ጰላድዮስ


Гео и язык канала: не указан, не указан
Категория: не указана



Гео и язык канала
не указан, не указан
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


ደቂቀ አትናቴዎስ(ዲ/ን ዘአትናቴዎስ) እና እኔ ጰላድዮስ በዕቅበተ እምነት ዘርፍ የተመረጡ ልጆችን እያስተማርን መሆኑ ይታወቃል። አሁን ደግሞ ስምንት(8) ልጆችን በተጨማሪ ማሰልጠን እንፈልጋለን። ስለሆነም እድሜያችሁ ከ18 አመት በላይ የሆናችሁ እንግሊዝኛ አንብቦ/ባ መረዳት የሚችል ወይም የምትችል እና በክርስትና ላይ ጥሩ መረዳት ያላችሁ እና እስልምና ላይ መስራት የምትፈልጉ ሰዎች ከታች ባለው ፎርም ላይ እስከ ቅዳሜ ምሳ ሰዓት አሳውቁን።

ፈተና ይኖረዋል😁 https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSd7WLQxB5UosUcDJpFGTMuMiUQxbIiK2Fhy-SmgFv_I-FNVFg/viewform?usp=publish-editor


#በእምነታቸው_ክፉ_ሐሳብን_ድል_ነሡት

ኅዳር ~ ፳፭

👉ዕረፍቱ ለቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት

እንኳን ለበዓለ ቅዱስ መርቆሬዎስ አደረሰን አደረሳችሁ!

"ወሀሎ አሐዱ ብእሲ ዘስሙ ፒሉፓዴር ዘበትርጓሜሁ መርቆሬዎስ ብሂል ነገረ ገድሉ መዓርዒር ለተናግሮ ዕፁብ ግብር ወዲበ ርእሱኒ አክሊል በትእምርተ መስቀል።"

"ስሙ ፒሉፓዴር የሚባል አንድ ሰው ነበር። ፒሉፓዴር የሚለው የስሙ ትርጉም መርቆሬዎስ ማለት ነው። ዜና ገድሉ እጅግ ደስ የሚያሰኝ ነው። ለመናገርም እጅግ ድንቅ ነው። በራሱ ላይም የመስቀል ምልክት ያለበት አክሊል ደፍቷል።"
(ቅዱስ ያሬድ)

(ፒሉፓዴር ገብረ ክርስቶስ = የክርስቶስ አገልጋይ ተብሎም ይተረጎማል)

"ሞዕዎ ለእኩይ ሕሊና በእምነቶሙ እስመ ሠናየ ገድለ ተጋደሉ።"

"ሰማዕታት በእምነታቸው ክፉ ሐሳብን ድል ነሡት። መልካም ገድልንም ተጋደሉ።" (ዝኒ ከማሁ)

"ሠናየ ገድለ ተጋደልኩ በድርየኒ ፈጸምኩ ወሃይማኖትየኒ ዐቀብኩ = “መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፥ ሩጫዬንም ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖቴንም ጠብቄአለሁ፤” እንዲል ፪ኛ ጢሞ ፬፥፯)

🤲ተወዳጁ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ ሆይ በምልጃህ አስበን!


ዉዶቼ ማንም : የትም : ምንም :
: ከማንም "ያነበውን" አይትፋባችሁ።.

https://www.tiktok.com/t/ZP8UQDbbg/


"ጽዮንን ክበቡአት፥
በዙሪያዋም ተመላለሱ፥
ግንቦችዋንም ቍጠሩ፤"

መዝሙር 47(48):12
እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥
ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ እንዲህ ብሎ፦ “ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤ መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ።"

መዝሙር 131(2):13

እንኳን ለቅድስት ጽዮን ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ !


