ከደራሲያን እልፍኝ


Kanal geosi va tili: ko‘rsatilmagan, ko‘rsatilmagan
Toifa: ko‘rsatilmagan



Kanal geosi va tili
ko‘rsatilmagan, ko‘rsatilmagan
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


#ያገሬ_መንታ_ገፅ
.
.
ውዷ ባለቤቴ፤
እኔም ወግ ይድረሰኝ፤
ወፍራም ሳግ ይውረሰኝ፤
አባት ልሁናቸው ውለጂልኝ መንታ፣
አንድ ሀገር የሚያድን አንዱ የሚፈታ፣
አንዱ ቤት ሚያፈርስ አንዱ 'ሚሆን ዋልታ፡፡
.
.
እንዲያ ነው እንግዲህ፤
በውላ'ጅ አካልሽ፤
መገፋት ቢተርፍሽ፣
ቢጠልዝሽ ደርሶ አካልሽን ቢያጎነው፣
ከቶ አትገረሚ፤
አንዱ ሲንድሽ ነው "ሌላ"ሽ 'ሚጠግነው፡፡

እናልሽ አለሜ፤
እናልሽ ህመሜ፤
እንዲያ ነው ዘመንሽ እንዲያ ነው ዘመኔ፣
አንቺን ሲነኩሽ ግን ታምሜያለሁ እኔ፡፡


Join & share
👇👇👇👇

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


የነበረበት? የጎንጥን ፊት ሳላስታውስ እንዴት ሽጉጥን ማስታወስ አወቅሁበት? ዋናውን መንገድ ወይም መዳረሻዬን ሳላውቅ እንዴት ኩርባዎቹን አወቅሁ?

አንድ የሆነ ትልቅ ህንፃ ጋር ደርሰን መኪናውን ካቆመ በኋላ ሰባተኛው ወለል ላይ እየመራ አደረሰኝ እና የሆነ በር ከፍተን ገባን። የማያቸውን ነገሮች የማውቃቸው ወይም አዲስ እንዳልሆነብኝ ለማስመሰል የማደርገው ሂደት ምን ያህል ይሳካልኝ አላውቅም! ሁለት ሴቶች ወለሉን እያፀዱ ነው። እዚህም እዚያም ወለሉ መሃል ዘርዘር ብለው የተቀመጡት ጠረጴዛዎች ላይ ወንበሮች ተደፋፍተውባቸዋል። ጥግጥጉን በቀይ ገመድ የታጠሩ ጥቋቁር ሶፋዎች አሉ፣ አንደኛውን ግድግዳ ሙሉ በተለያዩ ጠርሙሶችና ሌሎች ነገሮች የተሞላ መደርደሪያ ሸፍኖታል። ከመደርደሪያው እና ከፊቱ ካለው ከፍ ያለ እግራቸው ረዣዥም ወንበሮች ከተደፋበት መደገፊያ ነገር መሃል ሁለት ወንዶች እየተቀባበሉ ብርጭቆ እያደረቁ ይደረድራሉ። መግባቴን ሲያዩ ሁለቱ ወንዶች ስራቸውን ትተው ቆሙ። አንደኛው ወገቡጋ የሚደርሰውን መደገፊያ ነገር ዘሎ አጠገቤ ደረሰ።

«ውይ ሜሉዬ እንኳን እግዚአብሄር ለዚህ አበቃሽ! » ጭንቅ አድርጎ እያቀፈኝ በጆሮዬ እንደማንሾካሾክ ነገር «ቤቱ በአፍ ጢሙ ተደፍቶ ስራ አጥ ከመሆኔ በፊት ለጥቂት ነው የደረሽልኝ» ብሎ ለቀቀኝ። ፈገግ ብቻ አልኩ። የበፊቷ ሜላት እንዲህ ያለ አስጨናቂ መታቀፍ ሲደርስባት በጥፊ ትለፈው በፈገግታ መገመት ባልችልም……. እየተቀባበሉ እንኳን ደህና መጣሽ ይበሉኝ እንጂ መጀመሪያ ካቀፈኝ ሰው ውጪ የጨበጠኝም ያቀፈኝም የለም። ልክ እንደሚያውቅ ሰው የሽንት ቤት ምልክት ከሚታይበት ተቃራኒ ያለውን ቀጣዩን በር አልፌ ወደ ውስጥ ገባሁ። ሰፊ ኮሪደር እና የተለያዩ ክፍሎች አሉ። እያንዳንዱ ክፍል ውስጥ ሶፋ እና መሃሉ ላይ የብረት ዘንግ ያለበት ከፍ ያለ በቆዳ የተለበጠ ክብ አልጋ መሳይ ነገር አለ። የመጨረሻውን ክፍል ከፍቼ ስገባ አንዲት ቢነኳት ቆዳዋ ተሰርጉዶ የሚቀር የምትመስል ቆንጅዬ ወጣት በፓንት እና በጡት ማስያዣ እዛው አልጋ መሳዩ ቦታ ላይ ተኝታለች። በሩን ከፍቼ ስገባ ብንን ብላ ነቃች እና እንደመደንገጥ ብላ

«ማታ በጣም ዝዬ ስለነበር እዛ ድረስ ከምሄድ ብዬ እዚሁ ተኝቼ ነውኮ! እ? አሁኑኑ ተጣጥቤ ፏ እላለሁ። ይቅርታ በጣም» እያለች ተለማመጠችኝ። ለምን ይቅርታ እንደጠየቀችኝም፤ ስራዋ ምን እንደሆነም፤ ለምን እርቃኗን እንዳለችም ……. ምኑም በእርግጠኝነት ስላልገባኝ በአጠገቤ አልፋ ልትወጣ ስትል ትከሻዋን በአይዞሽ ዓይነት መታ መታ አደረግኳት። ልምምጧ ያሳዝናል። እንዴት ባሳቅቃት ነው ይህችን የመሰለች ልጅ ስታየኝ እንዲህ የምትርመጠመጠው?

እንደገባኝ ከሆነ እቤቱ ውስጥ የሚከወነውን ለማየት ሲመሽ መምጣት አለብኝ። ስር ስሬ ሲከተለኝ የነበረው ዳዊት ወደ ቤት እየመለሰኝ አስብ የነበረው ……. ስንት ዓይነት ሰው ነኝ? ወይም ነበርኩ የሚለውን ነበር። አንደኛው መጥቶ የሚጠመጠምብኝ፣ ሌላኛዋ ስታየኝ ሽንቷ ሊያመልጣት የሚዳዳ ፣ ለዳዊት የሚፈራን ግን የእኔ ፍቅር የሚለኝ …….. አባ እንደልጃቸው ፀጉሬን የሚደባብሱኝ ፣ ጎረቤቶቼ የሚጠሉኝ ፣ ጎንጥ እና ተናኜም ቢሆኑ እንደክፉ ሴት የሚያዩኝ …….. ትክክለኛዋ ሜላት የትኛዋ ነበርኩ? ወይስ ሁሉንም ነኝ? ለማናቸው ነው ትክክለኛ ማንነቴን የገለፅኩት? ለማናቸውስ ነው ያስመሰልኩት? ዝም ብዬ ሳስበው ለምሳሌ ልጅ ቢኖረኝ ፍቅረኛዬ ወይ ባሌ በሚያውቀኝ መልኩ ሊያውቀኝ አይችልም። ምናልባት ባስታውሰው ወላጆቼም ጓደኞቼ በሚያውቁኝ መንገድ አያውቁኝም። የምወደው ጓደኛ ኖሮኝ ቢያውቅ ለእሷ የምሆነውን መሆን ቅድም ብርጭቆ ሲያፀዳ ለነበረው ልጅ አልሆንም። ምናልባት እያስመሰልኩ አይደል ይሆናል። እኔ እንደልጅ፣ እኔ እንደሚስት፣ እኔ እንደጓደኛ፣ እኔው እንደእናት፣ እኔው እንደአለቃ …… እንደብዙ ነገር እንደብዙ የምኖር የእነዚህ ሁሉ ስብጥሮች እሆን ይሆናል።

በር ላይ አድርሶኝ ስንሰነባበት ከንፈሬን ሊስመኝ ሲጠጋኝ ሳላስበው ገፋሁት። ካደረግኩት በኋላ እሱ ፊት ላይ የነበረው ምላሽ እንድፀፀት አደረገኝ።

«ይቅርታ ጥሩ ስሜት ላይ ስላልሆንኩ ነው!»
«እረዳሻለሁ የኔ ፍቅር!» ብሎ ወደመኪናው ገባ!

እቤት ከገባሁ በኋላ ቅድም አስቀምጬው የነበረውን ስልክ መበርበር ጀመርኩ። ብቻ የሆነ ፍንጭ! የሆነ መረጃ! ያልነካሁት ያልፈተሽኩት ምልክት የለም። ከፎቶዎቹ ውጪ ለኪዳን የተጠጋጋ ስምም ሆነ መልእክት የለም። ሌሎች የማላውቃቸው ሰዎች ብቻቸውንም አንዳንዱ ከእኔ ጋር ፎቶ አይቻለሁ። የሆነ ነገር ካስታወስኩ ብዬ ፎቶዎቹን እየደጋገምኩ ባይም ጠብ የሚል ነገር የለም። እናቴ ልትሆን ትችላለች ብዬ የጠረጠርኳት አንዲት ሴት ጋር ተደጋጋሚ ፎቶ አለን። አልጋ ላይ ተኝታ አጠገቧ ተጋድሜ፣ አልጋ ላይ ተኝታ ጉሉኮስ ተሰክቶላት አልጋዋ አጠገብ ተንበርክኬ፣ የሆነ በረንዳ ላይ የሚመስል ቦታ ምግብ እየበላን ፣ ደግሞ ብቻዋን ፈገግ ብላ ……… አንዳቸውም የት ላገኛት እንደምችል መላ አልሰጡኝም።

