነቢዩ ዮናስን -አርገህም ስትፈጥረኝ
የባህሩን ፍዳ- ያሳውን ሆድ ማረኝ፡፡
*
አብረሃምን ሆኜም-በደስታ ሳመልክህ
ልጅህን እረደው-አትበለኝ እባክህ፡፡
***
የዳዊትም ኮከብ-በኔ ላይ ሲወጣ
እባክህ አምላኬ -ጎልያድ አይምጣ፡፡

©ታገል ሰይፉ

ለሀሳብ አስተያየታችሁ
አግኙን
@zeki23Etete
@aduyes
@test17
መርጣችሁ ለምርጦቻችሁ ለማጋራት
👇👇👇
@mekereze
@mekereze
@mekereze
ፈጣሪ በምህረት ዐይኑ ምድራችንን ይመልከትልን ።
አሜን !!!


ከፀጋ ጋር ከተጨዋወትናቸው ገጠመኞቻችን ብዙዎቹን አስታውሳቸዋለው።ፀጋ ያስቀኛል።ብቻዬን ቁጭ ብዬ በሀሳቤ ውል ሲል ደሞ ያስቆዝመኛል።ፀጋ ተሰጦውን ይዞ፣በተሰጦው እያሳቀ ነገን የሚጠብቅ፣በትናንት የሚፀፀት ይመስለኛል።ትናንት በትዝታ ከፈን ተከፍና መቃብር የወረደች፤ነገ በዛሬያችን ማህፀን የተፀነሰች ፤ዛሬ የወለድናት ልጃችን ወሆኗ የተሰወረበት ምስኪን ይመስለኛል።ከባለ ትልቅ ታሪክ፣ትንሽ የታሪክ ማሸጋገሪያ ድልድይ፣ከድልድዩ ባሻገር ይመጣል ጠባቂ ትውልድ ባለቤቷ ሀገራችን ትንሽ ብንጨልፍ እነሆ ፀጋ ሆነ...።እንቁ ባለሙያዎችን ጉሽ ጠላ ውስጥ እንደተገኙ ዳይመንዶች የመተፋትን እጣ ፈንታ ስታግታቸው እዚ ደርሳለች እና ሀገራችን...።ከሀገራችን ጨልፈን ፀጋን፤ከእኔ እና ከፀጋ በእውነተኛ ታሪክ የተመሰረተ ጨዋታ ጨልፈን እነሆ...
********************************
እኔ አስረኛ ክፍል ላይ የትምህርት ዘመኔ አብቅቶ እስክሪብቶና ደብተር ስሰቅል...እሷ አስርን ተሻግራ ፤ አስራ ሁለትንም በጥሩ ውጤት አልፋ... ዩኒቨርስቲ ገባች።መቼም ብቸኛ ጓደኛዬ ናት...ለሷም ብቸኛ ጓደኛዋ ነኝ።
ሌላ ሀገር ከሄደች በኃላ በቃ ሌላ ሆነች።ስደውል አታነሳም።የተደወለውን አይታም መልሳ አትደውልም።
የትምህርት ሲሚስተሩን ጨርሳ ስትመጣ ደውላ እንደናፈኳት፣ ለመደወል እንዳልተመቻት ምናምን በቅልጥፍና ትነግረኝና እቤታቸው ዶሮ እንዳርድ በዛውም እንዳገኛት ትማፀነኛለች።

ይህ ሁኔታ ቢደጋገምም ስትደውል ስልክ ማንሳቴን አልተውኩም....
ስልክ እንዳነሳው"ብቻ ዛሬም ዶሮ እረድ እንዳይሆን ?"
አልኳት።"አንተ ደሞ ነገር ስትወድ ናፍቀህኝ ነው የደወልኩት"አለችኝ።እኔም በደብራችን "እስቲ ማርያምን በይ" አልኳት።"ማርያምን" አለችኝ የምድሩን ማር እና የሰማዩን ያም በምናቧ እያጣጣመች።
አመንኳት።እኔም ስልኩን ዘግቼ ናፍቃኛለችና ስበር 02 ከሚገኝው ቤታቸው ደረስኩ።
ቤት ስደርስ እናቷ በረንዳላይ በሰፌድ ስንዴ እየለቀሙ ነው። እሷ በስተቀኛቸው ቁማ ስልኳን ትጠቀማለች።ሰፌዱን እያስቀመጡ" ጎሽ ፀግዬ እንኳን መጣህልኝ ዶሮ የሚያርድልኝ ሰው አጥቼ ነበር...እንኳን መጣህልኝ ።" አሉኝ።እሄኔ ዞር ብዬ... አየዋት።መቼም ከዚህ በኃላ ንስሀ መግባት የሷ ድርሻ ነው...አሻፈረኝ ካለች እንደ ይሁዳ የሷን ሀጢያት ልታላክክ እንደ እንጨቲቱ ልትሰቀልብኝ ስትመጣ አቅሜ እስከቻለ እምቢኝ እላለው ። መቼም ሰው አቅሙ እስከቻለ ነው...።
ዘካርያስ ምህረቱ ወ.በ
2013 ዓ.ም

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

637

obunachilar
Kanal statistikasi