"ሁሉ ሐዋርያት ናቸውን? ሁሉስ ነቢያት ናቸውን? ሁሉስ አስተማሪዎች ናቸውን? ሁሉስ ተአምራትን ይሠራሉን?
30: ሁሉስ የመፈወስ ስጦታ አላቸውን? ሁሉስ በልሳኖች ይናገራሉን? ሁሉስ ይተረጉማሉን?
31: ነገር ግን የሚበልጠውን የጸጋ ስጦታ በብርቱ ፈልጉ። ደግሞም ከሁሉ የሚበልጥ መንገድ አሳያችኋለሁ።"

1ኛ ቆሮንቶስ 12:28-31

"ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ።
22: አንዳንዶች ተከራካሪዎችንም ውቀሱ፥ አንዳንዶችንም ከእሳት ነጥቃችሁ አድኑ፥
23: አንዳንዶችንም በሥጋ የረከሰውን ልብስ እንኳ እየጠላችሁ በፍርሃት ማሩ።
24: ሳትሰናከሉም እንዲጠብቃችሁ፥ በክብሩም ፊት በደስታ ነውር የሌላችሁ አድርጎ እንዲያቆማችሁ ለሚችለው፥
25: ብቻውን ለሆነ አምላክና መድኃኒታችን ከዘመን ሁሉ በፊት አሁንም እስከ ዘላለምም ድረስ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ክብርና ግርማ ኃይልም ሥልጣንም ይሁን፤ አሜን።"

ይሁዳ 1:21-25

"ከጸለዩም በኋላ ተሰብስበው የነበሩበት ስፍራ ተናወጠ፥ በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ የእግዚአብሔርንም ቃል በግልጥ ተናገሩ።
32: ያመኑትም ሕዝብ አንድ ልብ አንዲትም ነፍስ ነበሩአቸው፥ ገንዘባቸውም ሁሉ በአንድነት ነበረ እንጂ ካለው አንድ ነገር ስንኳ የራሱ እንደ ሆነ ማንም አልተናገረም።
33: ሐዋርያትም የጌታን የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ በታላቅ ኃይል ይመሰክሩ ነበር፤ በሁሉም ላይ ታላቅ ጸጋ ነበረባቸው።
34: በመካከላቸው አንድ ስንኳ ችግረኛ አልነበረምና፤ መሬት ወይም ቤት ያላቸው ሁሉ እየሸጡ የተሸጠውን ዋጋ ያመጡ ነበርና፥
35: በሐዋርያትም እግር አጠገብ ያኖሩ ነበር፤ ማናቸውም እንደሚፈልግ መጠን ለእያንዳንዱ ያካፍሉት ነበር።
36: ትውልዱም የቆጵሮስ ሰው የነበረ አንድ ሌዋዊ ዮሴፍ የሚሉት ነበረ፥ እርሱም በሐዋርያት በርናባስ ተባለ ትርጓሜውም የመጽናናት ልጅ ነው፤
37: እርሻም ነበረውና ሽጦ ገንዘቡን አምጥቶ ከሐዋርያት እግር አጠገብ አኖረው።"