«እትይ ይሄ መኪና ለምን ጋራዥ አይገባም? በታክሲ ከሚመላለሱም ሰው ከሚያስቸግሩም ይሻልዎታል!» አለኝ ጎንጥ አመሻሽ ላይ ብቅ ብሎ አንድ ጎኗ የተጋጨ እና የጥይት ብስ ያለባት መኪናዬ ወደቆመችበት አቅጣጫ በአገጩ እየጠቆመ።

«ማን ሊነዳው?»
«እሷ ትሰራና መንዳቱስ አይጠፋዎትም! ካልሆነም …… ብሎ አቅማማ
«መኪና መንዳት ትችላለህ እንዴ?» አልኩት ደገፍ ብዬ ከተቀመጥኩበት እየሰገግኩ
« እንዲያ ነገር! ለአንዱ ዲታ ሹፌር ሆኜ 7 ዓመት ሾፍሬያለሁ።» አለ በማጣጣል አይነት።
«ታዲያ ለምን አልነገርከኝም እስከዛሬ? ደግሞ አንቱ አትበለኝ አላልኩህም?»
«አይ እትይ አፌ አይለምድልኝም አንች ማለቱን! ልምድ እንዲህ መች ቶሎ ይለቃል?»
«ሞክረው! መኪናዋን ነገ ውሰዳት ጋራዥ እኔ በታክሲ ደርሼ እመጣለሁ።» ካልኩት በኋላ ነው ስለቤቱ ያየሁትንም ያሰብኩትንም እንዳልነገርኩት ያስታወስኩት።

«እንዲህ ከመሸ ወዲያ መሄድ ደግ ነው ታዲያ? ወይ ልከተሎት!» ብሎ ይተገትገኝ ጀመር። «እትይ ዘንግተውት እንጂ ብዙ ጠላት ያሎት ሰው ኖት!» አሁንም ትንሽ ይቆይና «ባይሆን ከደጅ እጠብቆታለሁ! መንገዱን ላካሂዶት!»
«አንቱ አትበለኝ አልኩህኮ!»
«ይሁን እሺ እኔ ምኑም አላማረኝ እትይ!»
«እህእ!»
«ኸረግ እትይ እንዳትለኝማ አይበሉኝ!»

ባያሳምነውም ታክሲ ጠርቶ ሸኘኝ። የህንፃውን ስም ስነግረው ባለታክሲው አወቀው። እየሄድን የሆነ ጭር ያለ መንገድ ላይ የሆነ መኪና መጥቶ መንገድ ዘጋብን። ባለታክሲው እየተሳደበ መኪናውን አቆመ። ከቆመው መኪና ውስጥ ሁለት የገዛዘፍ ወንዶች ወርደው ደረታቸውን አሳብጠው እየተራመዱ ወደእኛ ቀረቡ!!

....................ይቀጥላል.........

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


የመኖር አካፋይ የመሞት ሲሶ መንገድ መሃል........
🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟

(ሜሪ ፈለቀ)

ክፍል 7

በር በሩን እያየሁ ቆይቼ መጣ! አራት ጊዜ ባጥፈው ያለምንም መጣበብ ሰፋፊዎቹ ጅንስ ሱሪዎቼ ጎን ኪስ መሰስ ብሎ ጥልቅ የሚል፣ ቀጭን ለመባል ራሱ መወፈር ስጋ መጨመር ያለበት ፣ አጭር ቀይ……….. ስጋም ቀልብም የራቀው የሆነ ጥላ ቢስ ነገር ነው። አሁን ከዚህ ጋር ምን ይደረጋል? መቼም ወንድ ነው ብዬ ከስር ሆኜ አልተደረግኩለትም አይደል?! ከላይ ብሆንበት ከእጥረቱ ከቅጥነቱ ፈሱ ነው የሚያመልጠው ነውኮ የሚመስለው። ኸረ እንደው በፈጣሪ ምኑ ደስ ብሎኝ ይሆን አብሬው የነበርኩት? ምናልባት ሌላ በፍቅር የሚፈልገኝ ወንድ ጠፋቶ ምርጫ አጥቼ ይሆናል።

ዓይኖቹ የሌባ ዓይኖች ናቸው…….. ቅብዝብዝ የሚሉ ከይሲ ዓይኖች……. ሲያወራ ሁሉም የሰውነቱ አካል ይሳተፋል። በእግሮቹ ጥፍር እንደመቆም፣ ጫማውን መሬቱ ላይ እንደመሳብ፣ ጉልበት እና ጉልበቱን እንደማጋጨት፣ ከወገቡም ሰበርበር እንደማለት፣ የእጁቹን ጣቶች እንደማፍተልተል ነገር ፣ መዳፍ እና መዳፉን እንደማሻሸት፣ ትከሻውን እንደመስበቅ፣ አንገቱን ከወሬው ስልት ጋር እንደመወዝወዝ ፣ ከንፈሩን እንደመንከስ፣ አፍንጫውን እንደመንፋት፣ ዓይኖቹ ከወዲያ ወዲህ እንደመቅበዝበዝ፣ በቄንጥ ያበጠረው ሉጫ ፀጉሩ እንደመንቀጥቀጥ…………. ብቻ ከወሬው ጋር የማይሾር አካል የለውም።

ምንም ከማላስታውሰው ከእኔ በላይ እሱ ግራ ገባው! እንደመነካካካት እንደማቀፍ እንደመሳም ሁሉንም ቅጥ በሌለው ሁኔታ ለኮፍ ለኮፍ አድርጎ ከወነ። አንድ ነገር በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል። ይፈራኛል! እንዲህ አገጩ እስኪዝረበረብ እየፈራኝ ምን ሆኖ ነው «የእኔ ፍቅር » የሚለኝ? አስገድጄው ወይ በቦክስ አላግቼው ይሆን እንዴ ፍቅረኛዬ ያደረግኩት? ጎንጥ ባያስጠነቅቀኝ ምንም እንደማላስታውስ ነግሬው ምን ሲሆን አብሮኝ እንደሆነ ባወቅኩ! ………

«በቀናችን ስትቀሪ እና ስልክ ሳታነሺ ስትቀሪ መጀመሪያ ያው break ፈልገሽ መስሎኝ ነበር። በኋላ ስታመሪ ግራ ገባኝ! በዛ ላይ ስልክሽ ዝግ ሲሆን በቃ ከአንዱ ተጣልታ አንዱ ሸቤ ናት ብዬ አስቤ ሳጣራ መታመምሽን ሰማሁ! ማለቴ መመታትሽን! ያው መጥቼ እንዳልጠይቅሽ ያው አንቺ ነሽ!» ያሄን ሁሉ የሚያወራው እዛው ደጅ እንደቆመ ነው። ጎንጥ እንዳልወደደው ያስታውቃል። በአይኑ ቂጥ በጥርጣሬ እና ባለመደሰት ሲያየው ቆይቶ እኔ ወደ ቤት እንዲገባ ስጋብዘው እሱ ደጅ ቀረ። ‘ያው አንቺ ነሽ!’ ማለት ምን ማለት ነው? መጠየቅ አትወጂም ነው? አትፈልጊም ነው? ምን ማለት ነው? ምንም ነገር ብናገር ከትውስታ ነፃ መሆኔን ላቃጥር ስለምችል እኔ ብዙ ዝም ማለት መረጥኩ። ያለማቋረጥ ከለፈለፈው ብዙ ነገር ገጣጥሜ የተረዳሁት እኔ እና እሱ የምንጋራው ምን እንደሆነ በግልፅ ያላወቅኩት ንግድ ቤት አለን። ስለመጠጥ፣ ሙዚቃ እና ሴቶች የሆነ የሆነ ነገር አውርቷል። ……ብቻ በወሬው መሃል ጣል ጣል ካደረገው የሚያያዝ ነገር በመነሳት ለመገመት ብሞክርም ከስልኬ ካገኘሁት መልእክት ጋር ተደምሮ ብዙ አልገባኝም። ፖሊሶች ለድንገተኛ ፍተሻ የሚመጡት ምን ዓይነት ንግድ ቢሆን ነው?

«….. ብቻ ብዙ ነገር በአንድ ወር ተመሳቅሏል። ያ ሾካካ ደግሞ ገንዘብ አልተሰጠኝም ብሎ ሊያስፈራራኝ አልዳዳው መሰለሽ? ቃልኪዳን በጣም ስለጠገበች አባርሪያታለሁ። በወሬ አላድክምሽ ስትመለሺ ሁሉንም ትደርሺበት የለ! ይልቅ አንቺ እንዴት ነሽ? የመታሽ ሰው ማንነት ታወቀ? …… »

«ዛሬውኑ መመለስ እፈልጋለሁ። ለምን አሁኑኑ አብሬህ ሄጄ ፊቴን አሳይቼ አልመለስም?» አልኩኝ ሄጄ የምገባው ምን ውስጥ እንደሆነ ባላውቅም ማወቅ እያጓጓኝ

«አሁን ይሻላል? የምልሽ አሁን ምን እንሰራለን ወይ አንደኛሽን በኋላ ሁሉም ሲገቡ ብትመጪ አይሻልም?» ፊቱ ላይ ግራ የመጋባት እና ጥርጣሬ ነገር ነገሰ። የሆነ ነገር እንደተሳሳትኩ ገባኝ

«ይሁን ሁሉም ባይኖሩም ቤቱ ያለበትን ሁኔታ ቃኘት አድርጌ እመለሳለሁ።» አልኩኝ እሱ ሲያወራ «ቤቱ» እያለ ሲያወራ ከሰማሁት ኮርጄ

«ካልሽ እሺ! ወስጄ እመልስሻለሁ!» አለኝ የሆነ ያልተዋጠለት ነገር እንዳለ እያስታወቀበት።

መኝታ ቤት ገብቼ ተናኜን ጠራኋት እና በፊት እንደምለብሰው አለባበስ ልብስ መርጣ እንድትሰጠኝ አደረግኩ። ምንድነው ብዬ ነው ይሆን እንደዚህ እለብስ የነበረው? መለወጤን ለማንም በቃልም በተግባርም ማሳየት ስላልነበረብኝ ያወጣችልኝን ልብሶች ለባብሼ ከዳዊት ጋር ለመሄድ ተነሳሁ።

«እትይ አንዴ ለብቻዎ ላናግሮት?» አለኝ ጎንጥ ወደ ውጪ ብቅ ስንል። ወደጓሮ ዘወር ብለን ድምፁን ዝግ አድርጎ በሹክሹክታ
«ይቅርታ ያድርጉልኝ እትይ ከዚህ ሰውዬ ጋር ብቻዎትን መሄድዎን አልወደድኩትም። የት እንደሚሄዱስ ያውቃሉ? ልከተልዎት!» አለ ፍርጥም ብሎ

«ግድ የለህም ጎንጥ ምንም አልሆንም! እስከመቼ እንደህፃን ልጅ ትጠብቀኛለህ? የከፋ ነገር እንኳን ቢመጣ ምንም የበፊቷን ሜላት መሆን ባልችል ይሄን አንድ ጭብጥ ሰውዬ መገንበር ያቅተኛል? » ስለው ፈገግ ነገር ብሎ

«ብቻውን ከሆነስ ቆርጥመው ይበሉታል። የት እንደሚወስድዎ ነው ያሳሰበኝ።»
«ግድ የለህም አጠራጣሪ እና ሰው የሌለበት ቦታ ከሆነ እጠነቀቃለሁ።»
«ግድ የሎትም ልከተልዎት?»
«ግድ የለህም ይሄን ብቻዬን ልወጣው! ይልቅ አንቱ የምትለኝን ነገር ተው!»


እንደጠበቅኩትም መኪናውን እየነዳ ያለማቋረጥ እየለፈለፈ ፣ እንዳልጠበቅኩትም አልፎ አልፎ አንድ እጁን እየሰደደ ወይ ትከሻዬን አልያም ጭኔን እንደመዳበስ እያደረገኝ (በጣም ደስ የማይል ስሜት አለው። በተለይ ጭኔ ላይ እጁን ሲያሳርፍ! መጀመሪያ ሲነካኝ ከመቀመጫዬ እንደመዝለልም አድርጎኝ ነበር። ) መንገዱን ተያያዝነው። የምንሄድበትን መንገድ በጭንቅላቴ ለመመዝገብ ፣ የማያቸውን ፅሁፎች ጭንቅላቴ ውስጥ ለማስቀረት እሞክራለሁ። አንዳንዶቹን በትልልቅ የተፃፉ ጽሁፎች የማውቃቸው የማውቃቸው ይመስለኛል። ይመስለኛል እንጂ ከምስሉ ተያይዞ የማስታውሰው ነገር የለም። ይሄ በጣም የሚያስጨንቅ ስሜት አለው። ትውስታ ይሆን ጭንቅላቴ የሚፈጥረው ስሜት ይሆን አለመለየት ፣ የቱ የነበረ የቱ አዲስ መሆኑን አለመለየት ከመርሳቱ በላይ ጭንቅላት ይወጥራል። ለምሳሌ መንገዱን አላውቀውም ነገር ግን መታጠፊያ ጋር ስንደርስ በዛ መታጠፊያ እንደሚታጠፍ ገምቼ ይሁን አውቄ አላውቅም። ግን ልክ መኪናውን እየነዳሁ ያለሁት እኔ ብሆን ልክ እዛ መታጠፊያ ጋር ስደርስ ማንም ሳይነግረኝ መሪውን የማዞር ይመስለኛል። ከትውስታዬ ማህደር ከሆነ መንገዱን ሳላውቀው እንዴት መታጠፊያዎቹን ብቻ አስታውሳለሁ? የሆነ ቀን ለክትትል ሀኪም ቤት ስሄድ ለሀኪሙ የሚሰማኝን መቀዣበር ስነግረው «በህይወትሽ ውስጥ በተደጋጋሚ ታደርጊያቸው የነበሩትን ነገሮች በደመነፍስ ሰውነትሽ ሲያደርጋቸው ልታገኚ ትችያለሽ። ሳታውቂው ታዘወትሪበት የነበረ ቦታ መገኘት፣ ቋንቋ ድንገት ሰዎች ሲያወሩ መረዳት ወይ መንገር ፣ በፊት ትወጃቸው ከነበሩ ነገሮች ጋር መቆራኘት፣ ትጠያቸው የነበሩ ነገሮችን መጥላት ……..የመሳሰሉ ነገሮች የሚከሰቱ ናቸው። ከነገሮች ጋር ተያይዞ ጭንቅላትሽ የሚከስተው ምስል ካለ ግን ያ የትውስታሽ አካል ነው። ምናልባት እቦታው ላይ ብትገኚ ክስተቱን የማስታወስ እድልሽ ሰፊ ሊሆን ይችላል።» ብሎኝ ነበር። በእርግጥ የአዕምሮ ክፍላችንን የሚያሳይ ምስል አስቀምጦ ብዙ የተወሳሰበ ነገር ሊያስረዳኝ ሞክሯል። አልገቡኝም እንጂ! ቤተ ክርስቲያን ሄጄ እቀመጥበት ከነበረበት ቦታ እና ከወንድሜ መልክ የቱ ነበር ለስሜቴ መቅረብ


"የመፃተኛው ኑዛዜ"
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ካገር ጫፍ እስከ ጫፍ በጥላህ ከልለህ
ተራራው የኔ ነው ለምን ትለኛለህ?
ወንዙ ድርሻዬ ነው ለምን ትለኛለህ?
እንኳንስ መሬቱ አንተም ያ'ንተ አይደለህ፡፡
:
እኔ መፃተኛ አንተ ኗሪ ነኝ ባይ
እኔ እግሬን ስከተል ርስትህን ስታይ
ስቀርብህ ገፋሀኝ ስትገፋኝ ቦታ አጣሁ
ድንኳን ብትተክል፤ ነፋስ ሆኜ መጣሁ፡፡
:
ያ'ባትህ ያ'ባቴ
ጠበኛ ስማቸው
ጠበኛ ህልማቸው
በህይወት ተጣሉ ፤ ታረቁ ባፅማቸው
ባ'ፈር ተቃቃሩ አፈሩ አስማማቸው
በዙሪያቸው በቅሎ ከቧቸው ሞት ደኑ
መተቃቀፍ መርጠው ማማና ወይን ሆኑ፡፡
:
ይችላል ይሉሀል ፍልሚያ ማዘጋጀት
ያ'ባት አጥንት ወስዶ ስሎ ጦር ማበጀት
አንተው ጦር ወርውረህ አንተው ቀድመህ ወደቅህ
አካሌ ደረቴ መሆንህን መች አወቅህ?!
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
((በዕውቀቱ ስዪም))

Share and join
👇👇👇

👆👆👆ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


የለህማ

ደሞ ደሞ
ነገር ጠሞ
ከግጥምጥም...ክፉ ተርታ
የቋጠርኩት...እስኪፈታ
ወንድነቴ...እስኪረታ
ትንሽ ያልኩት...እስኪንቀኝ
ያቀረብኩት...እስኪርቀኝ
አማረ ያልኩት...ቢያሳቅቀኝ
የሞላሁት...ቢጎዳድል
የታገልኩት...ቢያረገኝ ድል
ቀን ቢያጎርሰኝ...ክፉን ዕድል

ቀና ብዬ ወደሰማይ
          ሽቅብ ሽቅብ አየሁና፤
በታከተው
ሆድ በባሰው፥በቸኮለ፥ ባዶ ህሊና፤
እግዜርን አልኩ
              የ.ለ.ህ.ማ...!

አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)



ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


ምን አገራረፈን?

ዘመን ፈልፍሎብህ፥
ጅራፍ የጨበጠ፥ ክፉ ተጣማሪ
በተቀኘኸው ልክ፥ ገዳይና ማሪ
መቀበል ያስጠቃል፥ አቀብል አዝማሪ።
..........አቀብል...እንካማ...
.....||ዐይን ሰርግ ሊሄድ፡ ሲኳኳል ቆቡ ስር
.....ማን ይየው የታቹን?
.....ደምቶ ማለቁ ነው፡ አፍንጫ በነስር።||
የሚያዘንቡብህን፥
ስንኞች ወጥረህ፥ በማሲንቆህ ቆዳ
የሚቀዱብህን ፥ አዙረህ ብትቀዳ
ጥያቄ እንደፈራ፥ ሰነፍ አስተማሪ
ምላሹ ጅራፍ ነው፥
አትቀበል ተወው፥ አቀብል አዝማሪ።
............አቀብል... እንካማ
.....||እንደአረፋ ሙክት፡ ልክ እንደዒድ በሬ
.....ሰርክ የሚያሳርደኝ፡ አለመሶበሬ||
የመንደሩ ወግ ነው ፥
ግንድ እየደበቁ፥ ንፋስ መማገሩ
አቀባይ እጅ እንጂ፥
ተሸካሚ ጀርባ፥ የለውም ሀገሩ
ብልጥ...ሁን ... እባክህ
ገንዘብ እንደሌለው አራዳ ቆማሪ
ሳትሰጥ ሳትቀበል፥
አየር ባየር ብላ፥ አቀብል አዝማሪ
............አቀብል... እንካማ
....« በሳቅ መፍረስ የሚል ፡ ፈሊጥስ ነበረን
..... ፈርሶ መሳቅ ደሞ፡ ማነው ያስተማረን?»

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


የፍቅራችን ቅኔ

በፍቅር ሰሌዳ በመዋደድ ቅኔ፣
የኔ ልብ ባንተ ያንተም ልብ በኔ።
የነፍስያችን ወግ ካሳባችን ሰርፆ፣
በልባችን ሀዉልት ፍቅራችን ተቀርፆ።
ደምህና ደሜ ፍፁም ተዋህዶ፣
ባንደበት ሊገለፅ በቃላት ተጋምዶ።
ቀና ብለህ እያት ዉቢቷን ጨረቃ፣
የብርሃን ዝናር በወገቧ ታጥቃ።
ተስፋ ልታድል ጽልመት ለጋረደዉ፣
በትዝታ ጋሪ ሞሽራ ልትሸኘዉ።
ያቺ ዉብ ጨረቃ ምስክር ትሁንህ፣
በሷ ብርሃን የኔ መልክ ይታይህ።
ከዋክብትን ስታይ ከደጃፉ ቆመህ፣
በአንተ ብርሃን ድምቀቴ ይታወስህ።
የኔና አንተ ፍቅር በወርቅ ይመሰላል፣
ካፈር ተደባልቆ ከሳት ይፈተናል።
ከጭቃዉ ይጠራል ነበልባሉን አልፎ፣
ከነፍስ ተራቆ ከህሊና ገዝፎ


@ediw ub

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


የጉሽ ጠላን እና
ያንቺን እምቡጥ ከንፈር
ምን አገናኛቸው ?
የቀመሱት ሁሉ እኩል መስከራቸው?
አዪ....