ሐዋ. ሥራ 4:31-37

"አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን ወደ እርሱ ጠርቶ፥ እንዲያወጡአቸው በርኩሳን መናፍስት ላይ ደዌንና ሕማምንም ሁሉ እንዲፈውሱ ሥልጣን ሰጣቸው።
2: የአሥራ ሁለቱም ሐዋርያት ስም ይህ ነው፤ መጀመሪያው ጴጥሮስ የተባለው ስምዖን ወንድሙ እንድርያስም፥ የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብም ወንድሙ ዮሐንስም፥
3: ፊልጶስም በርተሎሜዎስም፥ ቶማስም ቀራጩ ማቴዎስም፥ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብም ታዴዎስም የተባለው ልብድዮስ፥
4: ቀነናዊውም ስምዖን ደግሞም አሳልፎ የሰጠው የአስቆሮቱ ይሁዳ።
5: እነዚህን አሥራ ሁለቱን ኢየሱስ ላካቸው፥ አዘዛቸውም፥ እንዲህም አለ፦ “በአሕዛብ መንገድ አትሂዱ፥ ወደ ሳምራውያንም ከተማ አትግቡ፤
6: ይልቅስ የእስራኤል ቤት ወደሚሆኑ ወደ ጠፉት በጎች ሂዱ እንጂ።
7: ሄዳችሁም፦ ‘መንግሥተ ሰማያት ቀርባለች፡’ ብላችሁ ስበኩ።
8: ድውዮችን ፈውሱ፤ ሙታንን አስነሡ፤ ለምጻሞችን አንጹ፤ አጋንንትን አውጡ፤ በከንቱ ተቀበላችሁ፥ በከንቱ ስጡ።
9: ወርቅ ወይም ብር ወይም ናስ በመቀነታችሁ፥
10: ወይም ለመንገድ ከረጢት ወይም ሁለት እጀ ጠባብ ወይም ጫማ ወይም በትር አታግኙ፤ ለሠራተኛ ምግቡ ይገባዋልና።
11: “በምትገቡባትም በማናቸይቱም ከተማ ወይም መንደር፥ በዚያ የሚገባው ማን እንደ ሆነ በጥንቃቄ መርምሩ፤ እስክትወጡም ድረስ በዚያ ተቀመጡ።
12: ወደ ቤትም ስትገቡ ሰላምታ ስጡ፤
13: ቤቱም የሚገባው ቢሆን ሰላማችሁ ይድረስለት፤ ባይገባው ግን ሰላማችሁ ይመለስላችሁ።
14: ከማይቀበላችሁም ቃላችሁንም ከማይሰሙ ሁሉ፥ ከዚያ ቤት ወይም ከዚያች ከተማ ስትወጡ የእግራችሁን ትቢያ አራግፉ።
15: እውነት እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ አገር ይቀልላቸዋል።
16: “እነሆ፥ እኔ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤ ስለዚህ እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ።"

ማቴዎስ 10:1-16

"የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው፤ ነፍስን ይመልሳል፤
የእግዚአብሔር ምስክር የታመነ ነው፤ ሕፃናትን ጠቢባን ያደርጋል።
8: የእግዚአብሔር ሥርዓት ቅን ነው፥ ልብንም ደስ ያሰኛል፤
የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው፥ ዓይንንም ያበራል።"

መዝሙር 18(19):7-8

የዕለቱ ምንባባት ናቸው አንብቧቸው🤗


Through His aid hearts are lifted up, the weak are held by the hand, and they who are advancing are brought to perfection. Shining upon those that are cleansed from every spot, He makes them spiritual by fellowship with Himself. Just as when a sunbeam falls on bright and transparent bodies, they themselves become brilliant too, and shed forth a fresh brightness from themselves, so souls wherein the Spirit dwells, illuminated by the Spirit, themselves become spiritual, and send forth their grace to others. Hence comes foreknowledge of the future, understanding of mysteries, apprehension of what is hidden, distribution of good gifts, the heavenly citizenship, a place in the chorus of angels, joy without end, abiding in God, the being made like to God, and, highest of all, the being made God.
                                                                                         St. Basil the Great, On the Holy Spirit, Ch. 9