የጠላውስ ይሁን
ጌሾ ነው ቅጠሉ
በከንፈር አይከብድም ሰካራም መባሉ?

.
.

በሚኪያስ ፈይሳ

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


​​መካድ ያመነጨው እርግማን
°°°°°°°°°°°°°

ወደድኩህ ስትይኝ
ሰጥቼሽ አልነበር ክቡር ድንግል ልቤን፣
በፍቅር አስክረሽ እስክነጠቅ ቀልቤን?

አፈቀርኩህ ስትይ
በገላሽ ልገድፍ ሁዳዴን ጾም ጥሼ፣
አልተጋደምኩም ወይ እምነት ተንተርሼ?

ግን ምን ዋጋ አለው
አንፍሰሽ ጥለሽው መውደዴን በወንፊት፣
ተጀቡነሽ አየው የማስመሰል ቅርፊት።
ደሞ አለማፈርሽ
በማጣት ገደል ስር ገፍተሽኝ ለመሄድ፣
ሾርበሽ ቆየሽኝ
አትወደኝም የሚል ሀሰት ለበስ ገመድ።
ጠንቅቀሽ እወቂ
የማፍቀርን ሚዛን ተፈቃሪ አይለካም፣
መቀበልን ሚሻ በመስጠት አይረካም።

ተቀበይ!!
:
አንጥፌልሽ ሳለ የገላዬን ምንጣፍ፣
ንቀሽ ስለተኛሽ በክህደት መዳፍ፤
ሕመም እንድትዘግኚ!
ስቃይ እንድትቀምሺ!
በንዴት ካረረው ጥቀርሻ ልቤ ላይ፣
ነድዬ አዘንባለሁ የ'ርግማኔን ቀላይ።

እነሆ በስብሺ!!
:
እምነቴን ተርትረሽ ለእጦት የዳርሽኝ፣
ዐይንሽ ብርሃን ይመኝ አይማርሽ ወረርሽኝ!!
ተስፋዬን ቦጫጭቀሽ የጣድሽኝ ለጽልመት፣
መርጋት አምሮሽ ይቅር ያንከልክልሽ ክህደት!!
ፍቅሬን አመናጭቀሽ ምሬት የጋበዝሽው፣
ኑሮ ኮሶ ያጥባሽ ይጥላሽ የወደድሽው!!
የኔን ሕመም ሁሉ በተራሽ ቅመሽው!!

#ኤልዳን



ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


አልሞትም ብዬ እንጂ፡
ክንዴን አልንተራስ፣
ከጦር የቀጠነ ፥ የሳሳ ከምላስ፡
ብዙ ብዙ ብዙ ፥ ሊገለኝ የሚሻ፡
ጉዳይ መቼ ጠፋ ፡ የስቃይ ማረሻ፤

አቡ(አላዛር ቴዎድሮስ)


ከ ወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


የት ነበርሽ ??
፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤፤

ህይወት ወጀብ
አገላብጣኝ ስብከነከን
ቀን ሲከፋ
ኢምንት በደል በኔ ሲገን
አካል ልቤ
ሰው ሰው ሰው ሲል
ናፍቆ ሲደብን...ባዛኝ አይኔ
ሺ ቢፈልግ ቢንከራተት
አጥቶሽ ነበር....
ግና ዛሬ ጭጋግ ያልኩት ድባብ ሲሸሽ
ኦና ቤቴ በሰው አጀብ
ሲምነሸነሽ
ዳግም ስቄ ፊቴ ፈክቶ ስውል ሳመሽ
ከደጃፌ ከበራፌ
አየው ቆመሽ..አዪዪዪ
ግድ የለውም
ጊቢ አለሜ ከትላንቱ የተረፈ ቅንጣት ፍቅር
በጥያቄ ተለውሶ
ከልቤ አለሽ..እስቲ አጫውችኝ
እንዲያ ስሆን ስፈልግሽ ወዴት ነበርሽ ?
:
በአንዱ ጉያ ክንድ ታቅፈሽ
ውብ ደረቱን ተደግፈሽ
ደጃች ውቤ ከሞቀው ቤት
እየደነስሽ...?

ወይስ ከሰው ተከልለሽ
ጭንቄን ላታይ በሳግ በዕምባ እየታጠብሽ
ከአራዳ ሰማዕቱ ደጅ
እየጸለይሽ...?

ወዴት ነበርሽ ?

/ ኪዮርና /


ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


#ተሳስተሻል
:
:
ሻማ ስትለኩሺ ኬክም ስትቆርሺ ላየሽ ሰው በሙሉ፣
የምጓጓለት ቀን ልደቴ ነው ዛሬ እያልሽ ነው አሉ።
:
:
እውነት ነው ወይ ውዴ እንደዚያ ብለሻል?
የሰማሁት ነገር ትክክል ከሆነ በጣም ተሳስተሻል።
:
:
ምክንያቱም ውዴ
እንደ ሾላ ጥላ እንዲያ ተንዠርግጎ ሀዘን በኔ አጥልቶ፣
ፍቅርን ተርቦ እኔነቴ ዳምኖ ልቤ በቁም ሞቶ፣
በሁሉም አቅጣጫ ከቦኝ ባለ ጊዜ ዕፀፅ በበረሀ፣
ነብስ የዘራሁትኝ ጠጥቼ አይደለም ወይ ከልብሽ ምንጭ ላይ የህይወትን ውሀ።
:
:
መውደድን ተርቦ ባለም ላይ ሲዳክር ለነበረው ልቤ፣
ዕፁብ የሆነውን የልብሽን ፍቅር ለልቤ መግቤ፣
ደመነፍሴን ሆኜ ትላንት እንዳላደርኩ ተስፋ ባጣ ግርጌ፣
ታውቂ የለም እንዴ ዳግም ሰው እንደሆንኩ ትንፋሽሽን ምጌ።
:
:
በውሀ ላይ ስሮጥ አንዳች ለማልጨምር ሁሌም ሆኜ እዛው፣
ላላተርፍ ነገር ጉልበቴን ስጨርስ ድካሜን ሳበዛው፣
ያለምንም ስስት ኑሮዬ እንዲሰልጥ ህይወቴ እንዲቀና፣
አንቺ አይደለሽ እንዴ ደርሰሽ ያሳየሺኝ የፍቅርን ጎዳና።
:
:
እውነት ለመናገር ብሶት እየጫረች ዐለም በፍዳዋ ደርሳ እንዳትማግደኝ፣
በዚች ቅድስት ዕለት ያንቺ መወለድ ነው ዳግም እንደገና እኔን የወለደኝ።
:
:
ውሉ ጠፍቶት ልቤን ህይወት በኔ ሲከር፣
አንቺን ባላገኝሽ ማን ይወልደኝ ነበር።
:
:
እናልሽ እንቁዬ
ገና ከጅምሩ ልደቴ ነው ዛሬ ማለትሽን ስሰማ፣
ተሳስተሻል ያልኩት ምንም ሳላቅማማ፣
ባንቺ መወለድ ውስጥ ዳግም እንደገና እኔ መወለዴን፣
መዘንጋትሽን ሳውቅ ቢቆርጠኝ ነው ሆዴን።
:
:
እናም ካሁን ወዲ
ይህን ቀን ለማክበር ሽር ጉድ ስትዪ፣
ከሁሉ አስቀድመሽ ይህቺን አስተውዪ።
:
:
በፍቅርሽ እስትንፋስ በተቸረሽ ጥበብ በትንሳዬሽ ጉልበት፣
ባንቺ መወለድ ውስጥ ዳግም እንደገና ስለተወለድኩኝ ሞቼ ካለሁበት፣
ዛሬ ቀን ምንድነው ብሎ ለጠየቀሽ እንዲ ብለሽ አስረጂ፣
ልደቴ ነው አትበዪ ያንቺ ብቻ አይደለም ልደታችን እንጂ።

#ሄኖክ_ብርሃኑ


ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


አንድ ቀን ሲከብደኝ
ካባቴ መቃብር ፊትለፊት አነባው
በደረቀ እምባዬ ከሃዘን መዝገብ ገባው
የውስጡን መዘርገፍ
በድን ሰው መወንጀል ምላሴን ሲቃጣው
ቁልቁል አቀርቅሬ  አንዲት ቃል አወጣው
"ያላንተ እንደማይጥም ሀቁን እያወከው
እንዴት አፈር ገባህ  እንዴት ሞትን ቻልከው?"
ብዬ ሳላማርር
ከመቃብር ስፍራ ሰማሁኝ አንድ ቃል
"እየኖርክ አይደለ 
መሞት ምን ይደንቃል?"

By mikiyas_feyisa

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!


እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


' እመቤት ነኝ ሜሉ ያለፈውን ሳምንት ስትቀሪ ባይመችሽ ነው ብዬ አለፍኩ ይሄንን ሳምንት ስትቀሪ ግን አሳሰብሽኝ። በሰላም ነው?' ........ሌላ ደግሞ ዳዊት የሚባል ሰው.........»ካለ በኋላ ድምፁን ዝግ አድርጎ «እትይ ይሄን ራስዎ ቢያነቡት ሳይሻል አይቀርም ብሎ ስልኩን ዘረጋልኝ። እትዬ ነበር የሚለኝ እሱም እንደ ተናኜ እትይ ብሎ መጥራት መጀመሩ ቁልምጫ መሆኑ ነው?
«አንብበው ችግር የለውም ኸረ!» አልኩት እስከዛሬ ከሚያውቀው የባሰ ምን ሊመጣ ይችላል ብዬ እያሰብኩ። መቼም የገዛ ባሌን ፍሬዎች የቲማቲም ወይ የብርቱካን ፍሬ ከዛፉ እንደመቀንጠስ ቀለል አድርጌ ከሰውነቱ ቆርጬ ፖሊስ ጣቢያ ድረስ ከመውሰድ የባሰ ጉዳይ ሊኖር አይችልም!
«አይ እትይ ግድ የልዎትም ራስዎ ያንብቡት!» አለ እያመነታ ስልኩን የዘረጋበት እጁን ሳይመልስ
«ግድ የለህም አንብበው» ስለው እያመነታ
«ካሉ እሺ!» ብሎ እስከዛሬ ያላየሁበት አይነት የማፈር ይሁን የመቅለስለስ ያልገባኝን ፊት እያሳየኝ ማንበብ ጀመረ። « የእኔ ፍቅር ስደውልልሽ አታነሺም ስትመጪ የምንጠጣውን እንዳትረሺ! በጣም ቆየሽኮ ፍቅር በሰላም ነው ስልክ የማታነሺው? ....... »
«እሺ እሱን ተወው እና ሌላ አንብብ ኪዳን የሚል መልእክት የለም?» አልኩት እኔም እንደማፈር እያደረገኝ። ፍቅረኛ ነበረኝ? ቢያንስ የእኔ ፍቅር የሚለኝ ሰው ነበረ።
«እኮ!» ብሎ ጣቱን ወደላይ እና ወደ ታች ኪዳንን ፍለጋ ይፈትለው ጀመር። «አይ እትይ ኪዳን የሚል የለም! ምናልባት በሌላ ስም ይሆናል የመዘገቡት! ስም መዝገቡም ውስጥ ኪዳን የሚል የለም!»
«እሺ እስቲ ሌሎቹን አንብብልኝ እና በሌላ ስምም ከሆነ ከመልእክቱ እንደርስበት ይሆናል።» አልኩኝ።
«ሌላ ያልተመዘገበ ቁጥር አሁንም 'እመቤት ነኝ ሜሉ ያስቀየምኩሽ ነገር አለ እንዴ? በባለፈው ንግግሬ ተቀይመሽኝ ይሆን? ግራ ገባኝኮ! ምንም ውስጥ ሆነሽ ቢያንስ መልእክት ትልኪብኝ ነበር። እንዲህ ጨክነሽብኝ አታውቂም! ብደውልም ስልክሽ አይሰራም። እባክሽ ቢያንስ ደህና መሆንሽን እንኳን አሳውቂኝ!»
«እናቴ ትሆን እንዴ?»
«መደወል እንችል ነበር ግን በሁለት የተለያየ ቁጥር ነው መልእክቱ የተላከው። በየትኛው እንደውል?» አለ ጎንጤ
«ምናልባት የራሷ ስልክ የላትም ይሆናል። አባ ታማለች ብለውኝ የለ? ባለፈው ሳምንት ሳትጠይቂኝ አይደል የሚለው የመጀመሪያው መልእክት?»
«ይሆን ይሆናል። ግን እትይ ለማንኛውም ለጊዜው ማን ምን እንደሆነ እስኪለይ ላገኙት ሁሉ ሰው ምንም እንደማያስታውሱ አይናገሩ! አጋጣሚውን ተጠቅሞ ሊጎዳዎት የሚያስብ ሰው ሊኖር ይችላል።» አለ ሀሳብ እንደገባው ሰው።
«አንደኛው ስልክ ላይ እንደውል!» አልኩኝ። ስልኩ አድምቆ ሶስታችንም በምንሰማው መጠን ሲጠራ ቆይቶ ከወድያኛው ጫፍ ተነሳ እና የወንድ ድምፅ «ሀሎ» አለ። ቀጥሎ የምለው ግራ ገብቶኝ ሳለ ጎንጤ ስልኩን ወደራሱ አስጠግቶ
«ይቅርታ ያድርጉልኝ እና በዚህ ስልክ እመቤትን ማግኘት እችል ይሆን? ሰው መልዕክት ሰዶኝ ነው!» አለ። የሰውየው ድምፅ ያመነታ መሰለ።
«ማነህ አንተ? እመቤትን ለምንድነው የፈለግካት? ማነው የላከህስ?»
«እኔን አያውቁኝም! እንደው እመቤትን ማግኘት ብችል ወይ የማገኝበትን ሌላ ስልክ ቢጠቁሙኝ።»
«ተሳስተሃል። እመቤት የምትባል ሴት በዚህ ስልክ የለችም!» ስልኩ ተዘጋ። መልሶ እየደወለ። «ሲወሸክት ነው! » አለኝ ለእኔ
«እመቤት የምትባል ሴት አላውቅም አልኩህ አይደል?» አለ ሰውየው እየተቆጣ
«እየዋሹ ነው እሎታለሁኝኣ! በዚሁ ስልክ ከእመቤት መልዕክት ተልኮ ነበር። እመቤትን ካላወቋቸው እመቤት ነኝ የሚል መልእክት እንዴት እዚህ ደረሰ?» አለ ጎንጤ ቆፍጠን ብሎ ሰውየው ስልኩን ሲነካካ ድምፁ ይሰማል።
«ማነው ላከኝ ያልከው?» አለ በጥርጣሬ እንደማጣራት
«ሜላት»
«ታዲያ ራሷ ሜላት ለምን አልደወለችም አንተጋ ስልኳ ምን ይሰራል?»
«ለጊዜው እትዬ ሜላት ታመዋል። እንደየትም ብለህ መልእክት አድርስልኝ ብለውኝ ነው!» ሲለው ሰውየው የጠበበው ድምጽ አሰማ።
«እ መልእክቱን ብትነግረኝ እኔ እመቤትን ሳገኛት አደርስልሃለሁ። እመቤት የት እንዳለች ሜላት ነግራሃለች?» አለ አሁንም እንደጨነቀው።
«በፍፁም! በዚህ ስልክ ደውል ብቻ ነው ያሉኝ!»
«ዌል ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ናት!» አባባሉ 'እስቲ መልእክትህን እዛ ሄደህ ታደርስ እንደሆነ እናያለን!' አይነት ነው።
«እባክዎትን ካላስቸገርኩ ደውዬ እንደነበር መልእክት ያድርሱልኝ!» ብሎ ዘጋ ስልኩን። እናቴ ልትሆን አትችልም! እናቴ እስር ቤት ምን ታደርጋለች? ታማ የለ? ጎንጤ ስልኩን ሲበረብር ስልኩ እጁ ላይ ጮኸ
«እትይ ዳዊት እየደወለ ነው!» አለኝ ስልኩ ላይ አንዳች ነገር ያየ ይመስል እያፈጠጠ።
«አንሳዋ!» አልኩት መልሼ እያፈጠጥኩ
«ኸረግ! ተዚያ ምን ልለው?» ብሎ ስልኩን ክፍት አድርጎ ጆሮዬ ላይ ለጥፎልኝ ለተናኜ እንድትወጣ በዓይኑ ምልክት ሰጥቷት እሱም ወጣ!
«ኦህ ማይ ጋድ ፋይናሊ! በሀሳብ ከማለቄ በፊት! ስልክሽ መከፈቱን ቴሌ ማሳወቂያ ሲልክልኝ አይኔን ነበር ማመን ያቃተኝ! ሜሉዬ የኔ ፍቅር! ምን ባደርግሽ ነው እንዲህ የጨከንሽብኝ?» ሀሎ እንኳን ሳልለው ያለማቋረጥ ይለፈልፋል።
«ትንሽ አሞኝ ነበር» አልኩኝ ጎንጤ ያለኝን አስታውሼ
«ኦህ ማይ ጋድ! ታዲያ አትደውዪልኝም ነበር? እሺ አሁን የት ነው ያለሽው? የት ልምጣ? ኦህ አምላኬ? እሺ አሁን እንዴት ነሽ?»
የሚጠይቀኝ እንድመልስለት አይመስልም! የሆነ ልክ ያልሆነ ስሜት እንዲሰማኝ አደረገኝ። እቤት እንዲመጣ ስነግረው የቤቴን አቅጣጫ አልጠየቀኝም!
«ጎንጥ ? ዳዊት የሚባል ሰው እዚህ ቤት መጥቶ ያውቃል? ሆስፒታል እያለሁ መጥቶ ጠይቆህ ከሆነ?» አልኩት ወደበረንዳ ብቅ ብዬ። እኔስ ጎንጤን ተናኜ እንደምትጠራው ጎንጥ ማለቴ ማቆላመጤ ይሆን?
«በፍፁም እትይ!»
በር በሩን እያየሁ ቆይቼ መጣ! አራት ጊዜ ባጥፈው ያለምንም መጣበብ ሰፋፊዎቹ ጅንስ ሱሪዎቼ ጎን ኪስ መሰስ ብሎ ጥልቅ የሚል፣ ቀጭን ለመባል ራሱ መወፈር ያለበት ፣ አጭር ቀይ ስጋም ቀልብ የራቀው የሆነ ጥላ ቢስ ነገር ነው። አሁን ከዚህ ጋር ምን ይደረጋል? መቼም ወንድ ነው ብዬ ከስር ሆኜ አልደረግለትም! ከላይ ብሆንበት ከእጥረቱ ከቅጥነቱ ፈሱ ነው የሚያመልጠው።
....................ይቀጥላል.........
ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩትከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


የመኖር አካፋይ የመሞት ሲሶ መንገድ መሃል........
🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟

(ሜሪ ፈለቀ)

ክፍል 6

«ልጄ ዘመንሽን ሁሉ ክፉ ያደረጉብሽን ሰዎች ለመበቀል ስትዪ ነው የኖርሽው። እንደገባኝ ከሆነ ከበቀል እና ለወንድምሽ ከመኖር ውጪ ሌላ ልምድም ህልምም ስላልነበረሽ የጎዳሽን ሰው ካጠፋሽ በኋላ አንቺ የምትኖሪለት ነገር አጥተሽ ነበር። ልጄ የበደሉሽን ይቅር በይ፣ ራስሽን ይቅር በይ! ለፍቅር በፍቅር ለመኖር ራስሽን አስለምጂ! እግዚአብሄር አዲስን እድል ሰጥቶሻል።» አሉኝ ከጉልበታቸው ላይ ሳልነሳ ብዙ ደቂቃዎች ወይም ሰዓት ካለፈኝ በኋላ

«አባ ለምንድነው ብዙ የሚያውቁት ነገር ያለ ግን ያልነገሩኝ የሚመስለኝ?»