https://www.tiktok.com/t/ZP8UUe7AF/


መዝሙር 68:9
እግዚአብሔር አምላክ ቡሩክ ነው፤እግዚአብሔር በየዕለቱ ቡሩክ ነው፤የመድኃኒታችን አምላክ ይረዳናል።


https://www.youtube.com/shorts/YoSVhGJsHOc
https://www.tiktok.com/t/ZP8UDNJpk/


ዛሬ ቅዳሴ ላይ የተነበበው የቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት

Philippians 1 አማ - ፊልጵስዩስ
12: ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህ የደረሰብኝ በእውነት ወንጌልን ለማስፋት እንደ ሆነ ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ።
13: ስለዚህም እስራቴ ስለ ክርስቶስ እንዲሆን በንጉሥ ዘበኞች ሁሉና በሌሎች ሁሉ ዘንድ ተገልጦአል፥
14: በጌታም ካሉት ወንድሞች የሚበዙት ስለ እስራቴ ታምነው የእግዚአብሔርን ቃል እንዲነግሩ ያለ ፍርሃት ከፊት ይልቅ ይደፍራሉ።
15: አንዳንዶች ከቅንአትና ከክርክር እንኳ ሌሎች ግን ከበጎ ፈቃድ የተነሣ ክርስቶስን ይሰብኩታል፤
16: እነዚህ ወንጌልን መመከቻ ለማድረግ እንደ ተሾምሁ አውቀው በፍቅር ይሰብካሉ፥
17: እነዚያ ግን በእስራቴ ላይ መከራን ሊያመጡብኝ መስሎአቸው፥ ለወገናቸው የሚጠቅም ፈልገው በቅን አሳብ ሳይሆኑ ስለ ክርስቶስ ያወራሉ።
18: ምን አለ? ቢሆንም በሁሉ ጎዳና፥ በማመካኘት ቢሆን ወይም በቅንነት ቢሆን፥ ክርስቶስ ይሰበካል ስለዚህም ደስ ብሎኛል።
19: ወደ ፊትም ደግሞ ደስ ይለኛል፤ ይህ በጸሎታችሁና በኢየሱስ ክርስቶስ መንፈስ መሰጠት ለመዳኔ እንዲሆንልኝ አውቃለሁና፥






"የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።"

ሮሜ 12:2

"Since it is likely that, being men, they would sin every day, St. Paul consoles his hearers by saying 'renew yourselves' from day to day. This is what we do with houses: we keep constantly repairing them as they wear old. You should do the same thing to yourself. Have you sinned today? Have you made your soul old? Do not despair, do not despond, but renew your soul by repentance, and tears, and Confession, and by doing good things. And never cease doing this."

Saint John Chrysostom

እንኳን ለቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የፍልሰት በአል በሰላም አደረሳችሁ።
https://www.tiktok.com/t/ZP8UBXJfm/


"The man who has sharp vision for God alone is blind in all the other things that attract the eyes of the multitude.“

St. Gregory of Nyssa

https://www.tiktok.com/t/ZP8U6VFn3/


Репост из: Theo-Sophia
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ ስም ህዳር 15 በዚህች ቀን ከዐበይት ሰማእታት የሚቆጠር፣ ተአምራትን የሚያደርግና ስሙን ለሚጠሩ፣ ለሚማጸኑት ሁሉ መልስ ለመስጠት የሚፋጠን ቅዱስ/ማር ሚናስ በሰማእትነት አረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሚናስ ጸሎት ይማረን፣ የወዳጁ የቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊም በረከቱ አይለየን አሜን።

ዳግመኛም በዚህች ቀን ከእግዚአብሔር ጋር ገጽ በገጽ የተናገሩ፣ ጸጋና ሃይማኖት በተዳከመበት ግዜ አካሄዳቸውን ከእግዚአብሔር ጋር ያደረጉ፣ ስለ ሕዝብ ምሕረትና ይቅርታ በብዙ መከራ ውስጥ ያለፉ ቅዱሳን ነብያት እናቶቻችን እና አባቶቻችን ፣ "ክርስቶስ ሆይ ውረድ ተወለድ፣ ወደዚህም ምድር መጥተህ አድነን" ብለው የጾሙትን ጾም፣ የጸለዩትን ጸሎት እናስብ ዘንድ ከህዳር 15 ጀምሮ ልደትን እስከምናከብርባት ታህሳስ 29 ቀን የምትዘልቅ ጾምን እንድንጾም የቤተክርስቲያን መምህራን ስርአትን ሰሩ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በቅዱሳን ነቢያት ጸሎት ይማረን፣ በረከታቸውም ከኛ ጋር ትኑር።