«የማይበጅሽን ብነግርሽ ምን ሊጠቅምሽ ልጄ? ስላሴ ከጭንቅላትሽ ብን አድርጎ ያጠፋው ባይጠቅምሽ አይደል? ወይም ለጊዜው ባያስፈልግሽ? »

«አባ ያለትናንት ዛሬን መኖር ይቻላል? ትናንት የሌለበትስ ዛሬ አለ? እያንዳንዱ ከሰዎች ጋር የሚያያይዘኝ ገመድ ከትናንት ጋር የተጋመደ አይደለም? ቤተሰቦቼም እኮ ትናንቴ ውስጥ የነበሩ ናቸው። እሺ ካልነገሩኝ እናቴን ወይ ወንድሜን እንዴት አገኛቸዋለሁ?»

«የሚጠቅምሽን መረጃ አልደብቅሽም ልጄ። ስለእናትሽ ብዙም አላወራሽኝ ስለወንድምሽ ግን አውርተሽ አትጠግቢም። ስሙን በየእለቱ የምትደጋግሚው ስለሆነ አልዘነጋሁትም። ኪዳን! አዎ ኪዳን ነው።» ጀርባዬ ላይ በትልቁ የተነቀስኩት የወንድሜን ስም ነው ማለት ነው። «ጥይምናው እና ፈገግታው ያንቺው ነው።» ሲሉ ለመጀመሪያ ጊዜ ከጉልበታቸው ቀና አልኩ

«እንዴ አባ ያውቁታል? አብሮኝ መጥቶ ያውቅ ነበር?» አልኩኝ በጉጉት

«እንደዛ አይደለም ልጄ! በስልክሽ ነው ምስሉን ያሳየሽኝ። » ጠይም ሳቂታ .......... የአልጋዬ ኮመዲኖ ላይ ያለው ፎቶ ነው የሚሆነው

ስልኬ! ......... እንዴት እንደምከፍተው ማወቅ አቅቶኝ መሳቢያ ውስጥ ያስቀመጥኩት መስታወቱ የተሰነጣጠቀ ስልኬ! ቀና ብዬ ጎንጤን አየሁት። ከተቀመጥኩበት እየተነሳሁ

«አባ ልሂድ በቃ! ብመጣ አገኝዎታለሁ? »

«አለሁኝ ከቤቱ የት እሄዳለሁ? (ወደ ሰማይ መልከት አደረጉ) በአይንሽ ካጣሽኝ መልከፃድቅን ጥሩልኝ በይ!» የለበስኩትን እያጤኑ «ለምስጋና እንደመጣሽ አምኜ አምላኬን አመሰግናለሁ» አሉኝ። መጨረሻ ላይ የተናገሩት እንዳልገባኝ ገብቷቸው ፈገግ እያሉ። «ሁሌም ስትመጪ ሌጣሽን ያለክንብንብ ደግሞም የክፉ ነገሮች ምስል ያለበት ልብስ ለብሰሽ ነበር። አንድ እለት ከጀርባው ትልቅ የእባብ ምስል ያለበት ጃኬት አድርገሽ 'ምነው ልጄ ከጀርባሽ ፈልገሽው ነው?' ብልሽ። ' ከእግዚአብሄር የታረቅኩ ቀን ለምስጋና ስመጣ ቀሚስ ለብሼ ነጠላ ደርቤ እመጣለሁ።' ብለሽኝ ነበር።» አሉኝ።

እቤት የምደርስበት ሰዓት እርቆብኝ ከደረስኩ በኋላ ከስልኬ ጋር ተፋጥጫለሁ። ጭንቅላቴ ውስጥ ምስላቸው የሌሉ ነገሮችን እንኳን ስይዛቸው በደመነፍስ ምን ማድረግ እንዳለብኝ አውቅ ነበር። ለምንድነው ስልኬን ምን ማድረግ እንዳለብኝ ግራ የገባኝ?

«ባትሪ ያለው አልመሰለኝም! እንዱለው ይሆን?» አለኝ ጎንጤ አለማወቄ ቢገባውም እንዳያሳፍረኝ በመጠንቀቅ ዓይነት። አቀበልኩት። ተቀብሎኝ ግድግዳው ላይ ተሰክቶ ገመዱ የተዝረከረከ ገመድ ብድግ ሲያደርግ የሚቀጥለው ሂደት ጫፉን ስልኩ ላይ መሰካት እንደሆነ አውቃለሁ። የሆነ አለ አይደል ሰው መንገድ ጠፍቶበት ልክ ቤቱን ሲያየው ይኸው እንደሚለው ዓይነት ነገር?

አባ 'እግዚአብሄር ጭንቅላትሽን እንደህፃን ልጅ ነጭ ወረቀት አድርጎ ሰጥቶሻል፣ የሚቀጥለውን ዘመንሽን አስተካክለሽ ፃፊበት' ይበሉኝ እንጂ እንደህፃን ነጭ ወረቀት የሆነ ጭንቅላት እንዳልቀረኝ አውቃለሁ። እንደህፃን እንዴት እንደምበላ ከ 'ሀ' አልጀመርኩም ወይም አፌ አልጠፋብኝም፣ መራመድ ለመቻል ከመዳህ አልጀመርኩም ፣ 'ኡፉ ነው' ባልባልም እሳት እንደሚፋጅ ሳየው አውቄያለሁ፣ ሽንቴን ልብሴ ላይ ይሁን ሽንት ቤት የምሸናው ሳላውቅ እላዬ ላይ አልለቀቅኩም፣ ሱሪ ለመልበስ በአንገቴ አላስገባሁም ወይም ጫማ ለማጥለቅ ግራ አልተጋባሁም፣ አልጋ ሳይ ይሄ መተኛሽ ነው ሳልባል ገልጬ ውስጥ ገብቼ ተኝቻለሁ ፣ የጥርስ ብሩሽ ሳይ ምንም ሳልጠይቅ እጄ አንስቶ ጥርሴን ቦርሿል .........

2. ስልኬ

ስልኬ ለመጀመር የሚያስችለውን ባትሪ ሲያገኝ ራሱ ከፈተ። እስክሪኑ ሲበራ ዘልዬ አጠገቡ ደረስኩ እና አነሳሁት። ያ አልጋዬ አጠገብ ያለው ፎቶ ላይ ያለው ልጅ ዓይኖች ያሉት ፎቶ ይታያል። ራሱ ነው! ኪዳን ነው። ትልቅ ሰው ሆኖ! ይሄን ምስል ሳየው እስከአሁን ምስሎቹን በወረቀት ሳየው ከተሰማኝ የተለየ ስሜት ተሰማኝ። የሆነ የሚያፍን ፈንጠዝያ! ልቤ ሰውነቴ ውስጥ ይነጥር ጀመር። ስልኬን በችኮላ ብነካካውም በኮድ ተዘግቷል። ተስፋ ቆርጬ መሬቱ ላይ እንደተቀመጥኩ

«እትዬ ስልኮትን በፊትዎት ነው ሲከፍቱ ያየሁት!» አለችኝ። እንዳልገባኝ አውቃ ስልኩ እጄ ላይ እንዳለ ወደ ፊቴ ስታቀርበው እውነትም የኮድ ምልክቱ ተነሳ። የሚቀጥለውን ፍለጋዬን ለማድረግ በረጅሙ ተነፈስኩ። ወዲያው ስልኩ በመደዳ የማያቆም ተደጋጋሚ ድምፅ ያሰማ ጀመር። ለምን እንደሆነ ድምፁ ረበሸኝ። የሆነ ቀጥሎ መጥፎ ክስተት ይከሰት ይመስል ጭንቅላቴን ወጠረኝ። መሬቱ ላይ አስቀመጥኩት። የሆነ ግጭት ጭንቅላቴ ውስጥ የተከሰተ መሰለኝ። የሆነ የተኩስ ድምፅ ነገር።

«ምነው እትይ? አመሞት እንዴ? » ወድያው አስከትላ «ጎንጥ! አንተ ጎንጥ» ጆሮዬ ላይ አምባርቃ ተጣራች። በረንዳው ላይ የነበረ መሰለኝ

«ምንድነው?» ዘሎ አጠገቤ ደረሰ።
«እኔእንጃ የስልኩ ድምፅ ረበሸኝ።» አልኩት ስልኩን ካስቀመጥኩበት አንስቼ እያቀበልኩት።

«ደውሎ ያጣዎትን ስልክ መልእክት እየላከልዎት ነውኮ! ሌላም መልዕክቶች አሉት።»
«የሚጠቅም ነገር ካለው አንብብልኝ» አልኩት ልቤ ለምን እንደፈራ ሳላውቀው እየተርበተበተብኝ። ዝም ብሎ ስልኩን ሲነካካ ቆይቶ

«ሾካካ የሚባል ሰው 'ዛሬ ፖሊሶች ለድንገተኛ ፍተሻ ስለሚመጡ ቤቱ ይፅዳ' የሚል መልዕክት ልኮልዎት ነበር። ኦው ብዙ መልዕክት ነው የላከው። 'ምነው ዘጋሽኝ? በሰላም ነው ስልክሽ የማይሰራው?'......... 'ኸረ ምንድነው ጉዱ አንቺ ሳትኖሪኮ ቤቱ ስርዓት አጣ! '...... »

«ተስተምረሃል እና?» አለች ተናኜ በጣም በተገረመ አባባል አገጭዋን በእጅዋ ደግፋ ጎንጤን እያየችው። እሷ ማንበብ እንደማይችል እንዴት አሰበች እኔ እንዴት እንደሚያነብ እርግጠኛ ሆንኩ? አላውቅም! እሱ ተናኜን ቁጣና ግልምጫ ደባልቆ ለግሷት ወደንባቡ ሲመለስ የሚያነብበት ስልት እና ፍጥነት ስለእርሱ ብዙ የማላውቀው ነገር እንዳለ እንድጠረጥር አደረገኝ።

« ........ 'ሜሉ መላ ሳይገባልኝኮ ሁለት ሳምንት ተቆጠረ.' ........... እእ 'መታመምሽን በወሬ ሰማሁ መጥቼ እንዳልጠይቅሽ ቤትሽን የሚነግረኝ አጣሁ። ብደውል ስልክሽ አሁንም ዝግ ነው።'»
«ራሱ ሾካካው ነው?» ያልኩት አስቤው አልነበረም። ሁለቱም እኩል ሲስቁ አባባሌ ራሴንም አሳቀኝ! ጎንጤ ሳቁን ሲገታ «አዎ ራሱ ነው!........ ' አንቺ በቅርቡ የማትመለሺ ከሆነ ለዳዊት መላዬን እንዲቆርስልኝ ንገሪልኝ ዛሬ ሄጄ ስጠይቀው የማውቅልህ ነገር የለም ብሎ አባርሮኛል።' ......... እ ሌላ ያልተመዘገበ ቁጥር........


#አወይ_ጥርሷ



ዓይኖቿ ጥለውኝ ገና ሳልነሳ፤
ከንፈሯ ደገመኝ አቤት የኔ አበሳ።


እኔን ማለት ትታ፤
ጭራሽ በሱ ፈንታ፤
ከንፈሯን አሽሽታ፤
ሳቀችብኝ ልጅት መሬት ስወድቅ አይታ።


እኔስ...
ካ'ይኗ ከከንፈሯ እመሬት ከጣለኝ፤
የጥርሷ ድርድር ነው ይበልጥ ያቃጠለኝ።

#ሄኖክ_ብርሃኑ

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


ሀዘን አዥጎድጉዶ
መቃብር ጎድጉዶ
ስሜ እስከሚከዳኝ
ሞት እስኪከነዳኝ

ሰው እንደናፈቀኝ
ስለፍቅሯ ስቀኝ
ናፍቆት እንደያዘኝ
ቃሏ እንደመረዘኝ

መሄድ እንደፈለኩ
መቅረት እንዳማረኝ
መዳን እንደተመኘው
ሞት እንደቀጠረኝ

አይታኝ ልትሰስት
በሳጥኔ ቅስት
በፍትሃቴ ማግስት

ጥቁር ለብሳ ትቁም
እሷ ብቻ ትመጣ
ወድሃለው ትበል
አንዴ ካፉ ይውጣ

መቃባር ፈንቅዬ
ታአምር ሰራለሁ
በለቅሶዬ ድንኳን
ሰርግ እደግሳለሁ

✍ አዲብ

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


ከመቀነትሽ ሰዉሪኝ
በትንፋሽሽ አሙቂኝ
ድጋፍ ክንዴን ተንተራሽዉ
ነፍሴን ከነፍስሽ ሰዉሪዉ

ይለኛል.......
እንጃ ላንተ እንጃ ለኔ
ይሁን ይሙቅ ሰዉነቴ
ትራስ ከንፈርህ ስሜቴ

ኋላ እንጃ ግን......
ዋ ለነፍሴ ዋ'' ለሞትህ
ምን ዋስ አላት ሰዉነትህ

❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
በትዝታ ወልዴ እንደተፃፈ✍

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩ
እንዲሁም ለተጨማሪ የግጥም አልፎም ለሁሉ አቀፍ የብእር ውጤቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉን....


"ልጄ እኔ በዘመናት እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ፀሎት በአንድም በሌላም መንገድ ሲመልስ አይቻለሁ:: ያንቺ ግን ይለያል! (መገረማቸው ይሰማል) የዛሬ ሁለት ወር ገደማ የገብርኤል እለት ማግስት እዝህችው ቦታ እንደዝህችው ተቀምጠሽ 'ያለፈውን ሁሉ በላጲስ ማጥፋት ቢቻል እና እንደአዲስ ሀ ብዬ መኖር ብችል?' ነበር ያልሽኝ! 'በቃሉ: በንስሓ: በጌታችን ደም እንደአዲስ ስርየትን አጊንተሽ መኖር ትችያለሽኮ!' ብልሽ .... 'አይ አባ መች እንዲህ ቀሎ!' ነበር ያልሽኝ:: ልጄ የተመኘሽውን አዲስ ህይወትኮ ነው እግዚአብሔር የሰጠሽ!! " አሉኝ ትከሻዬን ዳበስ ዳበስ እያደረጉ.... እዚህችው መኖር አይቻልም?? ቤት አልፈልግም... ፀሃይም ዝናብም... ክረምትም በጋም ለምን እዝህችው እግራቸው ስር ሆኜ አያልፍም?

የጠየቅኩትን አዲስ ህይወት እንድፅፍ ጭንቅላቴን ነጭ ወረቀት አድርጎ እንደሰጠኝ ቢነግሩኝም ስለራሴ የነገርኳቸው ነገር ካለ እንዲነግሩኝ ጠየቅኳቸው::

"መጀመሪያ ያገኘሁሽ ቀን ... እርግጠኛ ቀኑን አላስታውሰውም... ሰባት ስምንት ወር ቢሆን ነው... እዝህችው ጋር ቆመሽ በአምላክሽ ተቀይመሽ ጮክ ብለሽ እየተጣላሽው ነበር:: እያለፍኩ ገርመም ሳደርግሽ 'ምን ያፈጣሉ? በእግዚአብሄር የተናደደ ሰው አይተው አያውቁም? ' ብለሽኝ ነው ያስቆምሽኝ.... የዛን እለት ለብዙ ዓመታት ፈልገሽ አስፈልገሽ ያገኘሻት እናትሽ ስታገኛት በማይድን በሽታ ልትሞት ወራት እንደቀራት የሰማሽ ቀን ነበር:: ... ዝርዝሩን አልጠየቅኩሽም... ሲጠይቁሽም አትወጂም.... ከዛን ቀን በሗላ ቢያንስ በሳምንት አልያም በሁለት ሳምንት አርብ አርብ ትመጫለሽ... ያሳለፍሽው ህይወት በዝርዝር ባትነግሪኝም ከባድ እንደሆነ ግልፅ ነው:: .... መጥተሽ እዚህጋ ትቀመጫለሽ... አንዳንዴ ታዋሪኛለሽ ሌላ ጊዜ በዝምታ ቆይተሽ ትሄጃለሽ.... "

"እናቴ ምን ሆነች ከዛ? የት እንደሆነች ነግሬዎታለሁ?"

"አልነገርሽኝም ልጄ! እናትሽ እኔ እስካገኘሁሽ ድረስ በህይወት ነበሩ:: ወንድም እንዳለሽ ነግረሽኛል:: ስለእናትሽ ለወንድምሽ መንገር ተጨንቀሽ ነበር:: አዝናለሁ ልጄ ከዚህ በላይ የማውቀው የለም!" አሉኝ አሁንም ትከሻዬን ዳበስ ዳበስ እያደረጉኝ.....  እናት? የት ናት? ወንድም?? ታዲያ ለምንድነው ብቻዬን የምኖረው? ለምንድነው ጎንጤም ተናኜም ፖሊሶቹም የማያውቋቸው?? እነርሱስ ቢሆን እንዴት ሊፈልጉኝ አልመጡም? ....

            ...........ይቀጥላል.......
@kederasiyan


#የመኖር አጋማሽ ..የመሞት ሲሶ ... መንገድ መሃል ..... (ክፍል አምስት)
(ሜሪ ፈለቀ)

ማነኝ?
ለመርማሪ ፖሊሱ 'ነፍሰ ገዳይ' ነኝ:: እገሌ ዶክተር ነው: ኢንጅነር ነው... ምናምን እንደሚባለው... 'እ ... ሜላት? እሷኮ ነፍሰ ገዳይ ናት!' የሚል ማዕረግ ያለኝ ነኝ:: .. ድርጊት ወይም ድርጊቶች ናቸው ማንነቶቻችን?? እንደዛስ እንኳን ቢሆን እኔ የትኛዋን ነኝ?? እንደተናኜ አባባል 'አር ከማር የምትለየዋን' የአሁኗን ሜላት ወይስ ነፍሰገዳይዋን ሜላት?

"እትዬ በሰዓቱ የሆነውን ያደረጉበትን ምህንያት: የነበሩበትን ሁናቴ እና ሌሎች አጃቢ ግብሮች ማወቅ ባልቻሉበት ሁኔታ ድርጊቱ ብቻውን የተሟላ መረጃ አይደለምኮ!!" ዝም ስለው አሁንም ይቀጥላል!

ከፖሊስ ጣቢያው ከተመለስኩ ጀምሮ ለሰዓታት የማውቃቸውን ቃላት እዛ መርማሪ ፖሊስ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጬው እንደመጣሁ ሁላ ዲዳ ሆንኩ:: ሳሎን ሶፋው ላይ እንደተጋደምኩ  ተናኜ የሚለበስ አምጥታ ደረበችልኝ:: ጎንጤ ለእኔ ይሁን ለራሱ እንጃ ብቻ ነፍሰ ገዳይነቴን ማለዘቢያ ሰበብ ያስረዳኛል::

የሚለው ነገር እኮ እውነት ነው ለምሳሌ 'ሜላት ባሏን ገደለች' ከሚለው በምንም አጃቢ ምክንያት ካልታሸ ዓረፍተ ነገር:: 'ሜላት ባሏ ሊገድላት ሲል ሽጉጡን ቀምታ ገደለችው' ቢባል ራሱ ነፍሰ ገዳይነት ግን ራሷን ለመከላከል የገደለች ትንሽ የሚታዘንላት ነፍሰ ገዳይ ያደርገኛል:: ወይም 'ሜላት እህቷን ሊገድል ሽጉጥ ደግኖ የነበረውን ባሏን እህቷን ለማትረፍ ባደረገችው ትግል የባሏ ህይወት ሊያልፍ ችሏል' ያው ነፍሰ ገዳይነት ትንሽም ጀግንነት ሁሉ ይኖረዋል:: .... የእኔው አጃቢ ሁኔታኮ 'ሜላት ባሏን ገደለች' የሚለው ልዝብ ገላጩ ነው:: ... 'አጅሪት' ያለኝ መርማሪ ፖሊስ የማስታወስ ችሎታዬን ማጣቴን ከግምት አስገብቶ በማባበል ቃል መርጦ እንደነገረኝ.... እስከዛሬ በስራው እንደእኔ ዓይነት ኬዝ ገጥሞት አያውቅም!! እንደእርሱ ገለፃ ..