እንኳን ለጾመ ነብያት በሰላም አደረሳችሁ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ በቸርነቱ ደግሞ ጾሙን በሰላም አሳልፈን ብርሃነ ልደቱን ለማየት የበቃን የተዘጋጀን ያድርገን አሜን።


https://www.tiktok.com/t/ZP8U2ufVS/

copy link አካውንቴን አድርጉት የምለቀው በተደጋጋሚ እንዳይታ እያደረገብኝ ነው። ብሎ ብሎ duet ማድረግ አልቻልኩም inappropriate እያለኝ😭


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
https://www.tiktok.com/t/ZP8UYMLpp/


Репост из: Nathan's perspective
መላዕክትን የሚያጸናው መልዓክ

ነቢዩ ዳንኤል ለ ሶስት ሱባዔ በ ጾም እና በብዙ ጸሎት ወደ አምላኩ ወደ እግዚአብሔር ጥያቄውን አቀረበ ። ጸሎትን የሚመልስ እግዚአብሔርም የሱባዔውን መልስ በ መልዓኩ እጅ ወደ ባርያው ወደ ዳንኤል ላከ።

"ፊቱ እንደ መብረቅ አይኖቹም እንደ ነበልባል ፋና" የሚያበሩለትን የዛን መልዓክ ግርማ ባየ ጊዜ ዳንኤል ጸንቶ መቆምን አልቻለም ከመልዓኩ ግርማ የተነሳ ምንም ሃይል አልቀረለትም ወደ ምድር በግንባሩ ተደፋ

ብርሃናዊው መልዓክ እጁን ልኮ በዳሰሰው ጊዜ ዳንኤል ሃይልን አጊኝቶ ቀጥ ብሎ ቆመ "በርታ ጽና" ብሎ መልዓኩ በስልጣን ተናግሮታልና ዳንዔል በረታ ጸናም።

ዳንኤልን ያበረታው ሌላ መልዓክ አለቃው ስለ ሚሆን ስለ ቅዱስ ሚካኤል እንዲህ ሲል መሠከረ "የጸሎትህን መልስ ሊያስቀር ዲያቢሎስ በ አየር በተዋጋኝ ጊዜ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ።" ዳንኤልን እንዲረዳ የተላከውን መልዓክ ቅዱስ ሚካኤል ረዳው ዳንኤልን በአፉ ቃል "ጽና" ብሎ ያጸናውን መልዓክ ቅዱስ ሚካኤል በእውነት አጸናው። መልዓኩም እንዲህ ብሎ መሰከረ"“ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም።”
— ዳንኤል 10፥21


Репост из: Tsegaye kiflu | ጸጋዬ ክፍሉ
Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ይህ ቪዲዮ በጥንቃቄ ይመልከቱት፡፡ ህጻናት ባለበት አይከፈት፡፡ ይህ አራጆቻችን እየደገሱት ያለው ድግስ ነው


ወሐቢያው : አላህ ከአርሹ በላይ ነው። እንደዛ መባሉ ችግሩ ምንድን ነው? ይላል

ጠያቂው: በጣም ከፍ ብንልስ ወደላይ🤓

ወሐብያው: በጣም ከፍ ካልን ወደላይ አላህን እናገኘዋለን😂

መንኩራኩር አዘጋጁ በቅርቡ እንሄዳለን😂


https://www.tiktok.com/t/ZP8Ud8J88/




Репост из: ጋሽ ጰላድዮስ
“It is to the humble that Christ belongs, not to those who exalt themselves above His flock. Our Lord Jesus Christ, the Scepter of God’s majesty, did not come in the pomp of pride or arrogance though He could have done so but rather in humility.“

              St. Clement of Rome

ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ “እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል፡” ይላል።

              የያዕቆብ መልዕክት 4:6
http://youtube.com/post/UgkxltD_9dZAY570s2MvwUmxI7GE7-rASp5u?si=Pw7wMBuITYrZnhaV

https://www.tiktok.com/t/ZP8U1E3mx/

Показано 20 последних публикаций.

669

подписчиков
Статистика канала