የሆነ ቀን ቢሮው ተቀምጦ የተለመደ ስርቆት: ድብድብ... ወንጀሎችን ሲመረምር በሩን ከፍቼ ገባሁ:: ሁለት የሰው ቆለጥ ጠረጴዛው ላይ ዱብ ሲል ነው የገባው ሰው ባልደረባው አለመሆኑን ያወቀው... በደም የተለወሰ እጄን ልብሴ ላይ እየጠራረግሁ

" ፍሬውን ማስረጃ እንዲሆንህ ነው ያመጣሁልህ! ዋናውን ከፈለግከው አጉርሼዋለሁ:: " አልኩት:: ሬሳው ያልኳቸው ቦታ እንዳልኩትም ዋናውን ጎርሶ አገኙት:: የወንድነት ንብረቱ ከፊሉ መርማሪው ጠረጴዛ ላይ ... ከፊሉ አፉ ውስጥ ከመዝረክረኩ ውጪ በጥይት ነው የተገደለው.... ምክንያቴን እንዳስረዳ ስጠየቅ 'እንዴት እንደምገድለው ለረዥም ጊዜ ሳስብ ቆይቼ ተሳካልኝ::... ለዝህችው አቅሙ ይሄ የማይረባ.. ስንት እንዳስለፋኝ::" ብቻ ነው ያልኩት... በድርጊቴ ከልኩ በላይ መርካቴ ሲደመር ሟች ለመሬት ለሰማይ የከበደ በህዝብ ዘንድ የተወደደ ባለስልጣን መሆኑ ፍርዱን የእድሜ ልክ እስራት አስፈረደብኝ::

እኔ ይሄ ነፍሰ ገዳይነት በምን ምክንያት ቢቀመም: በምን ነባራዊ ሁኔታ ቢሰነግ ነው የሚለዝበው??

ገዳይነት ብቻ አይደለም እንደሁኔታው ሊገዝፍ እና ሊቀል የሚችለው?? የሟች ነፍስም ሊገዝፍ እና ሊቀል ይችላል... እንትን አውራጃ በነበረ የእርስ በእርስ ግጭት 200 ሰው ሞተ ከሚል ዜና እና እገሌ የሚባለው እውቁ ፖለቲከኛ ተገደለ! ከሚል ዜና ሲነፃፀር ከ200 ነፍስ የአንዱ ታዋቂ ነፍስ ይገዝፋል:: ... ያው ሞት ሚዛን ይሰፈርለታል:: ....

"እኔ ምን አውቃለሁ የሳብሽውን ገመድ!! " ብሎኝ ነበር መርማሪው የእድሜ ልክ እስራት ከተፈረደብኝ እንዴት ልወጣ እንደቻልኩ ስጠይቀው::

ሰውዬው ስለነገረኝ ይሆን አስታውሼ አላውቅም:: ዐይኔን ለመጨፈን ስሞክር የሚታየኝ ጠረጴዛ ላይ የሚንከባለል ቆለጥ ነው::....  የምግብ ጣዕም ሁሉ ደም ደም አለኝ:: .... ከዚህ በሗላ ስላለፈው ለማወቅ መቆፈሬን ማቆም ይኑርብኝ መቀጠል ግራ ገባኝ::... ፍርሃት ብቻ ነው የሚንጠኝ:: ጎንጤ አርጅቶ ሽፋኑ የተልፈሰፈሰ መፅሃፍ ቅዱስ አምጥቶ ከተኛሁበት ራስጌ እያስቀመጠ

"ባታነቢው እንኳን ከራስጌሽ ይኑር :: ከበረታሽ ግን አንብቢው ያበረታሻል:: " ብሎኝ ሲወጣ መፅሃፍ ቅዱሱን አንስቼ አገላበጥኩት:: በእርግጠኝነት የማልገልፀው የእሩቅነት ... የባይተዋርነት ስሜት ተሰማኝ:: ከመንፈሳዊነት የራቀ ህይወት እንደነበረኝ ለመረዳት ምንም ቀመር የሚያስፈልገው ሆኖ አይደለም:: እንደው ግን ቢያንስ በልጅነቴ... አንዱ የህይወቴ ቀን ላይ እንኳን ከእግዚአብሄር ደጅ ተገኝቼ አውቅ ይሆን??

"ተናኜ? ተናኜ? (በሩ ላይ ተለጥፋ እስክጠራት እየጠበቀች ይሁን ዘላ ገባች) ቤተክርስቲያን የሚለበስ ልብስ አውጪልኝ እስኪ... ይዘሽኝ ትሄጃለሽ" አልኳት... ሄዳ የሆነ የራሷን ሰፊ ጉርድ ይዛ ተመለሰች

"ይሄ ከበቃዎት ይሞክሩት እንጂ እትይ እርሶ ቀሚስ የሚመስል ነገርኮ የሎትም" አለች... ጎንጤ ብድግ ብሎ ሲከተለን

"አንተ እዚሁ ሁን ችግር የለውም!" ብዬው ነበር:: አልሰማኝም!

"የማይሆነውን! በመንገድ ምን ሊገጥሞት እንደሚችል ምን አውቃለሁ? አንዱ የጠገበ ቢጋጭዎትስ? ደሞ ቤተስኪያኑ ትንሽ ያስኬዳል እንደዚያ እርቀት ለመሄድ የሚያስችል አልጠነከሩም! ታክሲ ይጠራልዎ!" ብሎ ለሶስት በታክሲ ሄድን... ቤተክርስትያን ጊቢ ውስጥ አንዱን ዛፍ ደገፍ ብዬ ተቀመጥኩ... ተናኜ ትታኝ ልትፀልይ መሰለኝ ሄደች:: ጎንጤ ትንሽ ራቅ ብሎ እጁን ደረቱ ላይ መስቀልኛ አጣምሮ ያነበንባል:: .... የመጣሁት ላዋራው ነበር:: ልፀልይ: ልለምን.... ዝም ብቻ ነበር ግን ያልኩት... ምን ብዬ ነው የምለምነው?? ብዙ ደቂቃ ፀጥ ብዬ ተቀመጥኩ...

"ልጅ ሜላት" የሚል ድምፅ ሰምቼ ዞርኩ!! ነጭ ነጠላ ራሳቸው ላይ የጠመጠሙ : በእድሜ ተለቅ ያሉ ሰው ናቸው::

"አንቺ ነሽ? " ብለው የመገረም እና የመደሰት ቅልቅል ያለበት ፈገግታ ፈገግ እያሉ በትኩረት እያዩኝ.... " ያሰብሽው ሞላልሽ?" አሉ እየተጠጉኝ በጋቢያቸው ስር ደብቀው የያዙትን መስቀል አውጥተው እየተጠጉኝ..... ዝም ብዬ አያቸዋለሁ:: ከመፅሃፍ ቅዱሱ ይልቅ እኚህን ሰው ልቤ ያውቃቸዋል:: ብርድ ያንዘፈዘፈው ልቤ ባልገባኝ ምክንያት ሞቀው...

"ምነው ልጄ ደህናም አይደለሽ? ምነው አፍሽ ሰነፈብኝ?" አሉኝ ቀርበው ግራ በመጋባት እያዩኝ .... ጎንጤ ቀረብ ብሎ የሚሆነውን ይከታተላል:: .... ሳላስበው እንባዬ ይፈነቅለኝ ጀመር.... ለመጀመሪያ ጊዜ ከአደጋው ከነቃሁ ከወር ከአንድ ቀን በሗላ ... በስሜ ጠርቶ በፍቅር ያየኝ ሰው ገጠመኝ.... ድምፅ አውጥቼ እነፋረቅ ጀመር::

"እኔን ልጄ!! ምን ገጠመሽ? " ሲሉኝ ከተቀመጥኩበት ዘልዬ ተጠመጠምኩባቸው... ግራ እንደገባቸው ያስታውቃሉ:: አቀፉኝ..... እቅፋቸው ውስጥ ነፍሰ ገዳይ መሆኔን ረሳሁት.... ያየኝ ሁሉ ዐይን ውስጥ ያየሁትን ፍርድ እና ጥላቻ ረሳሁት... ግራ መጋባቴን ረሳሁት.... ባዶነቴን ረሳሁት .... ለደቂቃዎች ብዙ ነገሬን ረሳሁት... ሲያባብሉኝ ቆይተው .... እኔ ተቀምጬበት የነበረ ዛፍ አጠገብ ያለ ጉቶ ላይ አረፍ አሉ እንድቀመጥ እግራቸው ስር አሳዩኝ:: .... ከሁኔታቸው ከዚህ በፊት አድርጌው የማውቀው ነገር እንደሆነ ገባኝ:: እግራቸው ስር ተዘርፍጬ ጉልበታቸውን ደገፍ ብዬ የተፈጠረውን ነገር ሆስፒታል ከነቃሁ ሰዓት ጀምሬ ነገርኳቸው:: ዝም ብለው ሲሰሙኝ ቆይተው ብርዳሙ ልቤን የሚያሞቅ ፈገግታ ፈገግ ብለው::

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

513

obunachilar
Kanal statistikasi